ዲላ ዙሪያ ወረዳ ገብዎች ባለሥልጣን ቅ/ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Dilla
  • ዲላ ዙሪያ ወረዳ ገብዎች ባለሥልጣን ቅ/ጽ/ቤት

ዲላ ዙሪያ ወረዳ ገብዎች ባለሥልጣን ቅ/ጽ/ቤት ገቢን መሰብሰብ ዋና አላማችን ሆኖ ለ ማህበረሰቡ የግንዛቤ ስ?
(2)

በግብር ከፋዩ ከንግድ ስራ ገቢ ግብር ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመሙላት የክህሎትና ስልጠና መስጠቱ ቀዳሚ ተግባር ነው :- አቶ አሸናፊ ሀልቻዬ(ዲላ ፣ታህሳስ 23/2017 ...
01/01/2025

በግብር ከፋዩ ከንግድ ስራ ገቢ ግብር ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመሙላት የክህሎትና ስልጠና መስጠቱ ቀዳሚ ተግባር ነው :- አቶ አሸናፊ ሀልቻዬ

(ዲላ ፣ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም )

በግብር ከፋዩ ከንግድ ስራ ገቢ ግብር ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ የግንዛቤ ክፍተቶችን ለመሙላት የክህሎትና ስልጠና መስጠቱ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን የዲላ ዙሪያ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ሀልቻዬ ተናግሯል ።

ኃላፊው ይህንን የገለጹት የጌዴኦ ዞን ገቢዎች መምሪያ ከዲላ ዙሪያ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር በወረዳ ለሚገኙ ለደረጃ ''ሀ'' እና ''ለ'' ግብር ከፋዮች በታክስ ሂሳብ መዝገብ አያያዝ ፤ በደረሰኝ አጠቃቀም እና በሪፖርቱ አቀራረብ ላይ የክህሎት ስልጠና በሰጠበት ወቅት ነው ።

ለግብር ከፋዮች ግንዛቤ በመፍጠር መንግስት ማግኘት ያለበትን ሀብት እንዲያገኝና ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ለማስቻል ለግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ነው ያስረዱት ።

መንግሥት ከዜጎች በሚሰበሰበው ግብር የልማት ክፍተቶችን ለመሙላት በሚያደርገው ጥረት ግብር ከፋዩ የሚጠበቅበትን ግብር የመክፈል ግዴታ እንዳለበት ጠቁሞ ለግብር ከፋዩ የተሻለ ግንዛቤ እንዲፈጠር በማድረግ ገቢን አሟጦ ለመሰብሰብና ግብር ከፋዩ በህግ የተፈቀደለትን ወጪዎች በመለየት የታክስ ስርዓትን በተከተለ መልኩ በመስራት የሚጠበቀውን ግብር ለመክፈል የሚያስችል ስልጠና መሆኑ አያይዘው ገልጸዋል ።

የክህሎት ስልጠና የሠጡት በጌዴኦ ዞን ገቢዎች መምሪያ የታክስ የትምህርት ስልጠና ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ወይንሸት በቀለ በበኩላቸው በወረዳ ለሚገኑ የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች ከታክስ ሂሳብ መዝገብ ፣ ደረሰኝ አጠቃቀም እና በሪፖርት አቀራረብ ጋር ተያይዞ በውስጡ ሊይዝ የሚገባውንና ከግብር ከፋዩ ህብረተሰብ መረጃን በተጀራጀ አግባብ በመያዝ ከመንግስት የሚጠበቅበትን ግብር ለመክፈል የሚያስችል ግንዛቤ መፍጠሪያ መሆኑን ገልፀዋል ።

በዞኑ በፈቃደኝነት እና በታማኝነት ግብርን የሚከፍሉ የንግዱን ማህበረሰብ መጠን ለማሳደግ መሰል ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች በየደረጃው በገቢ ጽህፈት ቤቶች ተጠናክረው የሚቀጥል መሆኑን መግለጻቸውን የዘገበው የጌዴኦ ዞን ገቢዎች መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ነው ።

06/07/2024
የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን በማዘመን ግዜ ቆጣቢ በሆነ መንገድ አመራሮች የባለቤትነት  ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለፀሰኔ 22/2016 ዓ/ም ዲላ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙኒከሽን ጉዳዮች ጽ/...
29/06/2024

የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን በማዘመን ግዜ ቆጣቢ በሆነ መንገድ አመራሮች የባለቤትነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለፀ

ሰኔ 22/2016 ዓ/ም ዲላ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙኒከሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

የገቢ አሰባሰብ ስርዓቱን በማዘመን ግዜ ቆጣቢ በሆነ መንገድ አመራሮች የባለቤትነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የዲላ ዙሪያ ወረዳ አስተደደር አቶ ታርኩ ታደሰ ተናግሯ፡፡

አክለው አቶ ታርኩ ታደሰ በመርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የገቢ አሰባሰብ ስርአቱን ለማሳደግ ሁሉም አመራር ላይ መግባባት በመፍጠር የባለቤትነት ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ገልፀዋል ።

የዲላ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ኃላፍ አቶ ንቅናቄ ባለሲ እንደ ፖርቲያችን በታቀዱ እቅድ መሠረት በወረደችን ብዙ የገቢ ምንጭ ያለበት ስሆን ኮማንድ ፖስት ተቋቅመው አስፈለግው ሁሉ በማድረግ እና ህገመጥነትን በመከላከል መስራት እንደምገባ አሳስበዋል፡፡

አቶ አሸናፍ ሀልቻዬ የዲላ ዙረያ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፍ በተያዘው በጀት ዓመት ወረዳው 153 ሚሊዮን 340 ሽህ ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ 68 ሚሊዮን 342 ሽህ ብር በላይ ማሰባሰቡን በመግለጽ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ስነጻጸር ጉድለት መኖሩን አመላክተዋል ።

