Dire Dawa Culture & Tourism Office

Dire Dawa Culture & Tourism Office Dire Dawa The City of Peace and Love!

እንኳን ለ2019 ኢዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን፡፡==============================የድሬደዋ አስተዳደር ነዋሪ በጋራ ካፈራቸውና ከገነባቸው ጠቃሚ ማህበራዊ እሴቶች ውስ...
11/09/2026

እንኳን ለ2019 ኢዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን፡፡
==============================
የድሬደዋ አስተዳደር ነዋሪ በጋራ ካፈራቸውና ከገነባቸው ጠቃሚ ማህበራዊ እሴቶች ውስጥ ሀይማኖታዊና ሀገራዊ/ብሔራዊ በዓላትን በጋራ በመሰባሰብ ፣ በመጠያየቅ በመረዳዳትና ቤት ያፈራውን በመቋደስ በድምቀት ማክበሩ አንዱና ዋንኛው መሆኑ ይታወቃል ፡፡

በመሆኑም የሀገራችን ጸጋ በሆነችው የጳጉሜ ወር 5 ቀናቱንም በማክበር እነሆ አዱሱ አመት በደማቁ በማክበር ላይ እንገኛለን።

እነሆ አሮጌውን 2018 ሸኝተን አዲሱን 2019 አመት እንደወትሮው ከአመት አመት የምንሻገርበት ብቻ ሳይሆን በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ባካሄድንበትና በበርካታ ሀገራዊ ጉዳዮች መግባባት መፍጠር በተቻለበት ማግስት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ፡፡

ስለሆነም በድሬደዋ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኦንቨስትመንት ቢሮ የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ለመላው ነዋሪ ለአዲሱ የ2019 የዘመን መለወጫ በአል እንኳን አደረሳችሁ እያለ አዲሱ አመት በ2018 በባህልና ቱሪዝም ኢንዱስትሪ ላስመዘገብናቸው ሁሉን አቀፍ ውጤቶችና ድሎች ለነበራችሁ የነቃ ተሳትፎ እያመሰገነኩ በአዲሱ አመትም ድሎቻችንና ውጤቶቻችንን ለማስቀጠልና ለማበልጸግ እንዲሁም የጋራና የወል ትርክትን በሀገራዊ አብሮነት ለማጽናት በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅበትን አስተዋጾ እንደሚያበረክትና ሀላፊነቱን እንደሚወጣ ያለኝን ጽኑ እምነት እየገለጽኩ አዲሱ አመት የሠላም፣የደስታ፣የፍቅር፣የብልጽግና አመት እንዲሆንልን መልካም ምኞቴን እያስተላለፍኩ በድጋሚ እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ አደረሰን እላለሁ፡፡

አቶ ወንደሰን አባይ
=======የድሬዳዋ አስተዳደር የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት===

11/09/2026
የምስራቋ ጸሐይ፤ ድ.....ሬ........ዳ.......ዋ🌅🚆✈️🚍☀️⚽️🚴‍♀️🎤🎭⚙️🍊=========================ድሬዳዋ፤ የበረሃዋ ንግሥት ይሏታል! ትንሿ ኢትዮጵያ በሐረርጌ ደጋማ...
30/08/2026

የምስራቋ ጸሐይ፤ ድ.....ሬ........ዳ.......ዋ
🌅🚆✈️🚍☀️⚽️🚴‍♀️🎤🎭⚙️🍊
=========================
ድሬዳዋ፤ የበረሃዋ ንግሥት ይሏታል! ትንሿ ኢትዮጵያ በሐረርጌ ደጋማ ምድር ግርጌ የምትገኝ፣ በሙቀትና በውበት የምትታወቀው የባቡር ሐዲድ ትንፋሽ የፈጠራት ድንቅ ከተማ ናት።

ዛሬ ድሬዳዋ የድሮ ትውስታዎቿንና የሰፈሮቿን ስነ ጽሑፋዊ ናፍቆት ሳትለቅ፣ የኢንዱስትሪ፣ የንግድ ማዕከልነቷን እንደያዘች ዘመናዊነቷን እንዳስጠበቀች ታላቅ የኮሪደር ልማት እያስተናገደች ትገኛለች።

