የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት/Gidole town administration mayor office

  • Home
  • Ethiopia
  • Dilla
  • የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት/Gidole town administration mayor office

የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት/Gidole town administration mayor office "የበለጸገች ጊዶሌን የመገንባት ራዕይ ሰንቀን እንተጋለን!! - We strive to build a prosperous Gidole"

04/01/2026

# የመጨረሻ ማስታወቂያ #
!!አስቸኳይ ማስታወቂያ!!

ለጊዶሌ ነባር የከተማ ቦታ ጣሪያና ግድግዳ ግብር ከፋዮች ÷
ከተማ ሊዝ ቦታ ተጠቃሚዎችና ግብር ከፋዮች እንዲሁም ማስፋፊያ አከባቢ መሬት ያላቸው በሙሉ:-

የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ነባር የጣርያና ግድግዳ ግብር የ2018ዓ. ም ግብር ያልከፈላችሁ ÷
ከዚህ ቀደም በተለያዬ ዙር የሊዝ ቦታ በጨረታ ተወዳድራችሁ በማሸነፍ የሊዝ ቦታ ውል የገባችሁና ተደጋጋሚ ጥሪ የቀረበላችሁ የ2018 ዓመታዊ ጨምሮ ውዝፍ የግብር ክፍያ ግዴታቸሁን ያልተወጣችሁ መኖራችሁ ይታወቃል።

በተመሳሳይ ከዚህ ቀደም በከተማው ማስፋፊያ አከባቢዎች ሳይፈቀድ የተያዙ ቦታዎችና ግንባታዎችን ስርዓት ለማስያዝ፣ ለመቆጣጠርና ለመከላከል በተወሰነው ውሳኔ መሠረት ቦታ ወስዳችሁ እስከ አሁን ድረስ ቅጣትና የሊዝ ቅድመ ክፍያ ያልፈፀማችሁ እንዲሁም የሊዝ ቅድመ ክፍያ ፈፅማችሁ
የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ያልወሰዳችሁ ከሰኞ ታህሳስ 27/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 30/2018 ዓ.ም ብቻ የማዘጋጃ ቤታዊ ክፍያችሁን እንድትፈፅሙ ለመጨረሻ ጊዜ ለማሳወቅ ይወዳል።

ሆኖም በተጠቀሰው ጊዜ አመታዊና ውዝፍ የሊዝ ቦታ ክፍያን ያለፈፀሙ እና ክፍያ ፈፅመው ካርታ ያልወሰዱ አካላት አስተዳደሩ በተሰጠው ስልጣንና ህግና ደንብ በሚፈቀድለት መሠረት ይዞታውን ወደ መንግሥት የመሬት ባንክ ተመላሽ እንደሚደረግ በጥብቅ ያሳስባል።

የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤት

 #‎ዜና ሹመት‎‎የቀድሞ የጊዶሌ ከተማ ከንቲባ ኢ/ር ወልደመድኅን ካጫኖ  የጋርዱላ ዞን ከተማና መሠረተ-ልማት መምሪያ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።‎‎በዛሬው የምክር ቤት ውሎ የጋርዱላ ዞን ዋና አ...
01/12/2025

#‎ዜና ሹመት

‎የቀድሞ የጊዶሌ ከተማ ከንቲባ ኢ/ር ወልደመድኅን ካጫኖ የጋርዱላ ዞን ከተማና መሠረተ-ልማት መምሪያ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

‎በዛሬው የምክር ቤት ውሎ የጋርዱላ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ ግንኙነት ኪታሞ የቀድሞ ከንቲባ ኢ/ር ወልደመድኅን ካጫኖ ካላቸው እምቅ አቅምና ልምድ አንጻር እያደገ የመጣውን የከተመነት ምጣኔ በመምራት በጋርዱላ ዞን ሌሎች ከተሞችን ወደ ተሻለ ደረጃ ያደርሳሉ። የከተማና መሠረተ-ልማት ሥራዎችን ባላቸው ከፍተኛ ልምድ ይመራሉ በማለት ወደ ዞን በዕድገት የከተማና መሠረተ-ልማት መምሪያ ኃላፊ በመሆን እንዳደጉ ገልጸው የአዲሱን ከንቲባ ሹመት አቅርበዋል።

