Bule Woreda Health Office

Bule Woreda Health Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Bule Woreda Health Office, Government Organization, Bule, Dilla.
(1)

በዕየለቱ የሟቾች ቁጥር አስደንጋጭ በሆነ ሁኔታ እየጨመረ ስለመጣ ከመቼውም ጊዜ በላይ እንጠንቀቅ።***************በኢትዮጵያ ያለው የኮቪድ-19 ስርጭት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ይህም...
10/10/2021

በዕየለቱ የሟቾች ቁጥር አስደንጋጭ በሆነ ሁኔታ እየጨመረ ስለመጣ ከመቼውም ጊዜ በላይ እንጠንቀቅ።
***************

በኢትዮጵያ ያለው የኮቪድ-19 ስርጭት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ይህም በበሽታው የሚያዙ ፤ በፅኑ የሚታመሙና ህይወታቸውን የሚያጡ ወገኖቻችን ቁጥር ከሌላው ጊዜ በተለየ ሁኔታ በከፍተኛ መጠን እየጨምረ ይገኛል።

በኢትዮጵያ አንድ በኮቪድ-19 ቫይረስ የተያዘ ግለሰብ ከተመዘገበበት ዕለት መጋቢት 4/2012 ጀምሮ 354‚033 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ ፤ 736 ሰዎች አሁን ላይ በፅኑ ህሙማን ክፍል ይገኛሉ። እንዲሁም 5,950 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

አሁንም የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሀገራችን ላይ ስጋት መሆኑን ቀጥሏል። ስለሆነም እየአንዳንዱ ግለሰብ በሀላፊነት ስሜት እራሱን ፣ ቤተሰቡን ማስክ በማድረግ፣ የእጅን ንጽህና በተደጋጋሚ በመጠበቅ ፣ በማንኛውም ቦታ አካላዊ ርቀትን በመጠበቅ እና የኮቪድ-19 ክትባት በመከተብ የወረርሽኙን ስርጭት ለመግታት እና ለመቆጣጠር የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ እናሳስባለን::

ስለ ሕብረተሰብ ጤና አደጋ የኮቪድ-19 ጨምሮ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት እንዲሁም ጥቆማ ለመስጠት 8335 ላይ ደውለው የጤና ባለሙያዎችን ማነጋገር ይችላሉ።
የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
#እንድናገለግልዎማስክዎንያድርጉ



https://t.me/EthPHI
https://www.facebook.com/EPHIEthiopia

EPHI one of the oldest and known public health institutes in Africa. It is open 24/7 for public health emergency management through Emergency Operation Center. For any information and help call 8335 or send us a message through [email protected]

04/10/2021

1K likes
Thank you dear followers!

02/10/2021
የኮቪድ 19 አይነቶች ፤ ምንነት እና ውጤት   የኮቪድ 19 አይነት (variant) ስንል ምን ማለታችን ነው? ኮቪድ 19 ወይም በህክምና መጠሪያው SARS-COV 2 በዋነኝነት የመተንፈሻ አካ...
28/09/2021

የኮቪድ 19 አይነቶች ፤ ምንነት እና ውጤት

የኮቪድ 19 አይነት (variant) ስንል ምን ማለታችን ነው?

ኮቪድ 19 ወይም በህክምና መጠሪያው SARS-COV 2 በዋነኝነት የመተንፈሻ አካላት ላይ እክል የሚያመጣ፣ በቀሪዎቹ የአካላዊ ስርዓቶቻችንም ላይ ችግር ሊያስከትል የሚችል ደቂቅ ህዋስ ሲሆን የሚመደበውም ቫይረስ ከሚባሉት የደቂቅ ተዋህሲያን ፈርጅ ነው።
እነዚህ በጥቅሉ ቫይረስ ተብለው የሚጠሩት ተዋህሲያን ባህሪ ውስጥ አንዱ እና ዋነኛው ከአካባቢያችው ጋር በሚኖራቸው መስተጋብር ሂደት ፈጣን የገጽታ ለውጥ ማስተናገዳቸው ነው። የኮቪድ 19ም ቫይረስ በዚህ የተፈጥሮ ህግ መሰረት ቫይረሱ ከተለየበት ዲሴምበር 2019 ጀምሮ በርካታ ለውጦችን አስተናግዷል። ባለሙያዎችም በዘረ መል ጥናት እንዚህን ለውጦች በመከታተል ተመሳሳይ ለውጥ ያላቸውን ቫይረሶች ወደ አንድ ግንድ እያመጡ ስም እየሰጡ ይገኛሉ። ይህንንም ጥናት እያካሄዱ ያሉ የተወሰኑ ተቋሞች ያሉ ሲሆን በስፋት የሚታወቀው ግን በዓለም ጤና ድርጅት የተዋቀረው ቡድን እና ቡድኑ የቫይረሱን ግንዶች የሚጠራባቸው ስያሜዎች ናቸው። እነዚህም አልፋ፣ ቤታ፣ ጋማ እንዲሁም ዴልታ የተባሉት የኮቪድ 19 አይነቶች ናቸው።

