05/08/2024
አትሌት ፅጌ ዱጉማ እና አትሌት ወርቅነሽ መሰለ ለፍጻሜ አለፉ
****************
በፓሪስ ኦሎምፒክ በሴቶች 800 ሜትር የግማሽ ፍጻሜ ውድድራቸውን ያደረጉት አትሌት ፅጌ ዱጉማ እና አትሌት ወርቅነሽ መሰለ ለፍጻሜው አልፈዋል፡፡
ዛሬ ምሽት በተደረገው የሴቶች 800 ሜትር የግማሽ ፍጻሜ ውድድር አትሌት ፅጌ ዱጉማ ከምድቧ አንደኛ በመውጣት ስታጠናቅቅ፤ አትሌት ወርቅነሽ መሰለ በበኩሏ ሁለተኛ በውጣት አጠናቅቃለች፡፡
በውጤቱም መሰረት ኢትዮጵያውያኑ ዛሬ ከምሽቱ 4 ሰዓት ከ45 ደቂቃ ላይ በሚደረገው የፍጻሜው ውድድር ለሃገራቸው ሜዳሊያ ለማምጣት ይፋለማሉ።