Dire Dawa Culture & Tourism Office

Dire Dawa Culture & Tourism Office Dire Dawa The City of Peace and Love!

እንኳን ለከተራና ለብርሀነ ጥምቀቱ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! በሀገራችን በአደባባይ ከሚከበሩ ሀይማኖታዊና ባህላዊ በዓላት ውስጥ አንዱ የሆነው የጥምቀት በዓል በድሬደዋ በድምቀት በመ...
18/01/2026

እንኳን ለከተራና ለብርሀነ ጥምቀቱ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!

በሀገራችን በአደባባይ ከሚከበሩ ሀይማኖታዊና ባህላዊ በዓላት ውስጥ አንዱ የሆነው የጥምቀት በዓል በድሬደዋ በድምቀት በመከበር ላይ ይገኛል። የጥምቀት በዓል በይዘቱ ሀይማኖታዊ ቢሆንም በዋናነት የየአካባቢውን ባህላዊ ክዋኔዎች የሚንጸባረቅበት በመሆኑ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት/ዩኒስኮ/ በማይዳሰስ ቅርስነት ተመዝግቦ ከኢትዮጲያ አልፎ የመላው የአለም ህዝብ ሀብት የሆነ በአል ነው፡፡

ስለሆነም በአስተዳደራችን ይህን ታላቅ በዓል ስናከብር የድሬደዋ ነዋሪ የሚታወቅበትን የአብሮነት፣ የመከባበር፣ የመተባበርና የመደጋገፍ እሴቱን ይበልጥ በሚያጎለብቱ እና ሠላሙን በሚያስጠብቁ ተግባራት በማጀብ በድምቀት እንደሚያከብር የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት እምነቱ የጸና መሆኑን እየገለጸ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የደስታ፣ ብሎም ማህበራዊ ትስስራችንና ባህላዊ እሴቶቻችንን የሚጎለብትበት ሆኖ እንዲከበር መልካም ምኞቱን ያስተላልፋል፡፡
በድጋሚ መልካም የከተራና የጥምቀት በዓል እንዲሆንልዎ ጽ/ቤቱ መልካም ምኞቱን ይገልፃል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት.
ጥር 10/2018ዓ/ም.

06/01/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
በዓሉ የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆንላቹ ከወዲሁ እንመኛለን፡፡

መልካም በዓል!

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት
ታህሳስ 28/2018ዓ/ም.

እንኳን ለቁሉቢ ገብርኤል አመታዊ የንግስ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!ታህሳስ 19/2018 ዓ.ም በልዩ ድባብና ድምቀት የሚከበረውን የቁሉቢ ገብርኤል አመታዊ የንግስ በዓል በጉጉትና በናፍቆት ሲ...
27/12/2025

እንኳን ለቁሉቢ ገብርኤል አመታዊ የንግስ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!

ታህሳስ 19/2018 ዓ.ም በልዩ ድባብና ድምቀት የሚከበረውን የቁሉቢ ገብርኤል አመታዊ የንግስ በዓል በጉጉትና በናፍቆት ሲጠበቅ የቆየው እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምዕመን ከመላ ሀገሪቱ ወደ ትንሿ ኢትዮጲያ ድሬደዋ እየገባ ይገኛል፡፡ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራርና ነዋሪውም ለእንግዶቹ ደማቅ አቀባባል እየተደረገላቸው ነው፡፡

ስለሆነም ለቁሉቢ ገብርኤል አመታዊ የንግስ በዓል የመጡት ምዕመናን በቀጣይም በከተማችን በሚኖራቸው ቆይታ ነዋሪው በጋራ ባፈራውና በገነባው ድንቅ ቤተሰባዊ የእንግዳ አቀበቀበልና መስተንግዶ በማድረግ ቆይታቸውን አስደሳችና ማራኪ ትዝታ እንዲኖራቸው ከማድረግ ባለፈ የመጡበትን አላማ በስኬት አጠናቀው ወደ መኖሪያቸው ሲመለሱም ተገቢውን አሸኛኘት እንደምናደርግላቸው በጽ/ቤታችን ስም መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ፡፡

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት!
ታህሳስ 18/2018ዓ/ም.

27/12/2025

*እንኳን ለቁሉቢ ገብርዔል የንግስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
************************************************
ለአመታዊው የቁሉቢ ገብርዔል የንግስ በዓል ለማክበር የፍቅር ከተማ በሆነችው ድሬዳዋ እንኳን ደህና መጣችሁ እያልን እንግዶች ቆይታችሁ ያማረ እንዲሆን ከልብ እንመኛለን።

መልካም በዓል!

የድሬደዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት
ታህሳስ18/2018ዓ/ም.

አሽከርካሪዎች እንግዶች ወደ ከተማዋ ሲመጡ የድሬደዋን መልካም እሴት ባህልና ቅርሶች በማስተዋወቅ ረገድ በስፋት ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ተጠቆመ!የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት በከተ...
15/12/2025

አሽከርካሪዎች እንግዶች ወደ ከተማዋ ሲመጡ የድሬደዋን መልካም እሴት ባህልና ቅርሶች በማስተዋወቅ ረገድ በስፋት ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ተጠቆመ!

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት በከተማዋ ካሉ የባጃጅ እና ተባባሪ ታክሲ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች ጋር ውይይት አካሂዷል።

በድሬደዋ አስተዳደር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን አስተባባሪነት በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባይ በመድረኩ ላይ እንደገለፁት የአስተዳደሩን መልካም እሴቶች ባህልና ቅርሶች በስፋት ከማስተዋወቅ አንፃር የከተማ ታክሲ አሽከርካሪዎች ሚናቸው የጎላ መሆኑን ጠቁመው ለዚህም አስተዳደሩ ያሉትን ቅርሶችና ባህል እሴቶች ባግባቡ ተገንዝበው ለእንግዶች እንዲያስገነዝቡ ታሳቢ ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ እንደሆነ ጠቁመዋል።

የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባይ እንደገለጹት ከፊታችን ታህሳስ 19 ሚከበረውን የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል ለማክበር ሚመጡ እንግዶችን በፍፁም እንግዳ ተቀባይነት መንፈስ ተቀብሎ በማስተናገድ በከተማዋ ሚኖራቸው ቆይታ መልካም እንዲሆን በማስቻል ብሎም በቆይታቸው ድሬደዋ ያሏትን መስህቦች እንዲጎበኙ በማስተዋወቅ ረገድ ከናንተ ብዙ ይጠበቃል ብለዋል።

የለቱ መድረክም እንደአንድ በቤተሰብ ሆነን ከተማችንን ለማስተዋወቅ ለምናደርገው ቀጣይ ጉዞ መነሻ ነው ብለዋል። በመድረኩ በጽ/ቤቱ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኤርሚያስ በድሬደዋ በሚገኙ መስህቦችና ባህሎች ላይ የዳሰሰ ሰፋ ያለ ገለፃ ቀርቧል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት!.
ታህሳስ 6/2018ዓ/ም.

የቁልቢ ገብርኤል የንግስ ክብረ በዓልን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ::የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት የቁልቢ ገብርኤል የንግስ ክብረ በዓልን አስመልክቶ ለን...
11/12/2025

የቁልቢ ገብርኤል የንግስ ክብረ በዓልን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሄደ::

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት የቁልቢ ገብርኤል የንግስ ክብረ በዓልን አስመልክቶ ለንግስ ወደ ከተማዋ የሚገቡ እንግዶችን ለመቀበል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄዶል።

በውይይት መድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር አቶ ሀርቢ ቡህ በወቅቱ እንደገለጹት ወደ አስተዳደሩ የሚገቡ እንግዶችን ለመቀበል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በቅንጅት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በተለይም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የትራንስፖርት፣ ሆቴሎች፣ የንግድ ድርጅቶች እንዲሁም ጸጥታውን በማስጠበቅ በዓሉን በደማቅ ሁኔታ በአንድነት ለማክበር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩሉን አስተዋጾ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ወደ ድሬዳዋ ለሚገቡ እንግዶች ከተማዋን በማስተዋወቅ ረገድ በአስተዳደሩ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችን በማሳየት መረጃ በመስጠት የከተማዋን ገጽታ መገንባት እንደሚገባ የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባይ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎችም በውይይቱ ላይ እንደገለጹት ወደ አስተዳደሩ የሚመጡትን እንግዶች በከተማዋ ለሚኖራቸውን ቆይታ ተገቢውን አገልግሎት እና መስተንግዶ እንዲያገኙ ለማድረግ እየተደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው እንግዶቹን ለመቀበል ዝግጁ እና ተባባሪ እንደሆኑ አረጋግጠዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት
ታህሳስ 2/2018 ዓ/ም

ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውርን ለመከላከል የባለድርሻ አካላት የተደራጀ ትብብር ወሳኝ ሚና ይጫወታል፡፡ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን በተቀናጀ ትብብር ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውርን እንከላከል በሚል መ...
15/11/2025

ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውርን ለመከላከል የባለድርሻ አካላት የተደራጀ ትብብር ወሳኝ ሚና ይጫወታል፡፡

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን በተቀናጀ ትብብር ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውርን እንከላከል በሚል መሪ ሃሳብ ዓለም አቀፍ ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውር ቀንን ምክንያት በማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር በውይይትና በስልጠና በድሬዳዋ ከተማ እያከበረ ይገኛል፡፡

ወ/ሮ ህይወት ኃይሉ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን የቅርስ ዘርፍ ም/ ዋና ዳይሬክተር በውይይት መድረክ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፦ ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውርን ለመከላከል የባለድርሻ አካላት የተደራጀ ትብብር ወሳኝ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡

ህገ-ወጥ የቅርስ ዝውውርን የመከላከል ተግባር ዓለም አቀፍ ደረጃ ትኩረትን እንዲያገኝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና ባህል ድርጅት(ዩኔስኮ) በ2019ዓ.ም በ40ኛው አጠቃላይ ኮንፍራንስ ላይ በተላለፈው ውሳኔ መሰረት በየዓመቱ እንደ አውሮፓ አቆጣጠር ኖቨምበር 14 ዓለም አቀፍ ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውር ቀን ሆኖ ይከበራል፡፡

ዕለቱንም በማስመለከት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለስልጣን ከቅርስ ቁጥጥርና መከላከል ጋር ከሚሰሩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በጉዳዩ ላይ ውይይትና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ ይገኛል፡

ህገ-ወጥ የቅርስ ዝውውር በቅርሶች ላይ የሚደረግ ህገወጥ ንግድ፣ ዝርፊያና ዝውውርን ያካተተ እንደሆነ የተናገሩት ወ/ሮ ህይወት ኃይሉ ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውር ዓለም አቀፍና እያንዳንዱ ሀገራትን የሚመለከትና በውጤቱም የሀገራትን ባህልና ታሪክ እንዲሁም የቅርሶች መውደምና መጥፋትን ያስከትላል ብለዋል፡፡

አክለውም ማንኛውም ዜጋ በማንኛውም መስፈርት በማወቅም ሆነ ባለማወቅም የሚደረገው የህገ ወጥ የቅርስ ዝውውር ወንጀል ከመሆኑም በላይ የሀገርን ክብር አሳልፎ መሸጥ እና አስነዋሪ ተግባር መሆኑን አውቆ የራሱ ማንነትና ኩራት የሆነው ቅርስ ለመታደግ ጥብቅና መቆምና መከላከል መቻል አለበት ሲሉ ገልፀዋል፡፡

ይህ በዓለም ለስድስተኛ እና በኢትዮጵያ ለአምስተኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው የዓለም ዓቀፍ ህገ ወጥ የቅርስ ዝውውር ቀን የባለድርሻ አካላት ውይይትና ስልጠና እስከ ህዳር 06/2018ዓ.ም የሚቆይ መሆኑን የወጣው መርሃ ግብር ያመላክታል፡፡

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት.
ህዳር 2018ዓ.ም

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤትና በድሬዳዋ አሜሪካን ኮርነር የተዘጋጀ የበጎ ፈቃደኞች የእውቅና እና በማእከሉ በበጎ ፈቃደኞች የተሰራ ፕሮጀክቶች የማስተዋወቂያና እውቅና የመስጠት ...
12/10/2025

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤትና በድሬዳዋ አሜሪካን ኮርነር የተዘጋጀ የበጎ ፈቃደኞች የእውቅና እና በማእከሉ በበጎ ፈቃደኞች የተሰራ ፕሮጀክቶች የማስተዋወቂያና እውቅና የመስጠት መመርሀ ግብር ተካሄደ።

የድሬዳዋ አሜሪካን ኮርነር በተለያዩ የኮዲን የቴክኖሎጂ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ታዳጊዎችና ወጣቶችን ያስመረቀ ሲሆን በበጎ ፈቃድ ለሚያገለግሉ ግለሰቦች እውቅና ሰቷል።

በአስተዳደሩ ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤትና በድሬዳዋ አሜሪካን ኮርነር በተዘጋጀው የበጎ ፈቃደኞች የእውቅና እና በማእከሉ በበጎ ፈቃደኞች የተሰረ ፕሮጀክቶችን የማስተዋወቂያ መርሀ ግብር ላይ የተገኙት የድሬደዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ወንዶሰን አባይ መንግስት በሁሉም ዘርፎች ላይ ለዜጎች የሚያስፈልጉ አገልግሎቶችን ለማቅረብ በርካታ ጥረቶችን እያደረገ እንደሚገኝ አሁን ላይም በዚህ እረገድ አንፃራዊ የሆነ መልካም ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ይሁን እንጂ ካለው ውስን አቅም አንፃር መንግስት በሁሉም ዘርፍ ተደራሽ ለመሆን እንደማይችል በመሆኑም ባለድርሻ አካላት ያለውን ክፍተት ከመሙላት አኳያ የሚኖራቸው ሚና የጎላ እንደሆነ ፅህፈት ቤት ኃላፊው ገልፀዋል።