ይህ የኮሪደር ልማት ተራ የመንገድ ግንባታ ሳይሆን፤ የከተማዋን ነፍስ ከዘመናዊ የከተማ ፍልስፍና ጋር የማዋሃድ ጥበብ ነው።

ይህች የኢንዱስትሪ መጀመሪያና የከተማ ማስተር ፕላን የተጀመረባት ለኪነ ጥበብ ቅርብ ሆና ሁሌም የምትናፈቅ፣ በድምጻውያን አንደበት የተዘፈኑላት ውብ ስንኞች የከተማዋን ሕያውነት ይመሰክራሉ።

ታዋቂው ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ "ከጥንት አንስቶ እስከ ዛሬ ሲዘፈን ኖሯል ለድሬ ፤እኔም አለሁሽ እላለሁ መች አንደበቴን አስራለሁ ..'' እያለ ስለ ከተማዋ ውበትና ናፍቆት ሲያንቆረቁር፣ የድሬዳዋ ልጅ የሆነው ድምጻዊ አሊ ቢራ በበኩሉ በአፋን ኦሮሞ ዜማዎቹ የከተማዋን የባህል ብዝሃነትና የወንድማማችነት ስሜት በክብር አንስቷል።

ዛሬ ያ የተዘፈነላት ውብ አየርና ፍቅር፣ በኮሪደሩ ልማት አማካኝነት ሌላ አዲስ መልክና ዘመናዊ መዋቅር ተላብሷል። የቀደሙት ስንኞች የናፍቆት ነበሩ፤ የዛሬዎቹ ግን የዕድገትና የውበት ምስክር ሆነዋል።

ታሪካዊቷ እና የንግድ ማዕከል የሆነችው ድሬዳዋ ታሪካዊ ቅርሶቿን ከዘመናዊ የከተማ መሠረተ ልማት ጋር በሚያስማማ ሁኔታ በተጀመረው የልማት ፕሮጀክት፣ ነዋሪዎችንና ጎብኚዎችን የሚስቡ ዘመናዊና ምቹ መዝናኛዎችን እየፈጠረች ይገኛል።

ይህ የከተማ ዘመናዊነት ራሱን የቻለ ጥልቅ ፍልስፍና አለው። ለዘመናዊ ከተማ ግንባታ ስኬት፣ ታዋቂዋ አሜሪካዊት የከተማ ጥናት ምሁርና ደራሲ ጄን ጃኮብስ "The Death and Life of Great American Cities" በተሰኘው ቀዳሚ መጽሐፏ ላይ ከተሞች ለሁሉም ሰው የሚሆኑት፤ በሁሉም ሰው በጋራ ሲገነቡና ሲታሰቡ ብቻ እንደሆነ በፅኑ ትሞግታለች።

ከተማ መገንባት ያለባት ለተሽከርካሪዎች ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጆች መሆኑን የምታነሳው ጃኮብስ፤ የድሬዳዋ ኮሪደር ልማት በትክክል የዚህን ፍልስፍና ፈለግ እንዲከተል አድርጋለች ማለት ይቻላል።

ሰፊ የሳይክልና የእግረኛ መንገዶች፣ የሕዝብ መዝናኛ አረንጓዴ ስፍራዎች እና ክፍት ቦታዎች በምድር በባቡርና ማርያም ቤተክርቲያን አካባቢ እንዲሁም በጥንታዊው የኮኔል ገበያ ስፍራ በተሰራው የኮሪደር ልማት ተፈጥረዋል፡፡ በዚህም ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ሕያው እና ተደራሽ እያደረጋት ነው።

ድሬዳዋ የሰፈሮቿ ስም ብቻ ሳይሆን የታሪክ ማህደርም በመሆኗ፤ እያንዳንዱ ሰፈር የራሱ የስነ-ጽሑፍ ጥልቀትና ትረካ አለው። በአሁኑ ወቅት የከተማዋን ሰፋፊ ክፍሎች በማካተት በተለያዩ ምዕራፎች በመተግበር ላይ ያለው የኮሪደር ልማት እነዚህን ታሪካዊ ሰፈሮች አዲስ ገጽታ እያላበሳቸው ይገኛል።

