የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ/Dire Dawa Land Development and Management Bureau

  • Home
  • Ethiopia
  • Dire Dawa
  • የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ/Dire Dawa Land Development and Management Bureau

የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ/Dire Dawa Land Development and Management Bureau Land Adminsration and Land Related Services

የድሬደዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ እንኳን ለ1 ሺህ 447ኛው ዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ በአል) አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል። በአሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት ...
27/05/2026

የድሬደዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ እንኳን ለ1 ሺህ 447ኛው ዒድ አል-አድሃ (ዓረፋ በአል) አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

በአሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነት እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ ይመኛል።

መልካም በአል
የድሬደዋ አስተዳደር የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ

በድሬደዋ አስተዳደር የተዘረጋው የማይንቀሳቀስ ንብረት ግመታና ግብይት ስርዓት የዘርፉን አገልግሎት ለማቀላጠፍና የገቢ አሰባሰብን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ።በድሬደ...
24/05/2026

በድሬደዋ አስተዳደር የተዘረጋው የማይንቀሳቀስ ንብረት ግመታና ግብይት ስርዓት የዘርፉን አገልግሎት ለማቀላጠፍና የገቢ አሰባሰብን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ።

በድሬደዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የማይንቀሳቀስ ንብረት ግመታና ግብይት አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መሃመድ ጌዲ እንደገለጹት በድሬደዋ የተዘረጋው የግምት ስርዓት በሀገር አቀፍ የተሞክሮ ማዕከል ሆኖ እየተጠቀሰ ይገኛል።

ዳይሬክተሩ እንደገለጹት የንብረት ግመታ ስርዓቱ ራሱን የቻለ መዋቅር እንዲኖረው በመደረጉ የተገልጋዮችን ፍላጎት በተሻለ ሁኔታ ማሟላት እና ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ ተችሏል።

ባለፉት አምስት ዓመታትም ወደ 77 ሺህ የሚጠጉ ደንበኞችና ባለድርሻ አካላት ለካሳ፣ ለስም ዝውውር፣ ለግብር እና ለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የግምት አገልግሎቶች ተሰጥቷል።

የግብር አሰባሰብ ስርዓቱን ይበልጥ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ በአራት ወረዳዎች የብዝሃ ግመታ (Mass Valuation) ስራ መከናወኑ ተገልጿል።

በተጨማሪም ከግምት ስራዎች ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ ከእጅ ንክኪ በማላቀቅ በሲስተም አገልግሎት እንዲሰጥ መደረጉ ተጠቅሷል።

እንዲሁም ከ10 ዓመታት በላይ ያልተሻሻለው የነባር ይዞታዎች የኪራይ ተመን እንዲሻሻል መደረጉን እና ለ7 ዓመታት ሳይሻሻል የቆየው የጋራ መኖሪያ ቤቶች የግምት ዋጋም በወቅታዊ የገበያ ዋጋ መሠረት እንዲሻሻል ተደርጓል። በዚህም በቁርጥ ዋጋ ስሌት የተመሰረተ ዘመናዊ የግምት ስርዓት ተዘርግቷል።

በተጨማሪም የቦታ ደረጃና የሊዝ መነሻ ዋጋ ወቅታዊ በመደረጋቸው እና ልዩ ባህሪ ያላቸው ንብረቶች ላይ የልየታና የግምት ጥናቶች በመካሄዳቸው ከመሬት የሚሰበሰበውን ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መቻሉን አቶ መሃመድ ጌዲ ገልጸዋል።

ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም።

ባለፉት አምስት ዓመታት ከ2003 ዓ.ም በፊት ህጋዊ እውቅና ከተሰጠው አካል ፍቃድ ውጪ በህገ-ወጥ መንገድ ለተያዙ 7228 ይዞታዎች የይዞታ ማረጋገጫ በመስጠት ወደ ህጋዊ ስርዓት እንዲመጡ መደ...
23/05/2026

ባለፉት አምስት ዓመታት ከ2003 ዓ.ም በፊት ህጋዊ እውቅና ከተሰጠው አካል ፍቃድ ውጪ በህገ-ወጥ መንገድ ለተያዙ 7228 ይዞታዎች የይዞታ ማረጋገጫ በመስጠት ወደ ህጋዊ ስርዓት እንዲመጡ መደረጉን ጽ/ቤቱ ገለጸ።

