Dire Dawa Youth & Sport Commission DDYSC ድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Dire Dawa
  • Dire Dawa Youth & Sport Commission DDYSC ድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን

Dire Dawa Youth & Sport Commission DDYSC ድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን News

20/04/2026
DYSC መረጃ | በድሬዳዋ አስተዳደር 2ኛው የአትሌቲክስ የስፖርት ክለብ ተመሰረተበድሬዳዋ አሰተዳደር ዛሬ የተመሠረተው የአትሌቲክስ ቡድን ኩራ ገላን የሚባል ሲሆን ከዚህ ቀደም አፍረን ቀሎ ክ...
18/04/2026

DYSC መረጃ | በድሬዳዋ አስተዳደር 2ኛው የአትሌቲክስ የስፖርት ክለብ ተመሰረተ

በድሬዳዋ አሰተዳደር ዛሬ የተመሠረተው የአትሌቲክስ ቡድን ኩራ ገላን የሚባል ሲሆን ከዚህ ቀደም አፍረን ቀሎ ክለብ በይፋ መመስረቱን ተከትሎ እንደ አሰተዳደር በይፋ የተመሰረተ 2ኛው የአትሌቲክስ ክለብ ይሆናል።

የድሬዳዋ አስተዳደር የወጣቶችና ስፖርት የስፖርት ማህበራት ኩራ ገላን የአትሌቲክስ ቡድን ፈቃድ ሰጥቶታል።

በመድረኩ ፈሩ ቲያንሺ ውሹ የስፖርት ክለብ ትርኢት በማሳየት የፕሮግራሙ ድምቀት ሆኗል።

ኩራ ገላን የአትሌቲክስ ስፖርት መቀመጫውን ድሬዳዋ በማድረግ የተለያዩ ክልሎችን በመያዝ ክለብ 35 አትሌቶችን ያቀፈ ሲሆን 13ቱ ሴቶች ሲሆኑ ቀሪዎቹ ወንዶች ናቸው።

የክለቡ ኩራ ገላን የአትሌቲክስ የስፖርት መስራቹ አቶ ጣልያን ጣሂር ይባላሉ ሲል Diretv ዘገባ ያመለክታል ።

ሚያዝያ 10 ፥ 2018 ዓ.ም |

ምስል:- Diretv

I ወስኮ ኮሙኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት l

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም አትሌቲክስ “የአንድ ቀን የሩጫ ውድድር” ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም እያስተናገደች ነው።EAF
18/04/2026

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም አትሌቲክስ “የአንድ ቀን የሩጫ ውድድር” ዛሬ በአዲስ አበባ ስታዲየም እያስተናገደች ነው።

EAF

የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ አትሌቲክስ የሴቶች የ10ሺህ ሜትር ውድድር ተጀምሯል::EAF
18/04/2026

የአዲስ አበባ ግራንድ ፕሪ አትሌቲክስ የሴቶች የ10ሺህ ሜትር ውድድር ተጀምሯል::

EAF

ዜና | ወጣቶችን በሁለንተናዊ ዘርፍ  ተጠቃሚ የሚያደርግ የሰላም እና ደህንነት ብሄራዊ የድርጊት መርሃ ግብር ዝግጅት ላይ የሚመክር ውይይት ተካሄደበድሬደዋ አስተዳደር የወጣቶች ሰላም እና ደህ...
16/04/2026

ዜና | ወጣቶችን በሁለንተናዊ ዘርፍ ተጠቃሚ የሚያደርግ የሰላም እና ደህንነት ብሄራዊ የድርጊት መርሃ ግብር ዝግጅት ላይ የሚመክር ውይይት ተካሄደ

በድሬደዋ አስተዳደር የወጣቶች ሰላም እና ደህንነት ብሄራዊ የድርጊት መርሃ ግብር ዝግጅት ሂደት ላይ ከከተማ እና ከገጠር ከወጣት አደረጃጀቶች ከተውጣጡ የወጣቶች ተወካዮች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ።