ታዲያ በዚህ አመት ውስጥ ቫይረሱ በብዙ አይነቶች ካለ/ከተፈጠረ፤ ለምን እነዚህ አራቶቹ ተለይተው ወጡ?

የሚከሰቱት አይነቶች በባህሪያቸው ከሰው ሰው የመተላለፍ አቅማቸው ከፍተኛ የሆነ፣ የሚያስከትሉት የህመም ሁኔታ ጫን ያለ ወይም ለየት ያለ ሆኖ ከተገኘ ‘አሳሳቢ አይነት’ / Variant of Concern ተብለው ይመደባሉ። ከላይ የተጠቀሱትም አይነቶች በእነዚህ መስፈርቶች ላይ ተንተርሶ አሳሳቢ የህመም እና ስርጭት ሁኔታ ላይ በመድረሳቸው ከፍተኛውን የአለም የጤና ድርጅት የአመዳደብ ደረጃ ይዘዋል። ከዚህ ዝቅ ስንል ‘ክትትል የሚያስፈልጋቸው አይነቶች’ / Variant of Interest ተብሎ የሚጠራው መደብ ሲገኝ እነዚህንም በባህሪያቸው የመተላለፍ አቅማቸው መጠነኛ መጨመር ካሳየ ነገር ግን የሚያመጡት ህመም ላይ መጨመርም ወይም መለየት ከሌለ ከዚህ ደርጃ ላይ እናስቀምጣቸውለን።

አልፋ/ Alpha - B.1.1.7

መጀመሪያ የተለየው: ዩናይትድ ኪንግደም
ስርጭት: ከሌሎች አይነቶች አንጻር በጣም ከፍተኛ በሆነ መጠን እና ፍጥነት ይሰራጫል
ከባድ ህመም እና ህልፈት: በአንጻራዊነት የበለጠ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ላይ ህመም እንዲሁም ህልፈት ያስከትላል
ክትባት: በአሁኑ ሰአት እየተሰጡ ያሉ ክትባቶች ይሄንን አይነት በሚገባ ይከላከላሉ፤ ከከባድ ህመም እና ህልፈትም ይጠብቃሉ።

ቤታ/ Beta - B.1.351

መጀመሪያ የተለየው: ደቡብ አፍሪካ
ስርጭት: በመጠኑ ከፍ ያለ አንጻራዊ የስርጭት መጠን ይኖረዋል
ከባድ ህመም እና ህልፈት: እስካሁን ባለው መረጃ በግልጽ የተለየ የጨመረ ከባድ ህመም እና ህልፈት አያስከትልም
ክትባት: በአሁኑ ሰአት እየተሰጡ ያሉ ክትባቶች ይሄንን አይነት በሚገባ ይከላከላሉ፤ ከከባድ ህመም እና ህልፈትም ይጠብቃሉ።


ጋማ/Gamma - P.1

መጀመሪያ የተለየው: ጃፓን/ ብራዚል
ስርጭት: በመጠኑ ከፍ ያለ አንጻራዊ የስርጭት መጠን ይኖረዋል
ከባድ ህመም እና ህልፈት: እስካሁን ባለው መረጃ በግልጽ የተለየ የጨመረ ከባድ ህመም እና ህልፈት አያስከትልም
ክትባት: በአሁኑ ሰአት እየተሰጡ ያሉ ክትባቶች ይሄንን አይነት በሚገባ ይከላከላሉ፤ ከከባድ ህመም እና ህልፈትም ይጠብቃሉ።