በድሬደዋ አስተዳደር የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የመሬት ይዞታ አስተዳደር ጽ/ቤት ባለፉት 5 ዓመታት ለ11,796 ይዞታዎች የሽንሸና ፕላን በማዘጋጀት፣ ከእነዚህ ውስጥ በህግ እውቅናና ፍቃድ ለተሰጣቸው ከ2003 ዓ.ም በፊት ለተያዙ 7228 ይዞታዎች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በመስጠት ወደ ህጋዊ ስርዓት እንዲገቡ መደረጉን ገልጿል።

የመሬት ይዞታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ሁሴን መሀመድ ሳኒ እንደገለጹት፣ የህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረውን በይዞታው ላይ ህጋዊ እውቅና እንዲያገኝና ንብረት ማፍራት እንዲችል ወደ ህጋዊ ስርዓት የማምጣት ስራ በስፋት ተሰርቷል።

በዚህም በእቅድ ከተያዘው 100% በላይ አፈፃፀም መመዝገቡን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ይዞታዎቹ በፕላን መሰረት እንዲሰፍሩ በማድረግ የህብረተሰቡ የውስጥ ለውስጥ መንገድ ማስከፈት ጥያቄ ምላሽ እያገኘ መሆኑን ጠቁመዋል።

እንዲሁም ህብረተሰቡ በይዞታው ላይ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በማግኘቱ ወደ ህጋዊ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በመግባት ተጠቃሚ እየሆነ መሆኑን ገልጸው፣ ይህም አስተዳደሩ ከዘርፉ የሚያገኘው ገቢ እንዲያድግ አስተዋፅኦ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም

በኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ላይ ለቢሮው ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ። የድሬደዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ በኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ላይ ያተኮረ የግ...
23/05/2026

በኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ላይ ለቢሮው ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ።

የድሬደዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ በኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

ስልጠናው ከድሬደዋ አስተዳደር ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ተሰጥቷል።

በስልጠናው ላይ ኤች አይ ቪ የሚተላለፍባቸው መንገዶች፣ የመከላከያ ዘዴዎች፣ የቅድመ ምርመራ አስፈላጊነት እና አለም አቀፍ፣ ሀገር አቀፍና እንደ ድሬደዋ የስርጭት መጠን እና ይበልጥ ተጋላጭ የማህበረሰብ ክፍሎች ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

ስልጠናውን ከድሬደዋ አስተዳደር ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት የኤች.አይ.ቪ ኤድስ ዘርፈ ብዙ ምላሽ አፈጻጸም ክትትልና ግምገማ ባለሞያ አቶ ጅኔይድ ኢብራሂም የሠጡ ሲሆን የመንግስት ሰራተኞች በስራ ቦታቸው እና በማህበረሰቡ ውስጥ ትክክለኛ መረጃን በማስተላለፍ በበሽታው መከላከል ላይ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።

በመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የሴቶች፣ ወጣቶችና ኤች አይ ቪ ኤድስ ጉዳዮች ባለሙያ ወ/ሮ እህትአገኘሁ በቀለ ሰራተኞች ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት በስራ ቦታቸውና በማህበረሰብ ውስጥ በማጋራት
የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም

ኤጀንሲው ባለፉት ስድስት ዓመታት ከ40 ሺህ በላይ ይዞታዎችን ማረጋገጡን ገለጸ።በድሬደዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ በአዋጅ ከተቋቋመ...
22/05/2026

ኤጀንሲው ባለፉት ስድስት ዓመታት ከ40 ሺህ በላይ ይዞታዎችን ማረጋገጡን ገለጸ።

በድሬደዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ በአዋጅ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ 40 ሺህ 587 የመሬት ይዞታዎችን ማረጋገጡን የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ኢንቲሳር አብዱረህማን ገልጸዋል።

ዋና ዳይሬክተሯ እንዳሉት፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ ነዋሪዎች የ“ይረጋገጥልኝ” ጥያቄ በስፋት እያቀረቡ በመሆኑ፣ በየዓመቱ የሚረጋገጡ ይዞታዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን አስረድተዋል።

በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት
4 ሺህ 562 ይዞታዎች መረጋገጣቸውንም ጨምረው ገልጸዋል።

በተጨማሪም እስከ መጋቢት 2018 ዓ.ም ድረስ 21 ሺህ 959 ይዞታዎች በመዝጋቢ ተቋሙ መመዝገባቸውን እና ኤጀንሲው ለ67 ሺህ 456 ተገልጋዮች አገልግሎት መስጠቱን አመልክተዋል።