በምክክር መድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ካሊድ መሀመድ ተገኝተው እንደገለጽት የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ከድሬዳዋ ወጣቶች ስፖርት ኮሚሽን እንዲሁም life and peace ከተባለ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር የወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በወጣቶች ሰላም እና ደህንነት ብሄራዊ የድርጊት መርሃ ግብር ሂደት ላይ ወጣቶች በቀጥታ ተሳታፊ በማድረግ ለሀገረመንግስት ግንባታው የበኩሉን አስተዎጾ እንዲያበረክት ጭምር መሆኑንም አንስተዋል።

የሰላም የድርጊት መርሃ ግብሩ ወጣቶችን በስፋት በማሳተፍ በሰላም ግንባታ፣ የስብዕና ግንባታ እንዲሁም በግጭት አፈታት ዙሪያ የሚያበረከቱትን ሚና ለማሳደግ ያስችላል ብለዋል።

በመድረኩም አምስት አምዶች ላይ ያተኮረ የብድን ውይይት ተካሂዷል።

ምንጭ፦ DGC

DYSC l ሚያዚያ 8/2018

I ወስኮ ኮሙኒኬሽንና ህዝብ ግንኙነት l

 #ዘመናዊ የስፖርት ማስፋፊያ ስራዎች በድሬ በለውጡ ዓመታት በድሬዳዋ አስተዳደር  የስፖርት እድገት ማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል። ታዲያ በአስተዳደሩ የዘመናዊ ስፖርት ማስ...
16/04/2026

#ዘመናዊ የስፖርት ማስፋፊያ ስራዎች በድሬ

በለውጡ ዓመታት በድሬዳዋ አስተዳደር የስፖርት እድገት ማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል። ታዲያ በአስተዳደሩ የዘመናዊ ስፖርት ማስፋፊያ ልማት ስራዎች ምን እንደሚመስሉ በዚህ ፅሁፋችን በወፍ በረር ልንቃኝ ወደናል። መልካም ንባብ!

ስፖርት ከአዕምሮ፣ ጤና እና አካል ግንባታ በተጨማሪ ማኅበራዊ ትስስርን ለማጎልበት ትልቅ ጠቀሜታ አለው።
የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ደግሞ ተተኪ ስፖርተኞችን በብዛትና በጥራት ከማፍራት ባሻገር የዜጎችን ማኅበራዊ ትስስር በማጎልበት ለዘላቂ ሰላምና ልማት ፋይዳቸው የጎላ ነው፡፡

የድሬዳዋ አስተዳደር ይህን በመገንዘብ በሁሉም አካባቢዎች በርካታ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በመገንባት ዘመናዊ የስፖርት ማስፋፊያ ስራዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል።

👉የድሬዳዋ አለም አቀፍ ስታዲየም

የድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ በ2008 ዓ.ም ወደ ስራ የተገባ ሲሆን ከ520 ሚልዮን ብር በላይ ወጭ በ2016 ዓ.ም ግንባታው ተጠናቋል፡፡ ስታድየሙ በአራት ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን 25 ሺህ በላይ መቀመጫ፣ 16 በሮች፣ ስምንት የመሮጫ መም፣ አራት የመልበሻ ክፍሎች፣ አራት የዳኞች ክፍል፣ የVIP ማረፊያዎች፣ የVIP ካፍቴሪያ፣ የVIP ጨዋታ መከታተያ ክፍሎች፣ የጂምናዝም ክፍል፣ የሚዲያ ኮንፍረንስ ክፍሎች፣ 68 የንግድ ክፍሎችን በውስጡ የያዘ ሲሆን የደህንነት ካሜራዎች የተገጠመለትና በየጊዜው ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ እየታደሰ አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም ነው።

👉የድሬዳዋ ወጣቶች እና ስፖርት አካዳሚ

በድሬዳዋ አስተዳደር እየተገነቡ ካሉ የስፖርት መሰረተ ልማቶች አንደኛው የወጣቶች አካዳሚ ነው። የድሬዳዋ ወጣቶች እና ስፖርት አካዳሚ በ9 ሄክታር መሬት ላይ ከ 370 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት በአስተዳደሩ እየተከነባ የሚገኝ ነው።