የውጪ ዜጎችና የባቡር ሰራተኞች መኖሪያ የነበረችውና የዘመናዊቷ ድሬዳዋ መነሻ የሆነችው ከዚራ፤ ዛሬ በኮሪደሩ ውበት ተኳኩላ ጥንታዊ የስነ ሕንጻ ይዘቷን ሳታጣ በዘመናዊ መብራቶችና ንጹሕ መንገዶች አሸበርቃለች።

የከተማዋ የልብ ትርታና የትራፊክ መገናኛ የሆነው መገንጠያ ደግሞ በአረንጓዴ ተክሎችና ውብ የትራፊክ ደሴቶች ተውቦ የዘመናዊነት ማሳያ ሆኗል። ይህ የልማት መስመር እስከ ድሬዳዋ ምግብ ኮምፕሌክስ ዘልቆ የኮሪደሩ ዋነኛ አካል ሆኖ እናገኘዋለን።

የንግድ ታሪክ መናገሻ የነበረው ታይዋን የተመሰቃቀለው ገጽታው ቀርቶ በንጹሕ የእግረኛ ኮሪደርና በሥርዓት በተደራጁ ሱቆች ሲተካ፤ የከተማዋን ታሪክ የወሰነውና በጎርፍ አደጋው የሚታወቀው ደቻቱ ወንዝ በበኩሉ፤ የደራሽ ጎርፍና የውሃ መከማቸት ችግርን በሚፈቱ ዘመናዊ የውሃ ፍሳሽ ማስወገጃዎች፣ ቦዮችና ዳርቻው ላይ በተገነቡ ማራኪ መናፈሻዎች ታግዞ ከአስፈሪነት ወደ ማራኪ የቱሪስት መስህብነት ተቀይሯል።

ይህ ሁሉ ልማት ለድሬዳዋ ነዋሪዎች የሰጠው ትልቁ ስጦታ የክብር እና የአኗኗር ዘይቤ ለውጥ ነው። ፕሮጀክቱ በመላው የከተማዋ ክፍሎች ላይ ወጥ በሆነ መልኩ እየተተገበረ በመምጣቱ በርካታ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎችን አምጥቷል።

ነዋሪው ማታ ማታ ወጥቶ በነጻነት የሚተነፍስባቸው፣ ህጻናት የሚጫወቱባቸው እና ወጣቶች የሚያነቡባቸው የአረንጓዴ መናፈሻዎችና የውሃ ፏፏቴዎች መፈጠራቸው የህዝብን የባለቤትነት ስሜት ከፍ አድርጎታል።

በሌላ በኩል ደግሞ በፕሮጀክቱ ትግበራ ሂደት ለበርካታ ወጣቶችና የአካባቢው ነዋሪዎች ሰፊ የሥራ ዕድል የተፈጠረ ሲሆን፣ በኮሪደሩ ዳርቻ የተከፈቱ አዳዲስ ካፌዎችና ሱቆች ለአነስተኛና መካከለኛ ነጋዴዎች አዲስ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።

ከዚህም ባለፈ በምሽት በሚደምቁ ዘመናዊ የመንገድ መብራቶች ምክንያት የከተማዋ የምሽት ኢኮኖሚ ከዚህ በፊቱ በበለጠ ነቅቷል፤ ከተማዋን ወደ ስማርት ሲቲ የሚያሸጋግሩ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መሙያ ጣቢያዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች መካተታቸውም የነዋሪውን የደህንነት ስሜትና የቴክኖሎጂ ሽግግር አረጋግጠዋል።

ድሬዳዋ ዛሬም ያቺው የፍቅር እና የባቡር ከተማ ናት። ነገር ግን አሮጌውን የትናንት ካፖርቷን አውልቃ፣ ለኑሮ ምቹና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ዘመናዊ መልክ ተጎናጽፋለች።