የድሬዳዋ አሜሪካን ኮርነር በተለይ ችግር ፈቺ የሆኑ ስራዎችን ብሎም የቴክኖሎጂ ውጤቶች በማፍለቅ እረገድ የሚሰጠው አገልግሎት ለአስተዳደሩ ትልቅና ወሳኝ አቅም መሆን የሚችል መሆኑን ገልወዋል።

አስተዳደሩ ከዚህ ቀደምም ከማእከሉ ጋር በሚቻለው መጠን በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ወደፊትም በማንኛውም መልኩ የሚያስፈልጉ ድጋፎችን ለማቅረብ ዝግጁ መሆኑን አቶ ወንደሰን አረጋግጠዋል።

ማዕከሉ አገልግሎቱን የሚያቀርበው በነፃ ሲሆን ዘመኑ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በውስጡ የያዘ መሆኑን በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዲሁም በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ላይ ያሉ ተማሪዎችን ታሳቢ ያደረጉ አገልግሎቶችን በርካቶችን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ የድሬዳዋ አሜሪካን ኮርነር ፕሮግራም ዳይሬክተር ወ/ሮ ዘቢባ ሙሰማ በወቅቱ ገልጸዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ማእከሉ በአስተዳደሩ አጠቃላይ እንቅስቃሴ የሚደግፉ ስራዎችን ለማከናወን እቅድ እነዳለው በተለይም ድሬዳዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የበኩሉን ሚና ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን ፕሮግራም ዳይሬክተሯ ጨምረው ገልፀዋል።

ኮርነሩ የተለያዩ ወጣቶችን የቴክኖሎጂና ዲጂታል ይዘት ባላቸው ዘርፎች ለአመታት እያሰለጠነ እንደሚገኝ፣ ከዚህም በተጨማሪ ከተለያዩ ዩንቨርሲቲዎች የሚመጡ ተማሪዎችን የኢንተረን ሺፕ እንዲሰሩ እድሎች መፍጠሩን፣ በኮርነሩ የሰለጠኑ ተማሪዎች በተለያዩ አገር አቀፍ ውድድሮች ላይ ተሳትፈው አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ መቻላቸውን ፕሮግራም ዳይሬክተሯ አብራርተዋል።

ምንም እንኳን ማእከሉ ለወጣቱ እንዲሁም ለአጠቃላይ ማህበረሰቡ በእውቀት በቴክኖሎጂ ልማትና መረጃ ማበልፀግ እረገድ አገልግሎቶችን በበጎ ፈቃድ በነፃ ቢሰጥም ተጠቃሚዎችን በማብዛት በኩል ውስንነቶች እንዳሉ ፣ ይህንንም ለመቅረፍ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ ወላጆች፣ማህበረሰቡ እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት አንደሚገባ ወ/ሮ ዘቢባ ጥሪ አቅርበዋል።

በሌላ በኩል የድሬዳዋ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ፅ/ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ አንድነት ኪዳነ በዚህ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ዘመን ተወዳደሪ ሆኖ መገኝት ጊዜው የሚጠይቀው ወሳይ ጉዳይ መሆኑን ገልፀው አስተዳደሩ የተቋማትን አገልግሎትን ጨምሮ በርካታ ዘርፎችን በቴክኖሎጂ የማዘምን ስራዎችን እያከናወነ እንደመገኝ ወደፊትም ይህንን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።

ዜጎች በተለይ ወጣቶች በመንግስትም ሆነ በባለኡ ድርሻ አካላት የሚቀርቡ እራስን ለማብቃት የሚያስችሉ እድሎቸን በሚገባ መጠቀም እነደሚገባቸው ጠቁመዋል።

የድሬዳዋ አሜሪካን ኮርነር በአገር አቀፍ ደረጃ ከሚንቀሳቀሱ 6 ማእከላት አንዱ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት
ጥቅምት 2018 ዓ/ም.

04/10/2025

እንኳን ለ2018 ኢሬቻ በዓል አደረሳችሁ!