አካዳሚው ዘመናዊ አዳራሽ ፣ 8 የስፖርት አይነቶችን ውድድር ማካሄድ የሚችል ሁለገብ ሜዳ ፣ ዘመኑን የዋጀ የመዋኛ ገንዳ ፣ ሰው ሰራሽ ሳር የተነጠፈለት የእግር ኳስ ሜዳን ጨምሮ ለአካዳሚ የሚያስፈልጉ መሰረታዊ ስራዎች የተሰሩለት አካዳሚ ነው ።በአሁኑ ሰዓት የአካዳሚው ስራዎች የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ የሚገኙ ሲሆን አካዳሚ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት ሲገባ በ8 የስፖርት አይነቶች ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማሰልጠን የታቀደ ሲሆን የስፖርት አይነቶቹ ብዛት በየጊዜው እየጨመረ የሚሄድ ይሆናል።

ይህ ፕሮጀክት ለወደፊት ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራት እና የከተማውን ስፖርት ለማሻሻል ትልቅ ሚና የሚጫወት ይሆናል።

👉 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች

የድሬዳዋ አስተዳደር ለስፖርቱ ልማት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን በአካባቢው የመገንባት ስራዎችን እያከናወነ ሲገኝ ይህም
ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት አንፃር የራሱን በጎ አስተዋጽኦ እያበረከተ ከመሆኑ በላይ ሀገራዊ ውጤት እንዲመዘገብ አስተዳደሩ በስፋት እየሰራ መሆኑን ማሳያ ነው።

ስፖርትን ሀገራችን ለያዘችው የብልፅግና ጉዞ መፋጠን አንዱ መሣሪያ ለማድረግ የተጀመረው ይሄው ስፖርታዊ ፕሮጀክት፣ ባለፉት ዓመታት በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ ከ 83 በላይ በከተማ እና በገጠር ወረዳዎች ከባለሀብቱ ጋር በመተባበር ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች ተሰርተው ለአገልግሎት እንዲበቁ ማድረግ ተችሏል።

በሌላ በኩል በድሬዳዋ አስተዳደር በየአካባቢው የሚገኙ 65 ጥርጊያ ሜዳዎችን ምቹና ጽዱ በማድረግ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ህብረተሰቡ በሚሰራበት ፣ በሚማርበት እና በሚኖርበት አካባቢዎች ጤናማ ዜጋን ለመፈጠር እንዲሁም ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር የስፖርት መሠረተ ልማት ስራዎች በስፋት ተሰርተዋል።

በአጠቃላይ እነዚህ በአስተዳደሩና በግል አልሚዎች በሚሊዩን ብር ወጪ የተደረገባቸው ዘመናዊ የስፖርት መሠረተ ልማቶች ታዳጊዎች ገና ከትምህርት ቤት ጀምሮ ለስፖርት ቅርብ ሆነው እንዲያድጉ ከማድረጋቸው ባለፈ፣ ትውልዱ በአካልና በአእምሮ የበለጸገ እንዲሆን በማድረግ ረገድ ሚናቸው የጎላ ነው።

አሁን እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትም የመጪውን ትውልድ ተስፋና የድሬዳዋን የስፖርት ዕጣ ፋንታ የሚወስኑ ለመሆናቸው ማረጋገጫ የሚሰጡ ናቸው።

የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ!!