የኮሪደር ልማቱ ድሬዳዋን በታሪኳና በነፍሷ ላይ አዲስ የወጣትነት መልክ የቀባ፣ ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ውድ ስጦታ ያደረገ ድንቅ ስራ ነው። ይህ የልማት ጉዞ ኢንቨስተሮች በሆቴልና በሬስቶራንት ዘርፍ እንዲሁም የጤና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግም በርካታ የጤና ተቋማት እየተገነቡ ወደስራ በመግባታቸው ከከተማዋ የእንግዳ ተቀባይነት ጋር ተዳምሮ አቅም እንዲያሳድጉ ትልቅ በር ከፍቷል።

ድሬዳዋ አሁንም የምስራቋ ንግሥት እና የሁሉም ኢትዮጵያዊ መኖሪያ በመሆኗ "ትንሿ ኢትዮጵያ" እስከመባል ደርሳ፣ አሁን ደግሞ በኮሪደር ልማት የተዋበ አዲስ የዘመናዊነት ዘውድ የደፋች ንግሥት ሆናለች።

መረጃ:-FANA BC

የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ  ወደ ላቀ ደረጃ ለማሽጋገር በተቀናጀ አሰራር፣ በጋራ እቅድ እና በተናበበ ሪፖርተር  መተግበር እንደሚገባ ተገለፀ።====================በቱሪዝም ዘርፍ ...
29/08/2026

የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሽጋገር በተቀናጀ አሰራር፣ በጋራ እቅድ እና በተናበበ ሪፖርተር መተግበር እንደሚገባ ተገለፀ።
====================
በቱሪዝም ዘርፍ የመካከለኛ ዘመን የልማት ኢንቨስትመንት ዕቅድና 2019-2021 በተዋረድ ዕቅድ ትስስር ላይ የፌደራል፣ የክልልና የቱሪዝም ተቋማት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ያሳተፈ ወይይት በአዳማ እየተካሄደ ነው።

የቱሪዝም ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ያለውን ጉልህ ድረሻ አስተዋጽኦ ብሎም ለሥራ እድል ፈጠራና ለሀገር ገጽታ ግንባታ ያለውን ሚና ለማጠናከር የተቀናጀ አሰራር ተግባራዊ ማድግር አስፈላጊነትን ተገልጿል።

በተለይም በፌደራል፣ በክልልና በከተሞች የሚከናወኑ የቱሪዝም ሥራዎች የጋራ እቅድ፣ የጋራ ትግበራና የጋራ ክትትል ስርዓት አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በአንክሮ አመላክተዋል ።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ.ር ) እንደገለጹት ከ2019 እስከ 2021 ዓ.ም. በሚተገበረው የመካከለኛ ዘመን የልማት እቅድ መነሻነት የቱሪዝም ዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ የፖሊሲ፣ የስትራቴጂ፣ የሀብት ልየታ እና የተቋማዊ አቅም ግንባታ ሥራዎች በቅንጅት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው ፣ የእቅዱ ስኬት በሁሉም አስተዳደራዊ እርከኖች ባለው የትብብር ደረጃ እንደሚወሰንም ገልጸዋል።

አክለውም የኢትዮጵያን የቱሪዝም ሀብቶች በተቀናጀ ሁኔታ ለዓለም አቀፍ ገበያ ማስተዋወቅ፣ አዳዲስ የቱሪስት ምንጭ ገበያዎችን መለየት፣ የጋራ የማስተዋወቂያ መድረኮችን ማዘጋጀትና የዲጂታል ማስተዋወቂያ አሰራሮችን ማጠናከር በቀጣይ ጊዜ ትኩረት የሚሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸው ተገልጿል።

በተጨማሪም የቱሪዝም አገልግሎት ጥራትን ማሻሻል፣ የዘርፉን ኢንቨስትመንት ማበረታታት፣ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር እና የጎብኚዎችን እርካታ ማሳደግ የቅድሚያ ትኩረት የሚያገኙ ጉዳዮች መሆናቸው ተጠቅሷል።