ዴልታ/ Delta - B.1.617.2

መጀመሪያ የተለየው: ህንድ
ስርጭት: ከሌሎች አይነቶች አንጻር በጣም ከፍተኛ በሆነ መጠን እና ፍጥነት ይሰራጫል
ከባድ ህመም እና ህልፈት: በአንጻራዊነት የበለጠ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ላይ ህመም እንዲሁም ህልፈት ያስከትላል
ክትባት: ከዴልታ አይነት አዲስ ከመሆን ጋር ተያይዞ በኮቪድ ክትባት እና በዚህ አይነት መካከል ያለው ቁርኝነት ሙሉ ለሙሉ ግልጽ አይደለም። ይህም ሆኖ እስካሁን እየወጡ ያሉ ጥናቶሽ የሚያመለክቱት የኮቪድ 19 ክትባት አሁንም ቢሆን ጠቃሚ እንደሆነ ነው

ዴልታ አይነት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ አገራት በስፋት እና በፍጥነት እየተሰራጨ የሚገኝ አይነት ነው። ይህ አይነት ከአሳሳቢነቱ እና ከአዲስነቱ አንጻር በርካታ ጥያቄዎችን ያስነሳል።ከእነዚህ ጥያቂዎች መካከልም የተወሰኑትን የሚከተሉት ናቸው።

1. ክትባቱን የወሰደ ግለሰብ የዴልታ አይነትን የመከላከል አቅሙ ምን ይመስላል?
እስካሁን ባሉን መረጃዎች ክትባቱን ያልወሰደ ሰው ክትባቱን ከወሰደ ሰው ጋር ሲነጻጸር በዴልታ አይነት የመጠቃት እድሉ በስምንት እጥፍ የጨመረ ሆኖ ተገኝቷል። በተመሳሳይ ክትባቱን ያልወሰደ ሰው ክትባቱን ከወሰደ ሰው ጋር ሲነጻጸር በዴልታ አይነት ታሞ ህኪም ቤት የመግባት እና የማለፍ እድሉ በሃያ አምስት እጥፍ የጨመረ ሆኖ ተገኝቷል።

2. ከዚህ በፊት በኮቪድ 19 ተጠቅቶ ያገገመ ሰው (ነገር ግን ያልተከተበ) ግለሰብ የዴልታ አይነትን የመከላከል አቅሙ ምን ይመስላል?
ባለፉት 12 ወራቶች ውስጥ በኮቪድ 19 ተይዞ ያገገመ ሰው ሌሎቹን የኮቪድ አይነቶች የመከላከል አቅሙ ከሞላ ጎደል ከተከተበ ሰው ጋር ተመሳሳይ እንደነበር ሲነገር ቆይቷል። ነገር ግን ይህ ሁኔታ ዴልታ አይነትን እንደማያካትት ጥናቶች እያመላከቱ ነው።

3. ተጨማሪ የኮቪድ 19 አይነቶች ይፈጠራሉ?
አዎ። አሁንም ቢሆን የአለም የጤና ድርጅት ‘ሚው’ እና ‘ላምዳ’ የተባሉ አይነቶችን እየተከታተለ ይገኛል። ‘ላምዳ’ በጁን ወር 2021 እንዲሁም ‘ሚው’ በኦገስት ወር መጨረሻ ‘ክትትል የሚያስገልጋቸው አይነቶች‘ የሚለውን የአለም ጤና ድርጅት ደረጃን ተቀላቅለዋል።

የስራና ጤና ነክ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

Telegram ፡ t.me/healthinovation

Facebook: https://www.facebook.com/andualemsew/

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሠላምና ጤና አደረሳችሁ። አደረሰን። በዓሉ ዝግጅት እና  በምናከብርበት  ወቅት  ፣ከዚያም በኋላ መሰባሰባችን የቫይረሱን ስርጭት ይበልጥ ስለሚያባብሱ መሰባሰቦችን በ...
26/09/2021

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሠላምና ጤና አደረሳችሁ። አደረሰን።

በዓሉ ዝግጅት እና በምናከብርበት ወቅት ፣ከዚያም በኋላ መሰባሰባችን የቫይረሱን ስርጭት ይበልጥ ስለሚያባብሱ መሰባሰቦችን በመቀነስ ልናከናውን ይገባናል።

የኮሮና ቫይረስ መከላከያ መንገዶችን ማለትም ማስክ በአግባቡ መጠቀም፣ ርቀትን መጠበቅ፣እጆቻችንን በውሀ እና በሳሙና/ሳኒታይዘር ማፅዳት፣ ሰዎች በሚበዙበት ቦታ ባለመሰባሰብ ፣በመከተብ ራሳችንንም ይሁን ሌሎችን ከኮሮና ቫይረስ በመጠበቅ ግዴታችንን እንወጣ፡፡
መልካም በዓል
የደ/ብ/ብ /ሕ/ክ/ መንግስት ጤና ቢሮ