‎የጊዶሌ ከተማ ህዝብ ምክር ቤትም ኢ/ር ወልደመድኅን ካጫኖ በወጣትነታቸው ትልቅ ሸክም በመሸከም ውጤታማ ሥራ በመሥራታቸው በተለይም አከባቢው ከነበረበት የጸጥታ ሁኔታ ወጥቶ ወደ ልማት እንዲሸጋገር፤ ህዝባዊ አንድነት እንዲፈጠር፤ በከተማው ከፍተኛ የልማት መነቃቃት እንዲፈጠር፤ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ሥራዎችን በመምራት ላሳዩት የላቀ ትጋት አመስግኗቸው መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው የምክር ቤት አባላት ተመኝተውላቸዋል።

‎ኢ/ር ወልደመድኅን ካጫኖም በቀጣይ ከተማውን በሚችሉት አቅም እንደሚደግፉ ቃል ገብተው በቆይታቸው ከህዝብ ምክር ቤቱ፣ ከከተማው ህዝብ፣ ከሐይማኖት አባቶችና ከሀገር ሽማግሌዎች ለተደረገላቸው አበረታች ድጋፍ አመስግነዋል።

‎የጊዶሌ ከተማ መንግስት ኮምዩኒኬሽን አገልግሎትም ለቀድሞ ከንቲባችን መልካም የሥራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ተመኝተናል።

 #‎ዜና ሹመት‎የተከበሩ አቶ አሸናፊ ታዬ የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ሆነው ተሹመዋል::
01/12/2025

#‎ዜና ሹመት

‎የተከበሩ አቶ አሸናፊ ታዬ የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ሆነው ተሹመዋል::

18/11/2025
‎ከጊዶሌ ከተማ የማህበረሰብ ተወካዮችና የታችኛው መዋቅር አመራሮች ጋር በከተማው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙርያ ምክክር ተካሄደ።‎‎ከጊዶሌ ከተማ የማህበረሰብ ተወካዮችና የታችኛው...
14/11/2025

‎ከጊዶሌ ከተማ የማህበረሰብ ተወካዮችና የታችኛው መዋቅር አመራሮች ጋር በከተማው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙርያ ምክክር ተካሄደ።

‎ከጊዶሌ ከተማ የማህበረሰብ ተወካዮችና የታችኛው መዋቅር አመራሮች ጋር በከተማው የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙርያ ምክክር ተካሂዷል።

‎ምክክሩ በተለይም የጊዶሌ ከተማ የህንጻ ከፍታ ወሰንና የሴት ባክ፤ የታችኛው መዋቅር አደረጃጀት፤ የከተማ ልማት አካል የሆኑት የአስፓልት ኮሪደርና የመብራት መሠረተ-ልማቶችን ለማሳለጥ ያሰበ የህብረተሰብ ተሳትፎ ሥራዎችን በሚመለከት ነው።

‎መድረኩን የመሩት ከንቲባ ወልደመድህን ካጫኖ የአንድ ከተማ ዕድገት እና ልማት በመንግሥት ብቻ የሚፈጠር ሳይሆን፤ ይልቁንም የህዝብ የነቃ ተሳትፎ ዋና መሠረቱ ነው። የህዝብ ተሳትፎ የከተማዊ ትስስርን፣ የኢኮኖሚን፣ የአካባቢን እና የማህበራዊን ዕድገት የሚያጎላበት ዋና መሠረት ነው በማለት ገልጸዋል።

‎በከተማ ዕድገት እና የብልጽግና ጉዞ ላይ የህዝብ ተሳትፎ ካልተካተተ የተሟላ እድገት መፍጠር አይቻልም። የህዝብ ተሳትፎ በከተማ ልማት ውስጥ በጣም አስፈላጊ አካል ሲሆን፣ የህዝብ አስተያየት፣ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እና በውሳኔ ሂደት ውስጥ መካተት ከተማዊ ዕቅድን እንዲሳካ በእጅጉ ያግዛልም ብለዋል።

‎በመድረኩ የተሳተፉ አስተያዬት ሰጭዎችም በከተማው የተጀመሩ ልማቶችን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት ህዝቡን ለማሳተፍም ለመሳተፍም ያላሰለሰ ጥረት እንደሚያደርጉ ገልጸው እንደ አከባቢ በቁጭት ተነስቶ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

ፋይዳ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ የ"ፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያ ምንድን ነው? "ፋይዳ" የኢትዮጵያ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ሲሆን፣ አንድን ግለሰብ በልዩ ሁኔታ ለመለየት የሚያገለግል ...
27/10/2025

ፋይዳ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ

የ"ፋይዳ" ዲጂታል መታወቂያ ምንድን ነው?