መድረኩ በየክልሉ ያሉ ልዩ የቱሪዝም አቅሞችን በመጠቀም የባህል፣ የኮንፈረንስና የንግድ ጉባኤ (MICE)፣ የጤና፣ የምግብና የስፖርት ቱሪዝም ምርቶችን በጥራት ለማበልጸግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን መለየትና እነዚህ የቱሪዝም ምርቶች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገቢ ከማሳደግ ባሻገር የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም ለኢኮኖሚው ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቶት እንዲኖራቸው ታሳቢ አድረጎ መስራት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

የመካከለኛ ዘመን የልማት ኢንቨስትመንት ዕቅድና በ2019-2021 ዕቅድ ትስስር የተመለከተው ሰነድ በአቶ ብስራት ታደስ የእቅድና በጀት ክትትል ስራ አስፈጻሚ በኩል ቀርቦ ውይይት ተደረጎበታል።

በመጨረሻም በተነሱ ጥያቄዎች ላይ በአቶ ግርማ መላኩ የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ እና በሚመለከታቸው የሥራ ክፍል ኃላፊዎች በኩል ምላሽና ማብራሪያ የተሰጡ ሱሆን የመድረኩ ተሳታፊዎች የቱሪዝም ዘርፉን ውጤታማነት ለማሳደግ በጋራ እቅድ ዝግጅት፣ በተቀናጀ ትግበራ፣ በመደበኛ ክትትልና ግምገማ እንዲሁም በተቋማት መካከል ያለውን ትብብር በማጠናከር ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።

ነሐሴ 23/2018 ዓ.ም
መረጃ:-ቱሪዝም ሚኒስቴር

የአስተዳደሩ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት በወረዳ 5 ለሚገኙ ቤተመፅሃፍት 200 የሚሆኑ መፅሃፍትን ድጋፍ  አደረገ።=================================በአስተዳደሩ በክረምት በጎ ፈ...
28/08/2026

የአስተዳደሩ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት በወረዳ 5 ለሚገኙ ቤተመፅሃፍት 200 የሚሆኑ መፅሃፍትን ድጋፍ አደረገ።
=================================
በአስተዳደሩ በክረምት በጎ ፈቃድ አካል የሆነውን አንባቢ ትውልድን ለመፍጠር እንዲቻል ወጣቶች ግዜአቸውን ከአልባሌ ቦታ እንዳያሳልፉ አንባቢ ትውልድን ለመፍጠር እንዲቻል ድጋፍ መደረጉን የአስተዳደሩ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባይ ገልፀዋል ።

ኃላፊው አክለው በመደመር መንግስት የተገነባው የእመርታ ቤተ-መፅሃፍትን ጨምሮ ከግሪክ ካምፕ የሚገኘው የህዝብ ቤተመፅሃፍት ለህዝብ ክፍት በመሆናቸው ወጣቱ እንዲጠቀምባቸው እድሉ መመቻቸቱን ገልፀዋል።

በአስተዳደሩ እየተከበረ የሚገኘው የንባብ ሳምንት በቀጣይ አንባቢ ትውልድን ለመፍጠር የተለያዩ ድጋፎች እንደሚካሄደ ተገልጿል ።

በወረዳ 5 ለሚገኘው ቤተመፅሃፍት ከመፅሃፍት በተጨማሪ 3 ዴስክቶፕ ኮምፒውተሮች ድጋፍ እንደተበረከተ አቶ ወንደሰን አባይ ገልፀዋል።

ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም
መረጃ:-ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት በአስተዳደራችን ዘጠኙም ወረዳዎች  የተውጣጡ ወጣቶችን ያላቸውን ዝንባሌና ኪነጥበባዊ ተሰጥኦ በመለየት እንደየ ዝንባሌያቸውና ፍላጎታቸው በተለያዩ ኪ...
27/08/2026

የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት በአስተዳደራችን ዘጠኙም ወረዳዎች የተውጣጡ ወጣቶችን ያላቸውን ዝንባሌና ኪነጥበባዊ ተሰጥኦ በመለየት እንደየ ዝንባሌያቸውና ፍላጎታቸው በተለያዩ ኪነጥበብ ዘርፎች እየሰለጠኑ ይገኛል።
=========================
ስልጠናው በቴአትር፣ በሙዚቃ በባህላዊና ዘመናዊ ውዝዋዜ በስነ-ስዕል እና ስነጽሁፍ ዘርፍ በማደራጀት የክህሎት ስልጠና በመስጠትና በማመቻቸት ሙያዊ ድጋፍ ና ክትትል በማድረግ የተለያዩ የስነ አእምሮ ፈጠራዎችን በማበረታታትና በመደገፍ ዘርፈ ብዙ ስራ እየተሰሩ እንደሚገኝ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባይ ገልፀዋል ፡፡

በአስተዳደሩ በተለያዩ የኪነጥበብ ዘርፍ ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች የሚሰሯቸውን የኪነጥበብ ስራዎች ሃገራችን የተያያዘችውን የልማት ጎዳና በሚያሳልጥ መልኩ በልማታዊ ኪነጥበብ መቃኘት ስላለባቸው በዘርፉ ያሉትን አማተር የኪነጥበብ ቡድኖችና ዝንባሌው ያላቸውን ወጣቶች መደገፍና ማጠናከር እንደሚገባ ኃላፊው ገልፀዋል ።

በአስተዳደሩ ፍላጎትና ዝንባሌው ያላቸውን አማተር ኪነጥበብ ቡድኖችና ወጣቶችን በመመልመል መሰረታዊ ስነጽሁፍ ምንነት ላይ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛሉ

ስልጠናው ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ብቁ ተወዳዳሪና ተተኪ ወጣትና ታዳጊ ለማፍራት ስልጠናው አይነተኛ ሚና አለው።

በድሬዳዋ አስተዳደር በስነጽሁፍ ዘርፍ በርካታ ፍላጎትና ዝንባሌው ያላቸው ወጣቶች ቢኖሩም መሰረታዊ የሚባለውን የሥነጽሁፍ ጽንሰ ሀሳብ ተረድቶ የመስራት ችግር የሚታይ በመሆኑ ስለ ስነ-ጽሁፍ ምንነት አይነት የስነጽሁፍ አላባዊያንን የስነጽሁፍ አጻጻፍ ክህሎት ማሻሻያና ማዳበሪያ ስልጠናዎች ቢሰጡ ለከተማችን የኪነጥበብ ኢንዱስትሪ ማደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሎ ስለሚታመን የስልጠናው ጠቀሜታና አስፈላጊነቱ እጅጉን የጎላ እንደሆነ በመድረኩ ተጠቅሷል ፡፡

ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም
መረጃ:-ኢ/ኢ/ቢሮ ህዝብ ግንኙነት

የሰሜን ኢትዮጵያ ባህላዊ የልጃገረዶች በዓል (አሸንዳ፣ ሻደይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል) በደመቀ ሁኔታ እየተከበሩ ይገኛሉ።=========================​በየዓመቱ ከነሐሴ 16 እስከ ነ...
25/08/2026

የሰሜን ኢትዮጵያ ባህላዊ የልጃገረዶች በዓል (አሸንዳ፣ ሻደይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል) በደመቀ ሁኔታ እየተከበሩ ይገኛሉ።
=========================

​በየዓመቱ ከነሐሴ 16 እስከ ነሐሴ 22 ባለው ጊዜ ውስጥ የሚከበሩት የልጃገረዶች ነፃነት፣ ውበት እና እኩልነት መግለጫ ክብረ በዓላት ዘንድሮም በደመቀ ሁኔታ እየተከበሩ ነው።

የሴቶች እና ልጃገረዶች የነፃነት ቀን አሸንዳ፣ ሻደይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል በዓላት ዘንድሮም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በታላቅ ድምቀት በመከበር ላይ ናቸው።