እንኳን ለ2018 ዓ.ም የኢሬቻ በዓል በሰላም፣ በፍቅር እና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ። በዩኔስኮ የተመዘገው የኦሮሞ ገዳ ሥርአት አካል የሆነው የኢሬቻ በዓል የሀገራችንን መልከ-ብዝሃነት፣ ጥልቅ ዉበት ለመላዉ ዓለም ካሳዩ እና ካስተዋወቁ በዓላት መካከል አንዱ ሲሆን ኢሬቻ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ለፈጣሪ አምላክ ምስጋና የሚቀርብበት፣ ከሰው ጋር ሰላም፣ ፍቅር እና አብሮነት የሚከናወንበት፣ አዲስ ተስፋና ብሩህ ዘመን የሚበሰርበት በዓል ነው።

መልካም የኢሬቻ በዓል!

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት
መስከረም 2018 ዓ/ም.

እምርታ ቤተ-መፅሀፍ! በመደመር መፅሀፍ ሽያጭ እና በአስተዳደሩ በጀት ድጋፍ በ475 ሚሊዮን ብር በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የተሰራው እምርታ ቤተ-መፅሀፍ ወደ አገልግሎት ለማስገባት የግብአት ...
01/10/2025

እምርታ ቤተ-መፅሀፍ!

በመደመር መፅሀፍ ሽያጭ እና በአስተዳደሩ በጀት ድጋፍ በ475 ሚሊዮን ብር በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የተሰራው እምርታ ቤተ-መፅሀፍ ወደ አገልግሎት ለማስገባት የግብአት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሄዷል።

በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በተፃፈው በመደመር ትውልድ መፅሀፍ ሽያጭ እንዲሁም በአስተዳደሩ ድጋፍ ዘመናዊና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የተገነባው እመርታ ቤተ-መፅሀፍ አሁን ላይ የግንባታ ሂደቱ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት ለማስገባት የግብአት ማሰባሰቢያ መድረክ ከፌደራል የመጡ የተለያዩ የላይብረሪና ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች፣ በአስተዳደሩ የሚገኙ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እና ተቋማት በተገኙበት በድምቀት ተከፍቷል።

በመድረኩ ላይ የተለያዩ ግብአቶችን ከባለ ድርሻ አካላት ማለትም ከአብርሆት ቤተ-መፅሐፍት፣ ከኢትዮጵያ ቤተ-መፅሐፍት እና መዛግብት፣ ከኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ሽግግር ኢንስቲቲዩት እና ከአስተዳደሩ ነዋሪዎች የተለያዩ የመፅሐፍት ድጋፎች በዛሬው እለት አየተረከብን እንገኛለን።

ስለሆነም በአስተዳደሩ የምትገኙ የመንግስትና የግል የት/ት ተቋማት፣ ባለሀብቶች እና የአስተዳደሩ ነዋሪዎች ለዚህ ቤተ-መጽሀፍት የተለያዩ ስጦታዎችን እና ድጋፎችን ማበርከት የምትፈልጉ በሙሉ በእምርታ ቤተ-መፀሐፍት ግቢ ውስጥ በተከፈተው የግብአት ማሰባሰቢያ ቢሮ በመምጣት ድጋፍ ማድረግ እንደምትችሉ ጥሪያችንን እናስተላልፋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት
መስከረም 21/1/2018 ዓ/ም.

01/10/2025

እምርታ ቤተ-መፅሐፍ.
#ድሬዳዋ

እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት በአደባባይ ከሚከበሩ ታላላቅ በዓላት ውስጥ  በየአመቱ የሚከበረው መስከረም 16 ደ...
26/09/2025

እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ

በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት በአደባባይ ከሚከበሩ ታላላቅ በዓላት ውስጥ በየአመቱ የሚከበረው መስከረም 16 ደመራና መስከረም 17 የመስቀል በአል እንኳን አደረሳቹ፡፡

በአሉ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት በአለም አቀፍ የሰው ልጅ ወካይ ቅርስ ሆኖ የተመዘገበውን የመስቀል በዓል ሀይማኖታዊና ባህላዊ እሴቱንና ትውፊቱን በጠበቀ መልኩ በማክበር ያለው ለሌው በማካፈል እና በመረዳዳት እንድናሳልፍ እያልን በአሉ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆንልዎ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን።

መልካም በዓል!

የድሬደዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት!
መስከረም 16/2018 ዓ/ም.

Address

Dire Dawa

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:30
Tuesday 08:00 - 17:30
Wednesday 08:00 - 17:30
Thursday 08:00 - 17:30
Friday 08:00 - 17:30

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Dawa Culture & Tourism Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share