Gedeo Zone Women and Social Affairs Directive የጌዴኦ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ

  • Home
  • Ethiopia
  • Dilla
  • Gedeo Zone Women and Social Affairs Directive የጌዴኦ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ

Gedeo Zone Women and Social Affairs Directive የጌዴኦ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ Working for empowering the capacity &benefits of women and child safety&protection ,Social welfare&Inclusiveness .

‎ሴቶች- ወጣቶች- አካል-ጉዳተኞች- አረጋውያን የምርጫ ካርድዎን ወስዳችኋል? የመራጮች ምዝገባ ሊጠናቀቅ 2 ቀናት ብቻ ቀርተዋል።‎በመጪው ግንቦት በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ድምፅዎን...
20/04/2026

‎ሴቶች- ወጣቶች- አካል-ጉዳተኞች- አረጋውያን የምርጫ ካርድዎን ወስዳችኋል? የመራጮች ምዝገባ ሊጠናቀቅ 2 ቀናት ብቻ ቀርተዋል።

‎በመጪው ግንቦት በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ድምፅዎን ለመስጠት ተዘጋጅተዋል? የሀገርን ዕጣ ፈንታ በሚወስነው በዚህ ዴሞክራሲያዊ ሂደት ላይ የራስዎን አሻራ ለማሳረፍ የመጀመሪያው እርምጃ ለመራጭነት መመዝገብ ነው።

‎የመራጮች ምዝገባ ሚያዝያ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይጠናቀቃል። ይህ ማለት የምዝገባው ጊዜ ሊያበቃ 2 ቀናት ብቻ ቀርተውታል።

‎ሴቶች፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ እንዳያመልጥዎ! የሚበጅዎትን ለመምረጥ፣ በቀሩት 2 ቀናት ውስጥ ይመዝገቡ።

08/04/2026
በወረዳው የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማረጋገጥ እና የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥተው እየተሰራ እንዳለ ተገለፀ ( #ዲላ መጋቢት 26/2018 ዓ.ም) በጌዴኦ ዞን ገደብ...
04/04/2026

በወረዳው የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማረጋገጥ እና የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥተው እየተሰራ እንዳለ ተገለፀ

( #ዲላ መጋቢት 26/2018 ዓ.ም) በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እና ብሄራዊ የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ምዝገባ በሁሉም ቀበሌያት ለማጠናከር ትኩረት ተሰጥተው እየተሰራ እንዳለ ተገልጿል።

የገደብ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት በዛሬው ዕለት ከሀርሙፎ ቀበሌ ከተወጣጡ ሴቶች/እናቶች ጋር የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባና የውይይት ተካሂደዋል።

በውይይት መድረኩ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና ተሳትፎ ለማረጋገጥ በወረዳው ቀበሌ ደረጃ ትኩረት ተሰጥተው እየተሰራ እንዳለ የገደብ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ወ/ሮ አለማሽ ዘውዴ አስረድተዋል።

አክለውም ብሄራዊ የማንነት መገለጫ (ፋይዳ) ምዝገባ አሁን ከደረሰበት ከፍ ለማድረግና የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ ሁሉም እናቶች የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው አሳስቧል።

ሴቶች በማህበራዊ ፣ በኢኮኖሚያዊ እንድሁም በፖለቲካዊ ዘርፎች ላይ ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነትን ከፍ ለማድረግ ተቀናጅተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝቧል።

ከተረጅነት ወደ ምርታማነት የሚለውን እሳቤ በሁሉም እናቶች ላይ ለማስረፅ ሴት እናቶቻችን በሁሉም ልማት ዘርፎች በማበረታታት ውጤታማ ብልፅግና ማረጋገጥ የሚቻል እንደሆነም ወ/ሮ አለማሽ ተናግሯል።

በመጨረሻም መንግስት ለሴቶች ያመቻቸው ዕድል ከምንም ግዜ በላይ በመጠቀም በሁሉንም ዘርፎች በመሳተፍ ተሳትፎአቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው ጠቁሟል።

@የገደብ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት!

በተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ሳቢያ ለጎዳና ሕይወት ተጋላጭ ልጆች ቁጥር መጨመርን ለመግታት  ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ተቀናጅቶ ሊሰራ እንደሚገባ ተገለፀ‎‎( #ዲላ መጋቢት 25-2018 ዓ/ም) ...
03/04/2026

በተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ሳቢያ ለጎዳና ሕይወት ተጋላጭ ልጆች ቁጥር መጨመርን ለመግታት ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ተቀናጅቶ ሊሰራ እንደሚገባ ተገለፀ

‎( #ዲላ መጋቢት 25-2018 ዓ/ም) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን በተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ሳቢያ ለጎዳና ሕይወት ተጋላጭ ልጆች ቁጥር መጨመርን ለመግታት ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ተቀናጅቶ ሊሰራ እንደሚገባ የዞኑ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ጥሪ አቀረበ፡፡

‎ሲ አይ ኤስ ፒ የተሰኘ የጣሊያን ግብረ ሰናይ ድርጅት ፕሮቴክት በተሰኘ ፕሮጀክት በዲላ ከተማና ዲላ ዙሪያ ወረዳ ከጎዳና ላይ ያነሳቸውን 42 ልጆች ከቤተሰቦቻቸው ጋር የማገናኘት ስራ አከናውኗል።

‎ግብረ ሰናይ ድርጅቱ በሰራው ልጆችን ከወላጆቻቸው ጋር የማገናኘት ተግባር ደስታ እንደተሰማቸው ልጆችና ወላጆች ተናግረዋል፡፡

‎ በሰው ሰራሽና በተፈጥሯዊ ክስተት ለማህበራዊ ችግሮች የሚጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ቁጥር እየጨመረ መምጣት በሀገር ኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያሳድረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ እየሆነ መጥቷል።

‎ግብረ ሰናይ ድርጅቱ በሰራው ልጆችን ከወላጆቻቸው ጋር የማገናኘት ተግባር ደስታ እንደተሰማቸው የገለፁት ማርሸት ገመቹና ቸርነት አዳነ በጎዳና ላይ ቆይታቸው አስቸጋሪ ሕይወት ማሳለፋቸውን ተናግረዋል፡፡

‎በሲ አይ ኤስ ፒ ግብረ-ሰናይ ድርጅት የጌዴኦ ዞን አስተባባሪ አቶ ሐብታሙ ባጫ ድርጅቱ ወደ ስራ ከገባ ሰባት ወራት ማስቆጠሩን ጠቅሰው በጥናት ላይ ተመስርቶ በዲላ ከተማ ዲላ ዙሪያ ወረዳና ይርጋ ጨፌ ከተማ የሚገኙ አንድ መቶ ልጆች ከጎዳና አንስቶ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመቀላቀል በዘላቂነት የተሻለ ህይወት እንዲኖሩ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

‎ለማህበራዊ ችግር ተጋላጭ የሚሆኑ ልጆችን ከጎዳና ሕይወት መታደግ ለመንግስት ብቻ የሚተው ጉዳይ ባለመሆኑ ፕሮቴክት ፕሮጀችት 49 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በመመደብ ከጎዳና ተመላሽ ልጆችና ቤተሰቦቻቸውን ሕይወት ለመለወጥ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ነው አቶ ሐብታሙ ባጫ ያስረዱት።

‎ወላጆቻቸውን በፍቺ በኢኮኖሚ እጥረትና በሞት ማጣትና በተለያዩ ምክንያቶች ሳቢያ ልጆች ለፍልሰት ለጎዳና ተዳዳሪነትና ለሌሎች ለማህበራዊ ችግሮች ተጋላጭ የሚዳርጓቸው መንስዔዎች መሆናቸውን ነው የጌዴኦ ዞን ሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ፍሬነሽ አየለ የተናገሩት፡፡

‎ችግሩ ዘርፈ ብዙ በመሆኑ ከቤተሰብ ጀምሮ ለጎዳና ሕይወት ተጋላጭ ልጆች ቁጥር ለመቀነስ ከተለያዩ ግብረ ሰናዬ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ያሉት ወ/ሮ ፍሬነሽ አየለ ሲ አይ ኤስ ፒ ግብረ ሰናይ ድርጅት ፕሮቴክት ፕሮጀክቱ እያከናወነው ያለው ተግባር በሌሎች አጋር አካላት እንዲተገበር ጥሪ አቅርበዋል፡፡

‎በመርሐ ግብሩ ላይ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ከፍትህ ከፖሊስና ከተለያዩ መንግስታዊ ተቋማት ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ከሴቶችና ሕፃናት ደህንነት የሕፃናት አስተዳደግና መብትና አዎንታዊ ወላጅነት በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሰነድ ቀርቦ ከወላጆችና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ወይይት ተካሂዷል፡፡

‎@የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙንኬሽን አገልግሎት!