በዓሉ የጾመ ፍልሰታ ማጠቃለያን ተከትሎ የሚከበር ሲሆን፣ በዩኔስኮ (UNESCO) በማይዳሰስ ባህላዊ ቅርሥነት ለመመዝገብ ከሚደረጉ ጥረቶች ጋር ተያይዞ ልዩ ትኩረት አግኝቷል።

​አሸንዳ (ትግራይ ክልል)፦ በመቐለ፣ አክሱም፣ አድዋ እና በሌሎች የትግራይ ዞኖች የሚከበር ሲሆን፣ ልጃገረዶች ልዩ ባህላዊ አልባሳትን በመልበስ፣ አጊጠውና አሸብርቀው "አሸንዳ" የተባለውን ሳር በወገባቸው ላይ በማሰር በቡድን እየዞሩ በዘፈንና በጭፈራ ያከብሩታል።

​ሻደይ (አማራ ክልል - ዋግህምራ)፦ በሰቆጣ እና አካባቢው የሚከበር ሲሆን፣ ልጃገረዶች በታላቅ ስነ-ስርዓት ባህላዊ ዜማዎችን እያቀረቡ ከቤት እቤት በመዘዋወር በድምቀት ያከብሩታል።

​አሸንድዬ (አማራ ክልል - ወሎ)፦ በላስታ ላሊበላ፣ ወልድያ እና አካባቢዋ የሚከበር ሲሆን፣ ወጣቶች በባህላዊ ውበት አጊጠው የሚያቀርቡት የከበሮ እና የጭፈራ ስነ-ስርዓት የጎብኚዎችን ቀልብ የሚስብ ነው።

​ሶለል (አማራ ክልል - ራያ)፦ በራያ ቆቦ እና አካባቢው የሚታወቅ የበዓሉ መጠሪያ ሲሆን፣ በራያ ባህላዊ እስክስታ እና ዜማዎች ደምቆ ይከበራል።

​በትግራይ እና በአማራ ክልል በሚከበሩ የልጃገረዶች በዓል ከሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ የተወጣጡ በርካታ የባህል አምባሳደሮች፣ የውጭ ሀገር ቱሪስቶች እና የኪነ-ጥበብ ባለሞያዎች በበዓሉ ላይ በመገኘት ሲከብሩ ይስተዋላል።

በዓሉ የባህል መግለጫ ከመሆኑ ባሻገር የሴቶችን መብት ለማስከበር፣ እህትማማችነትን ለማጠናከር እና የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን ለማንቀሳቀስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።

​በዓሉ እስከ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በልዩ ልዩ ባህላዊ መርሃ-ግብሮች፣ በዘፈን እና በምርቃት ደምቆ የሚቀጥል ይሆናል።

መረጃ:-ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር

=====የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት===== =============================የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባይ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክ...
25/08/2026

=====የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት=====
=============================
የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ወንደሰን አባይ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል

በመልዕክታቸው ለመላው ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1501ኛው ለነብዩ መሐመድ (መውሊድ በዓል) በሰላም እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል

በአስተዳደሩ በባህልና ቱሪዝም ዘርፍም በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ የገለፁት ኃላፊው በአስተዳደሩ በባህል ዘርፍ መገለጫ ከሆኑት ኃይማኖታዊ ክብረ በዓላት አንዱ የሆነው ለመውሊድ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል

በአስተዳደሩ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እየተገነበ ሲሆኑ በቀጣይ አመታት ድሬዳዋን የቱሪዝም ማዕከልነቷን ለማረጋገጥ አስተዳደሩ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ በመልዕክታቸው ገልፀዋል

በመጨረሻም በዓሉ የሰላም፣የብልፅግና እንዲሆን በአንድነት በመተሳሰብ ማክበር እንደሚገባ በመልዕክታቸው አስተላልፈዋል።

=========ዒድ ሙባረክ=====

=======አቶ ወንደሰን አባይ====
የድሬዳዋ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት

የአሸንዳ፣ አይነዋሪ፣ አሸንድየ፣ ሻደይ እና ሶለል በዓላት================================በሀገራችን በድምቀት ከሚከበሩ የአደባባይ በዓላት መካከል በየዓመቱ ከነሐሴ 16 ቀን...
21/08/2026