ግንቦት 14 ቀን 2018 ዓ.ም

ባለፉት አመታት 954.81 ሄክታር መሬት ለልማት መተላለፉን ቢሮው ገለጸ፡፡የድሬደዋ አስተዳደር የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ባለፉት አምስት አመታት የመሬት ፍላጎትና የአልሚዎችን የማልማት ...
21/05/2026

ባለፉት አመታት 954.81 ሄክታር መሬት ለልማት መተላለፉን ቢሮው ገለጸ፡፡

የድሬደዋ አስተዳደር የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ባለፉት አምስት አመታት የመሬት ፍላጎትና የአልሚዎችን የማልማት አቅም መሰረት ባደረገ አግባብ 954.81 ሄክታር መሬት ማስተላለፍ መቻሉን ምክትል የቢሮ ኃላፊና የመሬት ልማት ባንክና ከተማ ማደስ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሁሴን ጌዲ ገልጸዋል፡፡

በበጀት አመቱ ባለፉት አስር ወራት ብቻ 158.3 ሄክታር መሬት ለኢንቨስትመንት፣ ለማኑፋክቸሪንግና ለተለያዩ አገልግሎቶች እንዲውሉ መተላለፋቸውን ጨምረው ተናግረዋል።

የአልሚውን አቅም መሠረት ያደረገ ከፍተኛ የመሬት አቅርቦት ስራ መሠራቱን የገለጹት ኃላፊው በዚህም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኢንቨስትመንትን መሳብ መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም ለነዋሪዎች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር በአስተዳደሩ ልማትን ለማፍጠን የበኩሉን እንዳበረከተ አብራርተዋል፡፡

ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ከመሬት ዘርፍ የሚገኘውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ባለፉት አስር ወራት ግማሽ ቢልየን ብር የሚጠጋ ገቢ መሰብሰቡን ገልጿል።የድሬደ...
20/05/2026

ከመሬት ዘርፍ የሚገኘውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።

የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ባለፉት አስር ወራት ግማሽ ቢልየን ብር የሚጠጋ ገቢ መሰብሰቡን ገልጿል።

የድሬደዋ አስተዳደር የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ሳጅድ አልዪ እንደገለጹት ቢሮው በበጀት አመቱ ባለፉት አስር ወራት ከመሬትና መሬት ነክ ዘርፎች ግማሽ ቢልየን ብር የሚጠጋ ገቢ መሠብሠቡን ገልጸዋል።

ቢሮው በየጊዜው ገቢን የመሰብሰብ አቅሙን እያሳደገ የመጣ ሲሆን ባለፉት አምስት አመታት ከመሬት ዘርፉ ከ1.5 ቢልየን ብር በላይ ገቢ የተሰበሰበ ሲሆን ይህም ከቀደሙት አመታት (2008-2013) ጋር ሲነጻጸር አራት እጥፍ ብልጫ አሳይቷል።

ቢሮው የሚሰበስበውን ገቢ ለማሳደግ በርካታ የማሻሻያና የሪፎርም ስራዎች ማከናወኑን የገለጹት ኃላፊው የዘርፉ አገልግሎት ፈጣንና ተደራሽ እንዲሆኑ መደረጉን ገልጸዋል።

ከተከናወኑ ተግባራት መካከል የይዞታ መረጃዎች በአግባቡ መደራጀታቸው፤ ከዚህ ቀደም ገቢ ይሰበሰብባቸው የነበሩ የገቢ ኮዶችን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መሰብሰብ በመቻሉ እንዲሁም የክትትልና ድጋፍ ስርአቱን በማጠናከር ውዝፍ እዳዎችን በዘመቻ ማስከፈሉ ለተመዘገበው የገቢ እድገት እንደምክንያት ተቀምጠዋል።

በተጨማሪም ለረጅም ጊዜያት ማሻሻያ ሳይደረግባቸው የቆዩ የነባር ይዞታዎች የኪራይ ተመን፣ የጋራ መኖርያ ቤቶች የዋጋ ተመን እንዲሁም ወቅታዊ የገበያ ዋጋን መሠረት ያደረገ የግምት ስርአት መዘርጋቱ ለገቢው መጨመር ከይነተኛ አስተዋእጾ አበርክቷል።

በቀሪ በጀት አመቱ ወራት የገቢ እቅዱን ለማሳካት እና ዘርፉ የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ ለመሰብሰብ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተጠቅሷል።

ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም

በድሬ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎቶችን ያግኙ። ቢሮው በማእከሉ ይሰጣቸው የነበሩ አገልግሎቶችን በእጥፍ በማሳደግ በመሶብ የአንድ ...
20/05/2026

በድሬ መሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎቶችን ያግኙ።

ቢሮው በማእከሉ ይሰጣቸው የነበሩ አገልግሎቶችን በእጥፍ በማሳደግ በመሶብ የአንድ ማእከል አገልግሎት ይጠብቅዎታል።

ግዜዎት ይቆጥቡ
ህይወትዎን ያቅሉ!