 #ድሬና ኳስስለ ድሬዳዋ የእግር ኳስ ታሪክ አጭር ቅኝት ድሬዳዋ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ውድድሮችም ጥሩ ተሰጥኦ ያላቸውን በርካታ የእግር ኳስ ተጫዋቾችን በማበርከት ትታወቃለች።  በ...
13/04/2026

#ድሬና ኳስ

ስለ ድሬዳዋ የእግር ኳስ ታሪክ አጭር ቅኝት

ድሬዳዋ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ውድድሮችም ጥሩ ተሰጥኦ ያላቸውን በርካታ የእግር ኳስ ተጫዋቾችን በማበርከት ትታወቃለች። በአፍሪካ እግር ኳስ ውድድር ታሪክ የኢትዮጵያን ተደጋጋሚ ተሳትፎ ስንመለከት፣ ከድሬዳዋ የወጡ አስደናቂ ተጫዋቾችን ስም በግንባር ቀደምትነት ማግኘት አይቀሬ ነው።

በቀድሞው ጊዜ ከ11 የብሔራዊ ቡድን ተሰላፊዎች ከ6 በላይ የሚሆኑት ከድሬዳዋ የነበሩ ሲሆን፣ እንደ አዳሙ አለሙ፣ ግርማ ዘለቀ፣ ሙቅቢል ጅብሪል፣ ተካበ ዘውዴ፣ መሐመድ ኡስማን(ሚግ)፣ አሰግድ ተስፋዬ፣ በከሬ አደም፣ መሐመድ ቢን ሸሪፍ፣ ዳኛቸው ደምሴ፣ ጌታቸው ወልዴ ፣ አባይነህ ጌታሁን ጌታቸው ገላሼ ፤ ፍሰሃ በጋሻው፣ አግላን ዚያድ፣ ኤልያስ ሙሜ ፣ አድላቸው ፍቅሩ ፣ አሸናፊ ግርማ፣ ዩርዳኖስ አባይ ፣ ሲሞን አባይ ፣ ሳምሶን ሚካኤል ፣ ኢብራሒም ጃሚ ወ.ዘ.ተ ሌሎችን ታዋቂና ስመጥር የእግር ኳስ ሊቆችንና ኮከቦችን ስፍር ቁጥር የለሽ የታላላቅ ክለቦች ማልያ ሰማቸውን በአራቱም ማዕዘን ያሰጠሩ ተጫዋቾች መካከል ይጠቀሳሉ። ታዲያ በአሁኑ ወቅትም ከለውጡ ማግስት ጀምሮ አስተዳደሩ ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰቶ እየሰራ ሲሆን በዚህም የድሬዳዋ እግር ኳስ የቀደመ ገናና ታሪክም እየተመለሰ ይገኛል።

👉 ክለቦቿ

የቀድሞው የጥጥ ፋብሪካ ክለብ፣ የአሁኑ ድሬዳዋ ጨርቃ ጨርቅ ክለብ በድሬዳዋ ከተማ የተመሠረተ ስመ ገናና በኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለብ ከቀዳሚዎቹ አንዱ ሲሆን፤ ኢትዮጵያን ወክሎ በአፍሪካ ሻምፒዮና የተጫወተ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ክለብም ጭምር ነው። በ1960ዎቹ መገባደጃ ላይ፣ በዚህ ክለብ ውስጥ የነበሩት አብዛኞቹ ተጫዋቾች ከኤርትራ የተወሰዱ ሲሆን፣ ይህም ለድሬዳዋ የእግር ኳስ ፕሮፌሽናሊዝምን በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና ነበረው።

በ1980 ዓ.ም. ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካ ሻምፒዮና ስታሸንፍ፣ እንደ ተካበ ዘውዴ (ግብ ጠባቂ) እና መሐመድ ቢን ሸሪፍ ያሉ የቀድሞው የጥጥ ፋብሪካ ክለብ ተጫዋቾች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማልያ ለብሰው ተጫውተዋል። በካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ የ1964 ውድድር ላይ የጥጥ ፋብሪካ ክለብ የግማሽ ፍጻሜ ደረጃ ላይ በመድረስ ምርጥ አፈፃፀምንም አሳይቷል ።