31/07/2021


በኢትዮጵያ ሦስተኛው ዙር የኮቪድ-19 (3rd Wave) ወረርሽኝ እየጀመረ መሆኑን የሚያሳዩ ምልክቶች እየታዩ ነው‼️

የኮቪድ-19 ቫይረስ በኢትዮጵያ መከሰቱ ከታወቀ ጊዜ ጀምሮ እስከ (ሐምሌ 22/2013) ለ3,006,482 ግለሰቦች የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 279,629 ግለሰቦች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። 263,392 ግለሰቦች ከኮቪድ-19 ቫይረስ አገግመዋል። 4,381 ግለሰቦች በኮቪድ-19 ምክንያት ሕይወታቸውን አጥተዋል።

በተለያዩ የዓለም ሀገራት መረጃዎች እና ጥናቶች እንደሚያሳዩት ሦስተኛው ዙር (3rd Wave) የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከሰቱ ታውቋል። ለዚህም እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው የኮቪድ-19 ዴልታ ቫይረስ ነው። በሀገራችን የኮቪድ-19 የዴልታ ቫይረስ መኖሩ ባይረጋገጥም የሶስተኛ ዙር (3rd Wave) ወረርሽኝ መከሰቱን የሚያሳዩ ምልክቶች መታየት ጀምሯል‼️

እንደ ማሳያነት ከዛሬ ሶስት ሳምንት በፊት በኮቪድ-19 ቫይረስ የሚያዙ ግለሰቦች ቁጥር ዝቅተኛ ነበረ። በአማካኝ በአንድ ቀን 70 ግለሰቦች በኮቪድ-19 ቫይረስ ተይዘው ሪፖርት ይደረግ የነበረ ሲሆን ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መጥቶ (ሐምሌ 22/2013) 476 ግለሰቦች በኮቪድ-19 ቫይረስ የተያዙ ሲሆን ይህም ቁጥር ሁለተኛው ዙር (2nd wave) ካበቃበት ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ ቁጥር ሆኖ ተመዝግበዋል፡፡ ናሙና ከሚሰጡ 100 ግለሰቦች 1 እስከ 2 ግለሰቦች የመያዝ ምጣኔ የነበረ ሲሆን (ሐምሌ 22/2013) ከሶስት እጥፍ በላይ ጨምሮ ወደ 7 ግለሰቦች የመያዝ ምጣኔ ከፍ ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል በፅኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ የሚገኙ ህሙማን ከሶስት ሳምንት በፊት በአማካኝ 124 ግለሰቦች የነበሩ ሲሆን (ሐምሌ 22/2013) በእጥፍ በመጨመር ወደ 228 ከፍ ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና የጤና ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶች ፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመተባበር እንዲሁም ማህበረሰቡን በማሳተፍ የኮቪድ-19 ቫይረስ በሀገራችን ከመከሰቱ በፊት የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎችን በመስራትና በማስተባበር ከተከሰተም በኋላ የተለያዩ የመከላከል እና የመቆጣጠር ስራዎችን እየሰሩ ይገኛሉ፡፡

በመሆኑም ሁለተኛው ዙር (2nd wave) ካበቃ በኋላ በተወሰነ መልኩ በማህበረሰቡ የታዩ መዘናጋቶች እንዲሁም የኮቪድ-19 መከላከያ መንገዶች በአግባቡ ባለመተግበራቸው ሶስተኛ ዙር (3rd wave) ሊከሰት የሚችልበት ምልክቶች እየታዩ ስለሆነ እያንዳንዱ ግለሰብ፤ ቤተሰብ፤ ሁሉም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፤ የሐይማኖት ተቋማት፣ ሲቪክ ማህበራት፤ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፤ የጤና ባለሙያዎች፤ መምህራንና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመከላከል ማስክ ማድረግ፣የእጅን ንፅህና በአግባቡ መጠበቅ እና ርቀትን በመጠበቅ በተጨማሪም የኮቪድ-19 ክትባት በመከተብ የኮቪድ-19 መከላከከልና መቆጣጠር ተግባር ላይ በባለቤትነት እና በኃላፊነት ስሜት አጠናክረው እንዲሠሩ እናሳስባለን፡፡