ቢሮው ተደራሽ አገልግሎትን ለተገልጋዩ ለማድረስ እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጸ።የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የመሬትና ካዳሰተር መሪ ስራ አሰፈፃሚ አቶ ብዙ...
19/05/2026

ቢሮው ተደራሽ አገልግሎትን ለተገልጋዩ ለማድረስ እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተገለጸ።

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የመሬትና ካዳሰተር መሪ ስራ አሰፈፃሚ አቶ ብዙአለም አድማሱ በቢሮው የካዳስተር ስራዎች አፈጻጸምና በመሶብ የአንድ ማእከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት የዘርፉን አገልግሎት አሰጣጥ ተመልክተዋል።

የድሬደዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ሳጅድ አልዪ እንደገለጹት ቢሮው አገልግሎት አሰጣጡን ፈጣንና ቀልጣፋ እንዲሆን ለማስቻል በርካታ አገልግሎቶችን በድሬ መሶብ አንድ ማእከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ማስገባቱን ገልጸው አስፈላጊ ድጋፍና ክትትል ቢሮው በቅርበት እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

አክለውም አገልግሎቱ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ለማስቻል ተገልጋዩ ካለበት ቦታ በመሆን በራሱ አገልግሎት እንዲያገኝ ለማስቻል እየተከናወነ የሚገኘው የሲስተም ማሻሻል ስራ የሙከራ ትግበራ ለማከናወን ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የድሬደዋ ከተማ መሬት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ኢንቲሳር አብዱረህማን በበኩላቸው ከጊዜው ጋር የዘመነ አገልግሎትን በመስጠት በአንድ ማዕከል በርካታ ጉዳዮችን ጨርሶ በመውጣት የተገልጋይን እርካታ ማሳደግ ያስቻለ መሆኑን ገልጸዋል።

በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የመሬትና ካዳሰተር መሪ ስራ አሰፈፃሚ አቶ ብዙአለም አድማሱ በምልከታው መሠል የቴክኖሎጂ እና የአንድ ማእከል አገልግሎቶች ብልሹ አሰራሮች የሚያስቀሩ በመሆኑ ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም

በድሬደዋ ዲጂታል የአድራሻ ስርአት ለመተግበር የመስክ መረጃ መሰብሰብ ስራ ተጀመረ።የድሬደዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የከተማ መሬት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ የዲጂታል አድራሻ ስ...
18/05/2026

በድሬደዋ ዲጂታል የአድራሻ ስርአት ለመተግበር የመስክ መረጃ መሰብሰብ ስራ ተጀመረ።

የድሬደዋ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የከተማ መሬት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ የዲጂታል አድራሻ ስርአት ተግባራዊ ለማድረግ እንዲያስችል የመስክ መረጃ የማሰባሰብ ስራ በዛሬው እለት አስጀምሯል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ኢንቲሳር አብዱረህማን የዲጂታል አድራሻ ስርአት ድሬደዋን ዘመናዊ ከተማ ለማድረግ ለተጀመረው የዲጂታል ጉዞ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም የዲጂታል አድራሻ ስርአት ተግባራዊ ለማድረግ እንዲረዳ የመስክ መረጃ የማሰባሰብ ስራ መጀመሩን ገልጸው በመስክ መረጃውን ለሚሰበስቡ ባለሙያዎች የአስተዳደሩ ነዋሪዎች እና ተቋሟት አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

በኤጀንሲው የካዳስተር ቅየሳ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ብንያም ግርማ በበኩላቸው የመስክ መረጃውን በአጭር ግዜ በማሰባሰብና በማጠናቀቅ በአጭር ግዜ ዲጂታል የአድራሻ ስርአቱን ተግባራዊ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ.ም

Address

Dire Dawa

Telephone

+251912713204

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ/Dire Dawa Land Development and Management Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ/Dire Dawa Land Development and Management Bureau:

Share