"ፋይዳ" የኢትዮጵያ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ሲሆን፣ አንድን ግለሰብ በልዩ ሁኔታ ለመለየት የሚያገለግል ዘመናዊና አስተማማኝ የማንነት ማረጋገጫ ዘዴ ነው።
"ፋይዳ" ምን ምን ነገሮችን ያካትታል?

ፋይዳ የአንድን ዜጋ አስፈላጊ የሆኑ የማንነት መረጃዎችን በዲጂታል መልክ ያጠቃልላል።
ከእነዚህም መካከል፦

_ ሙሉ ስም፣ የትውልድ ዘመን፣ ፆታ፣ የዜግነት ሁኔታ
_ የፊት ገጽታ ምስል
_ የጣት አሻራ እና ሌሎች ባዮሜትሪክ መረጃዎች
_ ማንነትዎን በዲጂታል መንገድ የሚያረጋግጥ 12 አሃዝ ያለው ቁጥር።
_የመታወቂያ ቁጥር: የምዝገባ ሂደቱ ሲጠናቀቅ ልዩ የ"ፋይዳ" ቁጥርዎ በሞባይል ስልክዎ አጭር የጽሑፍ መልዕክት ይላክልዎታል። ይህ ቁጥር የመታወቂያ ካርዱን ያህል ዋጋ አለው።
_ የመታወቂያ ካርድ: ዲጂታል ቁጥሩ በቂ ቢሆንም፣ ከፈለጉ አካላዊ የመታወቂያ ካርዱን ማግኘት ይችላሉ።

🙏 የ"ፋይዳ" መታወቂያ አስፈላጊነትና ፋይዳው ምንድን ነው?

1. ለግለሰቡ ያለው ጥቅም

_ ባንክ አካውንት ለመክፈት፣ የጤና፣ የትምህርትና የማኅበራዊ ድጋፍ አገልግሎቶችን በፍጥነትና በቀላሉ ለማግኘት ያስችላል።
_ ባዮሜትሪክ በመሆኑ ማንነትዎ እንዳይሰረቅ ወይም እንዳይታወክ ይከላከላል። መታወቂያው ቢጠፋም ማንነትዎ የተጠበቀ ነው።
_ የብድር፣ የኢንሹራንስና ሌሎች የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማግኘት እንደ ዋና መስፈርት ያገለግላል። በተለይ ለሴቶች፣ ለስደተኞች እና ለአካል ጉዳተኞች የኢኮኖሚ ተሳትፎን ያሳድጋል

2. ለሀገር ያለው ፋይዳ (ጥቅም):

_ የመንግሥት አገልግሎቶች በፍትሐዊነት እና ግልጽነት ለሚገባቸው ዜጎች ብቻ እንዲደርሱ ያግዛል።
_ የማንነት ማጭበርበርን፣ ሕገወጥ ዝውውርን እና በሀሰተኛ ሰነድ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ለመቆጣጠር ያስችላል።
_ ትክክለኛ የሥነ ሕዝብ መረጃ መሠረት በመሆን ለብሔራዊ ልማት እቅዶችና በጀት ምደባ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደርጋል።
_ የሀገሪቱን የዲጂታል ሽግግር በማፋጠን፣ የንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችን ያቀላል።

🙏የ"ፋይዳ" መታወቂያን እንዴት ማውጣት ይቻላል?

1. የመመዝገቢያ መስፈርቶች፡
_ አብዛኛውን ጊዜ በቅድሚያ የሚፈለገው ዋናው የማንነት ማረጋገጫ ሰነድ እንደ ልደት ሰርተፍኬት፣ የመንጃ ፍቃድ፣ የድሮ መታወቂያ፣ የጋብቻ ሰርተፍኬት፣ ወዘተ ያሉ ማስረጃዎች ይሆናሉ፤

2. የምዝገባ ሂደት

_ በኢትዮ ቴሌኮም ፣ በተመረጡ የባንክ ቅርንጫፎች፣ በፖስታ ቤትና በምንኖርበት አካባቢ በተመቻቹ ሌሎች የመመዝገቢያ ማእከላት በአካል በመቅረብ መመዝገብ ይቻላል፡፡
_ ሁላችንም የዚህ ዘመናዊና መሠረታዊ የሆነውን የዲጂታል መታወቂያችንን እንድናገኝ ዛሬውኑ እንመዝገብ!

ፋይዳ፡ ለበለጸገች ኢትዮጵያና ለተሻለ ግላዊ አገልግሎት!