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

15/04/2013 ዓ.ም=============በማችንግ ፈንድ የተገዛዉ አምቡላንስ በትላንትናው ዕለት ለወረዳችን ገቢ ተደርጎ ዛሬ  አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። አምቡላንሱ የተገዛው ከ350 ሺህ ...
24/12/2020

15/04/2013 ዓ.ም
=============
በማችንግ ፈንድ የተገዛዉ አምቡላንስ በትላንትናው ዕለት ለወረዳችን ገቢ ተደርጎ ዛሬ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። አምቡላንሱ የተገዛው ከ350 ሺህ ብር በላይ ከወረዳችን ተከፍሎ ሲሆን ዞኑም ለወረዳችን ለማችንግ ፈንድ የሚፈለገውን መነሻ ሂሳብ ተጨማሪ 350 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጎልናል። በዚህ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ አሰተዋጽኦ ላደረጋችሁ ለወረዳችን አስተዳደር፣ ፋይናንስ ጽ/ቤት፣ለዞኑ ጤና መምሪያ እና ለዞኑ አስተዳደር ላቅ ያለ ምስጋና ይድረሳችሁ እንላለን።

19/11/2020
ድል ለኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊታችን!!!
17/11/2020

ድል ለኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊታችን!!!

ሀገር ዓቀፍ የፖሊዮ ዘመቻ ከመስከረም 27-30/2013 ዓ.ም ይካሄዳል።
03/10/2020

ሀገር ዓቀፍ የፖሊዮ ዘመቻ ከመስከረም 27-30/2013 ዓ.ም ይካሄዳል።

17/09/2020

በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/ መንግስት ተጨማሪ 25 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል!

ዛሬ መስከረም 7/2013 ዓ.ም ባለፉት 24 ሰዓታት ዉስጥ በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/ በተደረገው 977 የላብራቶሪ ምርመራ 25 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ በአጠቃላይ በክልሉ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 2,211 ደርሷል፡፡

በዛሬው ዕለት በቫይረሱ ከተያዙት ሰዎች መካከል፡-

• ከወላይታ ዞን 14 (12 ከቦሎሶ ቦምቤ፣ 1 ከቦዲቲ እና 1 ከሆቢቻ)፣
• ከጌዴኦ ዞን 3 (3ቱም ከዲላ ከተማ)፣
• ከካፋ ዞን 3 (3ቱም ከሺሾንዴ)፣
• ከጉራጌ ዞን 2 (2ቱም ከቸሃ)፣
• ከጋሞ ዞን 1 (ከአርባምንጭ ከተማ)፣
• ከስልጤ ዞን 1 (ከሳንኩራ)፣
• ከባስኬቶ 1 ናቸው፡፡

በዛሬው ዕለት ካገገሙ 82 ሰዎች መካከል ከስልጤ 22፣ ከወላይታ 15፣ ከከምባታ ጠምባሮ 13፣ ከጋሞ 11፣ ከቤንች ሸኮ 10፣ ከሸካ 5፣ ከባስኬቶ 3፣ ከቡርጂ 1፣ ከኮንሶ 1 እና ከየም 1 ናቸው፡፡ በአጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1,656 ደርሷል፡፡

በደ/ብ/ብ/ህ/ክ/ መንግስት ጤና ቢሮ

17/09/2020

በኢትዮጵያ 689 ተጨማሪ ሰዎች ኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸው፤ 420 ሰዎች ደግሞ አገግመዋል
***************
ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 10 ሺህ 605 የላቦራቶሪ ምርመራ 689 ሰዎች ኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 66 ሺህ 913 ደርሷል።
በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 420 ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተከትሎ በአጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 27 ሺህ 85 ሆኗል።
ባለፉት 24 ሰዓታት በኮሮናቫይረስ የ15 ሰዎች ህይወት ማለፉ መረጋገጡን ተከትሎ በበሽታው የሞቱ ሰዎች ቁጥር 1 ሺህ 60 ደርሷል።
በአሁኑ ወቅት ቫይረሱ ካለባቸው 38 ሺህ 766 ሰዎች መካከል 300 ያህሉ በጽኑ ሕክምና ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
በአገሪቱ እስካዛሬ ድረስ በአጠቃላይ ለ1 ሚሊዮን 176 ሺህ 252 ሰዎች የኮሮናቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጓል።

Address

Bule
Dilla

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bule Woreda Health Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Bule Woreda Health Office:

Share