ኢትዮ ሲሚንት ስፖርት ክለብ በድሬዳዋ ከተማ ሌላኛው አንጋፋ ክለብ ሲሆን፣ በ1964 የአፍሪካ ሻምፒዮና ላይ እንደ ሊቻኖ ቫሳሎ፣ ኤታሎ ቫሳሎ፣ ጌታቸው ወልዴ እና ግርማ ዘለቀ ባሉ ምርጥ ተሰጥኦ ባላቸው ተጫዋቾቹ አማካኝነት ኢትዮጵያን አስጠርተዋል ። እነዚህ ተጫዋቾች የሚመሩት ቡድን በ1964 ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ የአፍሪካ ሻምፒዮናም ሆነዋል።

👉ስለ ድሬዳዋ ስታዲየም አጭር ዳሰሳ

ታሪክ እንደሚያመለክተው፣ እ.ኤ.አ.በ1967 የድሬዳዋ ስታዲየም መሠረት ድንጋይ እንደ ተቀመጠ ይነገራል ፤ ታዲያ ስቴዲየሙ በየጊዜው የተለያዩ እድሳት እና ማሻሻያዎችን ተደርገውለታል።

ስታዲየሙ በዋነኝነት ለእግር ኳስ ጨዋታዎች የሚያገለግል ሲሆን ሌሎችንም ብዙ አገልግሎቶች ይሰጣል፣ በስታዲየሙ ዙሪያ፣ ገቢ ከሚያመነጩ ሥራዎች በተጨማሪ፣ የስታዲየሙ መስፋፋት ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድሎችን ፈጥሯል።
በአጠቃላይ በአሁኑ ሰዓት የድሬዳዋ አለም አቀፍ ስታዲየም የካፍ (CAF) መስፈርትን አሟልቶ አለም አቀፍ ጨዋታዎችን እያስተናገደ ሲገኝ ይህም፤ በድሬዳዋ ለስፖርቱ ዘርፍ በተለይም ለእግር ኳሱ እድገት ከፍተኛ ትኩረት ተሰቶ እየተሰራ መሆኑ ያሳያል። በተለያዩ ወቅት አገር አቀፍ ጨዋታዎችን በማስተናገድ በሀገሪቱ ከሚገኙ ዘመናዊ ስታዲዩሞች ተመራጭ አድርጉታል። ታዲያ ለዚህ ድል ስፖርት ወዳዱ የአስተዳደሩ ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ከፍተኛ አስተዋፆ ያደረጉ ሲሆን ዘርፉን በቅርበት እየደገፉም ይገኛሉ።

ከጥቂት ቀናት በፊት ለ 2027ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የመልስ ጨዋታ የድሬዳዋ አለም አቀፍ ስታዲየም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን እና የሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ ብሔራዊ ቡድንን ጨዋታን ያስተናገደ ሲሆን ጨዋታውም በኢትዮጵያ 1 ለ 0 አሸናፊነት በድል ተጠናቋል።

ታዲያ በጨዋታው ወቅት ከፍተኛ ዝናብ የጣለ ቢሆንም የድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ሜዳ በሚገርም ሁኔታ ምንም ጭቃም ሆነ ውሃ ሳይታይበት ካለምንም እንከን በጥራት ጨዋታውን አከናውኖ አጠናቋል።

የድሬዳዋ ስታዲየም በዚህ ልክ ደረጃውን ከፍ አድርጎና በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ መሰረት ለመሰራቱ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፤ ጥረታቸውም ፍሬ አፍርቷል።

ታዲያ ጨዋታው ቀደም ሲል በዝግ ስታዲየም እንዲካሄድ ተወስኖ የነበረ ሲሆን ደጋፊዎች በተገኙበት እንዲካሄድ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ፈቃድ ሰቷል።

የካፍ የደህንነት ኦፊሰር በድሬዳዋ ስታዲየም ተገኝተው ባደረጉት በአካል ምልከታና ግምገማ መሠረት፣ 10,000 ተመልካቾች በስታዲየሙ ተገኝተው ጨዋታውን እንዲከታተሉ በመወሰኑ በርካታ ቁጥር ያላቸው የድሬዳዋ ነዋሪዎች ጨዋታውን በመከታተል ዋልያዎቹን አበረታተዋል።