ጥቅምት 16/2018 ዓ.ምየጋርዱላ ዞን መድና በሆነችው በጊዶሌ ከተማ  ከ18  ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ G+2 ህንፃ ተመረቀበጊዶሌ ከተማ  ከ18  ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ...
26/10/2025

ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም

የጋርዱላ ዞን መድና በሆነችው በጊዶሌ ከተማ ከ18 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ G+2 ህንፃ ተመረቀ

በጊዶሌ ከተማ ከ18 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ G+2 የዘነበ ከበደ መታሰቢያ ህንፃ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

ህንፃው ለከተማዋ አዲስ ውበትን ከማጎናጠፉም በላይ ሌሎች በከተማው ኢንቨስት ማድረግ ለሚፈልጉ ባለሀብቶች ትልቅ ኢኮኖሚያዊ መነቃቃትን የፈጠረ ነውም ተብሏል።

ንብረትነቱ የወጣት ዲያስፖራ ሲሳይ ዘነበ የሆነው የህንፃ ምረቃ ስነ -ስርዓቱ ላይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ግንኙነት ኪታሞ፣ የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ ቦጋሌ ቦቴ፣ የጊዶሌ ከተማ ከንቲባ ኢ/ር ወልደመድህን ካጫኖ፣ በዞኑ የዲራሼ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ፍትራር ታዬ እና በዞኑ የሁሉም መዋቅር ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው ህንፃውን በመመረቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።

በምረቃ መርኃ-ግብሩ የዞኑ ዋና አስተዳዳር አቶ ግንኙነት ኪታሞ እንደተናገሩት የጋርዱላ ዞን በመሠረታዊነት ተፈጥሮ የቸራት የበርካታ ሀብቶች መገኛ እና ለኢንቨስትመንት ዘርፉ እጅግ ምቹ እንደሆነች ገልጸዋል።

አያይዘውም ወጣት ዲያስፓራ ሲሳይ ዘነበ በትውልድ ከተማው ለሌሎች የነጋዴው ማህበረሰብ አርአያ በመሆን ላበረከተው የተሻለ ተግባር በማመስገን በተጨማሪም በአከባቢው ኢንቨስት ማድረግ እንዲችል መንግስት አስፈላጊውን ሁሉ ምቹ ሁኔታዎችን እንደሚፈጥርለትም ተናግረዋል።

የጊዶሌ ከተማ ከንቲባ ኢ/ር ወልደመድህን ካጫኖ በበኩላቸው ለከተማው ሁለንተናዊ ዕድገት ሁሉም ከእርስ በእርስ መተቻቸትና መነቋቆር ወጥቶ የሚሰሩ እጆችን ማበረታታትና መደገፍ እንዳለበት አመላክተዋል።

ጊዶሌ ከተማ የበርካታ ተፅዕኖ ፈጣሪ ባለሀብቶች መነሻ ናት ያሉት ከንቲባው ባለራዕው ዲያስፓራ ወጣት ሲሳይ ለሌሎች ምሳሌ በመሆን በኢኮናሚው ዘርፍ በከተማው ላይ ላበረከተው ትልቅ አስተዋጽኦ ከልብ አመስግነዋል።

የዘነበ ከበደ መታሰቢያ በሚል የተሰየመው G+2 የሆነው ህንፃው ከ18 ሚሊየን ብር በላይ የሆነ ወጪ መፍጀቱን ባለራዕይ ዲያስፖራ ወጣቱ ጠቅሷል።

ህንፃው በአሁኑ ጊዜ በጊዜያዊነት ለሁለ - ገብ የገበያ ማዕከልነት እንደሚያገለግልም ወጣቱ በገለፃው አሳውቋል።

ወጣቱ ከዚህ በተጨማር በቀጣይ በዞኑ በሚገኙ ከተሞች ላይ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ በሰፊው ኢንቨስት የማድረግ ራዕይዎችን እንደሰነቀም አውስቷል።

በምረቃ መርሃ - ግብሩ ላይ ከዞኑ ከፍተኛ ባለስልጣናት በተጨማሪ የወጣት ዲያስፖራው ወገን ዘመዶች፣ ታላላቅ የአከባቢው የሀገር ሽማግሌዎች እና ከንግዱ ማህበረሰብ የተወጣጡ ነጋዴዎች ተገኝተው ወጣቱን አበረታተዋል።

ዘገባው የ Gardula Zone Government Communication Affairs Department ነው።

ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለምን ልመዝገብ?ፋይዳ ከህጻናት ጀምሮ እስከ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፣ ለአርሶ አደር ፣ ለሠራተኛ ፣ ለጡረተኛ ፣ እንዲሁም በሁሉም እድሜ ክልል ለሚገኙ ማንኛውም ሀገሪቱ...
25/10/2025

ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለምን ልመዝገብ?