30/03/2026
21/07/2018 ዓ.ም የዲጂታል መታወቂያ/ፋይዳ/ ምዝገባ በሁሉም ወረዳና ከተማ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
30/03/2026

21/07/2018 ዓ.ም
የዲጂታል መታወቂያ/ፋይዳ/ ምዝገባ በሁሉም ወረዳና ከተማ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በፍስሀ ገነት ምርጫ ክልል ለክልል ምክርቤት የብልጽግና ፓርቲ እጩ ወ/ሮ ፍሬነሽ አየለ የመራጮች ምዝገባ ካርዳቸውን በሚኖሩበት አካባቢ በመገኘት ወሰዱ  ገደብ ከተማ፣ መጋቢት 17/2018 የመ...
26/03/2026

በፍስሀ ገነት ምርጫ ክልል ለክልል ምክርቤት የብልጽግና ፓርቲ እጩ ወ/ሮ ፍሬነሽ አየለ የመራጮች ምዝገባ ካርዳቸውን በሚኖሩበት አካባቢ በመገኘት ወሰዱ

ገደብ ከተማ፣ መጋቢት 17/2018 የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን።

የጌዴኦ ዞን የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ እና በፍስሀ ገነት ምርጫ ክልል የክልል ምክርቤት እጩ የብልጽግና ፓርቲ ተወካይ ወ/ሮ ፍሬነሽ አየለ የመራጭነት ካርዳቸውን በገደብ ከተማ ባሬዳ ቀበሌ ጨካታ/07 ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ወስደዋል ።

ክብርት ወ/ሮ ፍሬነሽ አየለ ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን በመጠቀም ኃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን እና እድሜያቸው ለመምረጥ የደረሳቸው ዜጎች ካርዳቸውን በመመዝገብ እንድወስዱ መልዕክታቸውን አክለዋል።

ዘገባው የገደብ ከተማ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ነው ።

ዲላ፣17/07/2018 ዓ.ም በወረዳና ከተማ ደረጃ ሴቶችና ህፃናት  የድጅታል መታወቂያ ምዝገባ /ፋይዳ/ ተሳትፎ በዚህ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል ።
26/03/2026

ዲላ፣17/07/2018 ዓ.ም በወረዳና ከተማ ደረጃ ሴቶችና ህፃናት የድጅታል መታወቂያ ምዝገባ /ፋይዳ/ ተሳትፎ በዚህ መልኩ እየተካሄደ ይገኛል ።

ዲላ፣16/07/2018 ዓ.ምየኮቾሬ ወረዳ ውሃና ኢነርጂ ጽ/ቤት የሴቶችን ጊዜና ጉልበት የሚቆጥቡ ተስማሚ ቴክኖሎጂዎችን (ምርጥ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃ ) ሴቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ ያለ ሥራ...
25/03/2026

ዲላ፣16/07/2018 ዓ.ም
የኮቾሬ ወረዳ ውሃና ኢነርጂ ጽ/ቤት የሴቶችን ጊዜና ጉልበት የሚቆጥቡ ተስማሚ ቴክኖሎጂዎችን (ምርጥ ማገዶ ቆጣቢ ምድጃ ) ሴቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ ያለ ሥራ የሚበረታታ ነወ።

‎በይርጋጨፌ ወረዳ ኢድዶ ከተማ በሴቶች ልማት ሕብረት  የተዘጋጀ የእንሴት ችግኝ አባላቶቹ ተጠቃሚ መሆናቸዉ ተገለፀ‎‎ይርጋጨፌ ወረዳ  #መጋቢት 16/2018 ዓ.ም‎‎በይርጋጨፌ ወረዳ ኢድዶ ከ...
25/03/2026

‎በይርጋጨፌ ወረዳ ኢድዶ ከተማ በሴቶች ልማት ሕብረት የተዘጋጀ የእንሴት ችግኝ አባላቶቹ ተጠቃሚ መሆናቸዉ ተገለፀ

‎ይርጋጨፌ ወረዳ #መጋቢት 16/2018 ዓ.ም

‎በይርጋጨፌ ወረዳ ኢድዶ ከተማ በሴቶች ልማት ሕብረት የተዘጋጀ የእንሴት ችግኝ አባላቶቹ ተጠቃሚ መሆናቸዉ ተገልጿል።

‎ልማት ሕብረቶቹ በቡድን በመደራጀት በተለያዬ ስራ መስክ በመሠማራት ዉጠታማነታቸዉን እያረጋገጡ ይገኛል።

‎በዘንድሮ በበልግ ወቅት የምተከለዉን የእንሴት ስሜ ችግኝ አዘጋጅተዉ ለተጠቃሚ ለቡዱኑ አባላቶች ማከፋፈል ችለዋል።

‎የእድዶ ከተማ ማዘጋጃ ዋና ስራ አስክያጅ አቶ ገዛሄኝ አሰፋ በበኩላቸዉ ሴቶች በልማት ሕብረት ተደራጅተዉ ዉጤታማ እንድሆኑ በቅርብ ክትትል ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸዉን ተናግሯል።