የአሸንዳ፣ አይነዋሪ፣ አሸንድየ፣ ሻደይ እና ሶለል በዓላት
================================
በሀገራችን በድምቀት ከሚከበሩ የአደባባይ በዓላት መካከል በየዓመቱ ከነሐሴ 16 ቀን ጀምሮ እስከ ወሩ መጨረሻ ድረስ በተለያዩ ባህላዊ አልባሳት የደመቁ ሴቶች ትውፊታቸውን ጠብቀው ለዘመናት ሲያከብሩት የቆዩት የአሸንዳ፣ አይነዋሪ፣ አሸንድየ፣ ሻደይ እና ሶለል በዓላት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት መጽሐፍ ቅዱሳዊ መነሻ እንዳላቸው የታሪክ ድርሳናትና የቤተ-ክርስትያኒቱ ሊቃውንት ያስረዳሉ።

በዓሉ በተለይም በአማራ ክልል ዋግህምራና በሰቆጣ አካባቢዎች " ሻደይ" በላስታ ላሊበላና ጎንደር "አሸንድዬ" በራያ ቆቦ "ሶለል" ተብሎ የሚጠራ፤ በትግራይ ክልል "አሸንዳ" የሚል ትግረኛ ስያሜ ያለውና በክልሉ አክሱም የሚከበረዉ "አይነዋሪ" በዓል ሲሆን በሁለቱም ክልሎች ከነሐሴ አጋማሽ ጀምሮ ባሉት ቀናት ልጃገረዶች በባህላዊ አልባሳትና ጌጣጌጦች አምረውና ተውበው ከታች ነጭ ከላይ አረንጓዴ የሆነ ረጅም የሳር (ቄጠማ) ታጥቀው ውበትን የሚያወድሱ፣ ምርቃት የሚሰጡ እና ማህበራዊ መልእክቶችን የሚያስተላልፉ ግጥሞችን በባህላዊ ዜማዎች አስውበው በውዝዋዜ አጅበው በጎዳና ላይ የሚያቀርቡበት ውብ ክብረ በዓል ነው።

የበዓሉ ዋነኛ መገለጫዎች እና አከባበርን ስንመለከት ልጃገረዶችና እናቶች በየአካባቢያቸው ባህላዊ አልባሳትና ጌጦች አጊጠዉ በወገባቸው ላይ “አሸንዳ/ሻደይ” የተባለውን ከታች ነጭ ከላይ አረንጓዴ የሆነ ረጅም የሳር ልብስ (ቄጠማ) በመታጠቅ በአደባባይ በመውጣት፣ ከበሮ እየመቱና እያጨበጨቡ ባህላዊ ዜማዎችንና ግጥሞችን ይጫወታሉ።

በበዓሉ የወጣት ወንዶችን ተሳትፎ ስንመለከት ልጃገረዶቹን በማድነቅ፣ በማጀብና ከአላስፈላጊ ትንኮሳዎች በመጠበቅ ይሳተፋሉ።

በአጠቃላይ የአሸንዳ፣ አይነዋሪ፣ አሸንድየ፣ ሻደይ እና ሶለል በዓላት ልጃገረዶች ካለባቸው ድርብ ማህበራዊ ጫና ተላቀው በሙሉ ነጻነት ቀኑን ሙሉ ሲደሰቱ የሚውሉባቸው፣ ለላቀ ማህበራዊ ሀላፊነት የሚታጩበትና ትስስራቸዉን የሚያጠናክሩባቸዉ፣ የክረምት መገባደድና የአዲስ ዓመት አዲስ ብስራት ዋዜማ የሚበሰርባቸው እንዲሁም ልምላሜ የሚታይባቸው በዓላት ናቸው።

ነሃሴ 14 ቀን 2018ዓ.ም
መረጃ:-ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር

Address

Dire Dawa

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:30
Tuesday 08:00 - 17:30
Wednesday 08:00 - 17:30
Thursday 08:00 - 17:30
Friday 08:00 - 17:30

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Dawa Culture & Tourism Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share