ፋይዳ ከህጻናት ጀምሮ እስከ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፣ ለአርሶ አደር ፣ ለሠራተኛ ፣ ለጡረተኛ ፣ እንዲሁም በሁሉም እድሜ ክልል ለሚገኙ ማንኛውም ሀገሪቱ ውስጥ ለሚኖሩ ህጋዊ ነዋሪዎች፦
- የፋይናንስ አገልግሎቶች
- የተለያዩ መንግስት አገልግሎቶች
- የሰነድ ምዝገባ እና ማረጋገጥ አገልግሎት
- ከትምህርት ጋር ለተያያዙ አገልግሎቶች
- የትራንስፖርት እና መጓጓዣ አገልግሎቶች
- እንዲሁም የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶችን በተቀላጠፈ መልኩ ለማግኘት ያስችላል። የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጠቀሜታ በዝርዝር ለመረዳት ድረገጻችንን id.gov.et/benefits ይጎብኙ።

እርስዎም በዚህ ቅዳሜ እና እሁድ በሁሉም የምዝገባ ጣቢያዎች (id.gov.et/locations) በመሔድ ይመዝገቡ ፤ በፋይዳ ይገልገሉ።

እንኳን ለ 118ኛው ዓመት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ምሥረታ በዓል አደረሣችሁ ።
25/10/2025

እንኳን ለ 118ኛው ዓመት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ምሥረታ በዓል አደረሣችሁ ።

የዲራሼ ብሔረሰብ ባህላዊ ሙዝቃ (ፊላ)  በዩኔስኮ በሰው ልጆች ወካይ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰሩ ያሉት ስራዎች  ተገመገመ።ጥቅምት 2018ዓ.ምበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በቀድሞው ባህልና ቱሪ...
25/10/2025

የዲራሼ ብሔረሰብ ባህላዊ ሙዝቃ (ፊላ) በዩኔስኮ በሰው ልጆች ወካይ ቅርስነት ለማስመዝገብ እየተሰሩ ያሉት ስራዎች ተገመገመ።

ጥቅምት 2018ዓ.ም

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በቀድሞው ባህልና ቱሪዝም ቢሮ፣ ከአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ፣ ከጋርዱላ ዞን ባህልና ቱሪዝም ዩኒትና ዞኑ አስተዳደር እንዲሁም የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን በጋራ በውል ስምምነት የሚሰሩት የፊላ ባህላዊ ሙዝቃ ጥናት ፕሮጀክት እስካሁን የተሰሩ ተግባራትና በቀጣይ በትኩረት መሠራት ባለባቸው ጉዳዮች ዙሪያ አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የባህልና ስፖርት ቢሮ እና የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ ጋር ውይይት ተካሂዷል ።

በውይይቱ ላይ የተገኙት የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ የፊላ ፕሮጀክት አስተባባሪ ዶ/ር እንዳልካቸው ኃይሉ፣ አቶ ጋሻው ካጫኖ እና አቶ ታፈሰ ካንኮ የተገኙ ሲሆን ከጋርዱላ ዞን አቶ ገዛኸኝ ገለቦ :አቶ ተማሪ ተስፋዬ በተጨማሪም የክልሉ የባህል ዘርፍ ኃላፊ እና የቱሪዝም ዘርፍ ኃላፊዎች እንዲሁም የቢሮ ከፍተኛ ባለሙያዎች በተገኙበት አጠቃላይ የሥራው አከል በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጎ በቀጣይ በትኩረት ለሚሰሩ ጉዳዮች ዙሪያ ዕቅድና የጋራ ስምምነት ተደርጓል ።

ፊላ ባህላዊ ሙዝቃ ፕሮጀክት በተመለከተ በቀጣይ በቅርብ ቀን በጋርዱላ ዞን ለሚዘጋጀው ስምፖዝዬም ዙሪያ ለሚሰሩ ዝግጅቶች የሥራ ክፍፍል ተደርጎ ፣ ኮሚቴ ተዋቅሯል ። በአጠቃላይ ሥራውን የሚመሩ ባለድርሻ አካላት በትኩረት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው ከስምምነት ተደርሷል ።

20/10/2025

Address

Dilla

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጊዶሌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት/Gidole town administration mayor office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share