‎ወቅቱ የእንሴትና የቡና ችግኝ ተከላ እንድሁም የበልግ አዝማራ ወቅት መሆኑን ተገንዘብዉ የከተማ ነዋርዎች ሳይዘናጉ ባላቸዉ ጓሮ እንድተክሉ ኃላፊዉ ጥሪ አቀርቧል።

‎ የጋራ መግባባትን ለመፍጠር እንተጋለን❗
‎የይርጋጨፌ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
‎ በማድረግ ይቀላቀሉ #መረጃ ቶሎ እንድደርስዎ , Share Comment ወይም አስተያዬት ማስቀመጥዎን አይርሱ!




በዲላ ዙሪያ ወረዳ የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን "ማርች 8" በድምቀት ተከበረ‎‎መጋቢት 10 ቀን 2018 ዓ.ም | ዲላ ዙሪያ ወረዳ‎‎በዲላ ዙሪያ ወረዳ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት አ...
19/03/2026

በዲላ ዙሪያ ወረዳ የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን "ማርች 8" በድምቀት ተከበረ

‎መጋቢት 10 ቀን 2018 ዓ.ም | ዲላ ዙሪያ ወረዳ

‎በዲላ ዙሪያ ወረዳ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት፣ 115ኛው የዓለም አቀፍ እና 50ኛው የኢትዮጵያ የሴቶች ቀን (ማርች 8) "50 ዓመት የሴቶች ድምጽ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።

‎በበዓሉ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የዲላ ዙሪያ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊና ረዳት የመንግስት ተጠሪ ወይዘሮ መርኩሪ ወልደየስ፤ ሴቶች በሀገር ግንባታ፣ በኢኮኖሚ እድገትና በማህበራዊ ሰላም ግንባታ ላይ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። "ሴቶች ከቤተሰብ ጀምሮ እስከ ሀገር አቀፍ ደረጃ ልጆችን በመልካም ስነ-ምግባር አንጾ በማሳደግና ለሀገር የሚጠቅም ዜጋ በማፍራት ቁልፍ ተግባራትን እያከናወኑ ይገኛሉ" ብለዋል።

‎የወረዳው የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ መሰለች አሰፋ በበኩላቸው፣ ሴቶች በልማት፣ በፖለቲካና በኢኮኖሚ ዘርፎች የወረዳውንም ሆነ የሀገሪቱን ብልጽግና ለማረጋገጥ የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ መሆኑን ጠቁመዋል።

‎ኃላፊዋ አክለውም በወረዳው የሚገኙ ሴቶች በተለያዩ የሥራ ዘርፎች በተለይም በግብርና፣ በጓሮ አትክልትና በዶሮ እርባታ ተሰማርተው ውጤታማ እየሆኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። በተለይም በአከሾ ሀፈሮ፣ በሽገዶ እና በቡላ ቀበሌዎች የተመዘገቡ ምርጥ ተሞክሮዎች በዞንና በክልል ደረጃ እውቅና ማግኘታቸውን በመጥቀስ፣ የሴቶችን የቁጠባ ባህል ማሳደግና በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን እንዲሁም ያለ እድሜ ጋብቻን በመከላከል ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባ አሳስበዋል።

‎በዕለቱ በአቶ እንግዳ ፈይሳ የቀረበ የመወያያ ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ በስራቸው ከፍተኛ አፈጻጸም ላሳዩ ሴቶች የእውቅና ሰርቲፊኬት ተበርክቶላቸዋል።

‎በዓሉ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ በሚያሳዩ የተለያዩ ዝግጅቶች ተጠናቅቋል።

‎ዘገባው፡ የዲላ ዙሪያ ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ነው።

Address

Dilla

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gedeo Zone Women and Social Affairs Directive የጌዴኦ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gedeo Zone Women and Social Affairs Directive የጌዴኦ ዞን ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ:

Share