👉ስፖርት ወዳዱ የድሬ ህዝብ

ኢትዮጵያ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን መሥራች አገር ናት። እንዲሁም ደግሞ በ1962 የአፍሪካ ዋንጫን በማንሳት ታላቅ ታሪካዊ ስኬት አላት። እንደ ይድነቃቸው ተሰማ ያሉ አንጋፋ የስፖርት አመራሮች በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድረዋል።
ታዲያ ድሬና ስፖርት ተነጣጥለው የማይታዩ መሆናቸው ቀደምት ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን የድሬዳዋ ማህበረሰብ ለእግር ኳስ ያለው ፍቅር በአፍሪካ ደረጃ በጣም ጎልቶ የሚታይ ነው። በዚህም ታዲያ የድሬዳዋ ክለቦቿ ከአገር አቀፍ እስከ አለም አቀፍ የደረሰ አበረታች ውጤቶች ባለቤት ናቸው። ማህበረሰቡም ለኳሱ ጥልቅ ፍቅር አለው።

ለዚህ ጥልቅ ፍቅር በርካታ ምክንያቶች አሉ። ስመጥር ታላላቅ ተጫዋቾች ከድሬዳዋ አልፈው በኢትዮጵያውያ የኳስ ታሪክ ላይ አሻራቸውን አኑረዋል። የድሬዳዋ እግር ኳስ ደጋፊዎች መካከል ያለው ፉክክር ፍፁም ሰላማዊና ስፖርታዊ ጨዋነት የሚታይበት ነው። በዚህም ነው ማህበረሰቡ ለኳሱ ያለው ፍቅር የሚገለፀው፤ እነሆ "ስፖርት ለሰላም፣ ለፍቅር፣ ለአብሮነት" በድሬዳዋ መገለጫ ሆኖ ይቀጥላል ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን

እንኳን አደረሳችሁ!!የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን  አደረሳችሁ  መልዕክት አስተላለፉበ...
11/04/2026

እንኳን አደረሳችሁ!!
የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

በመልዕክታቸውም ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሠላም፣ በአንድነትና በፍቅር አደረሳችሁ ብለዋል፡፡

ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች በዓልን ደስተኛ ሆነው እንዲያሳልፉ ካለን ላይ በማካፈልና እርስ በእርስ በመረዳዳት እንዲሁም በመተሳሰብና በፍቅር በዓሉን ማሳለፍ እንደሚገባ ክቡር ከንቲባ በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል።

በመጨረሻም በዓሉ የሠላም፣ የደስታ፣ የፍቅር እንዲሆን እምኛለሁ በማለት ክቡር ከንቲባው የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

መልካም የትንሳኤ በዓል !!

የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፤ ሚያዚያ 3/2018 ዓ.ም

እንኳን አደረሳችሁ!!የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ  አቶ ሀርቢ ቡህ የትንሳኤ በአልን አስመልከቶ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ በዓ...
11/04/2026

እንኳን አደረሳችሁ!!
የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ የትንሳኤ በአልን አስመልከቶ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የአንድነት እንዲሆን የተመኙት ክቡር ም/ከንቲባው ፤ ያለንን በማካፈል፣ ጎረቤትን በማገዝ እና በመጠየቅ እንዲሁም የተቸገሩትን በመርዳት በአሉን በጋራ ማሳለፍ እንደሚገባ በመልዕክታቸው ገልፀዋል።

በዓሉ የፍቅር ፣ የአብሮነት ፣ የመተሳሰብ እና የመቻቻል እሴቶች ይበልጥ የሚጠናከሩበት ሊሆን እንደሚገባ ክቡር ም/ ከንቲባው ጠቁመው፤ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የፍቅር፣ የሰላም፣ የደስታ፣ የብልፅግና እና የመተሳሰብ በአል ይሆን ዘንድ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

መልካም የትንሳኤ በዓል!!

የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክት ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ ፤

ሚያዚያ 3/2018 ዓ.ም

Address

Dire Dawa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dire Dawa Youth & Sport Commission DDYSC ድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Dire Dawa Youth & Sport Commission DDYSC ድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን:

Share