18/01/2026
እንኳን ለከተራና ለብርሀነ ጥምቀቱ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!
በሀገራችን በአደባባይ ከሚከበሩ ሀይማኖታዊና ባህላዊ በዓላት ውስጥ አንዱ የሆነው የጥምቀት በዓል በድሬደዋ በድምቀት በመከበር ላይ ይገኛል። የጥምቀት በዓል በይዘቱ ሀይማኖታዊ ቢሆንም በዋናነት የየአካባቢውን ባህላዊ ክዋኔዎች የሚንጸባረቅበት በመሆኑ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት/ዩኒስኮ/ በማይዳሰስ ቅርስነት ተመዝግቦ ከኢትዮጲያ አልፎ የመላው የአለም ህዝብ ሀብት የሆነ በአል ነው፡፡
ስለሆነም በአስተዳደራችን ይህን ታላቅ በዓል ስናከብር የድሬደዋ ነዋሪ የሚታወቅበትን የአብሮነት፣ የመከባበር፣ የመተባበርና የመደጋገፍ እሴቱን ይበልጥ በሚያጎለብቱ እና ሠላሙን በሚያስጠብቁ ተግባራት በማጀብ በድምቀት እንደሚያከብር የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት እምነቱ የጸና መሆኑን እየገለጸ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የደስታ፣ ብሎም ማህበራዊ ትስስራችንና ባህላዊ እሴቶቻችንን የሚጎለብትበት ሆኖ እንዲከበር መልካም ምኞቱን ያስተላልፋል፡፡
በድጋሚ መልካም የከተራና የጥምቀት በዓል እንዲሆንልዎ ጽ/ቤቱ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት.
ጥር 10/2018ዓ/ም.