አቶ አሸናፍ ገቢ ለልማት አማራጭ ብቻ ሳይሆን የኢኮኖሚ ማነቃቂያ እና የማህበረሰቡ የመሰረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ የምሰጥ በመሆኑ የምክክሩ ተሳታፊዎች የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ የበኩላቸውን እንዲወጡም አሳስቧል፡፡

የምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት አመራሮችና ባለድርሻ አካላት በበኩላቸው ዕቅዶችን ከግብ ለማድረስ በቀጣይ የተሻለ ውጤት ለማስመዘገቢ ከገቢ ሴክተሩ ጎን በመቆም በቀሪ ጊዜ አፈፃፀም ላይ ለዕቅዱ መሳካት የበኩላቸውን ለመወጣት የጋራ መግባባት ላይ መድረሳቸው ተውቋል።
ዲላ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት

ተርን ኦቨር ታክስተርን ኦቨር ታክስ በአገር ውስጥ በሚከናወን የዕቃ ወይም የአገልግሎት ሽያጭ ወቅት በየደረጃው የሚጣል የታክስ ዓይነት ነው፡፡ተርን ኦቨር ታክስን ሰብስቦ ገቢ የማድረግ ግዴታለ...
10/05/2024

ተርን ኦቨር ታክስ

ተርን ኦቨር ታክስ በአገር ውስጥ በሚከናወን የዕቃ ወይም የአገልግሎት ሽያጭ ወቅት በየደረጃው የሚጣል የታክስ ዓይነት ነው፡፡

ተርን ኦቨር ታክስን ሰብስቦ ገቢ የማድረግ ግዴታ

ለተጨማሪ እሴት ታክስ ያልተመዘገበ ወይም ዓመታዊ የንግድ አንቅስቃሴው ከብር 1 ሚሊየን በታች የሆነ ማንኛውም በንግድ ስራ ላይ የተሰማራ ሰው ወይም ድርጅት በአገር ውስጥ ከሚሸጣቸው ዕቃዎችና አገልግሎቶች ላይ ሰብስቦ ለሚመለከተው የታክስ መስሪያ ቤት/ሚኒስቴር ገቢ ያደርጋል፡፡

ዕቃዎች ወይም አገልግሎቶችን የሚሸጥ ማናቸውም ሰው ወይም ድርጅት በሽያጭ ላይ ሊከፈል የሚገባውን ታክስ ከገዥው ሰብስቦ ለሚስቴሩ ገቢ የማድረግ ግዴታ አለበት፡፡ ስለሆነም ሻጩ ለታክሱ የመጀመሪያ ተጠያቂ ይሆናል፡፡

የተርን ኦቨር ታክስ የስሌት መሠረት

ተርን ኦቨር ታክስ የሚሰላበት የዋጋ መሠረት የዕቃው ወይም የአገልግሎት ጠቅላላ የሽያጭ ገቢ ይሆናል፡፡

የሚከተሉት ከተርን ኦቨር ታክስ ክፍያ ነፃ ናቸው፡-

1. ቢያንስ ሁለት ዓመት ያገለገለ መኖሪያ ቤት ሽያጭና የመኖሪያ ቤት ኪራይ፤
2. የፋይናንሰ አገልግሎቶች፤
3. ለሳንቲሞችና ሜዲሊያዎች ጥናት አገልግሎት ከሚውሉት በስተቀር የአገር ውስጥና የውጪ አገር ገንዘቦችና የዋስትና ሰነዶች ማሰራጨት፤
4. በኃይማኖት ድርጅቶች የሚሰጡ የእምነት ወይም ከአምልኮ ጋር የሚገናኙ አገልግሎቶች፤
5. የሕክምና አገልግሎትና አግባብ ባለው የመንግስት መ/ቤት በሚወጣ መመሪያ መሠረት በሐኪም የሚታዘዙ መድኃኒቶች፤
6. በትምህርት ተቋማት የሚሰጡ የማስተማር አገልግሎቶች እንዲሁም ለሕፃናት ጥበቃ በመዋዕለ ሕፃናት የሚሰጡ አገልግሎቶች፤
7. የኤሌክትሪክ፣ የኪሮሲን የውሃ አቅርቦት፤
8. የትራንስፖርት አገልግሎት፤
9. ማናቸውንም የሥራ እንቅስቃሴ ለማከናወን ለሚሰጥ ፈቃድ ለመንግስት የሚፈፀም ክፍያ፤
10. 60% እና ከዚያ በላይ ሠራተኞቹ አካል ጉዳተኞችን ቀጥሮ የሚያሰራ ድርጅት የሚያቀርባቸው ዕቃዎችና አገልግሎቶች፤
11. መጽሐፍት፤
12. ሌሎች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የሆኑ ሁሉ ናቸው፡፡

በድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/MoREthiopiaOfficial/169
በፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ERCA.info
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/.../featured
በቲክቶክ፡- tiktok.com/
በቴሌቪዥን ፕሮግራሞቻችን ፡- ዋልታ ቴሌቪዥን ቅዳሜ አመሻሽ ከ 12፡30 ጀምሮ፣ ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኃላ፣ ኢቲዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣ በሬድዮ ፕሮግራሞቻችን፡- ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ. በወርሃዊ ጋዜጣችን፡- ገቢያችን ህልውናችን እንዲሁም በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡ - 8199 በመደወል መረጃዎችን በመጠየቅ ስለሚከታተሉን እናመሰግናለን።

በዲላ ዙሪያ ወረዳ ለሚገኙ ለደረጃ “ሀ”  ግብር ከፋዮች በታክስ ሒሳብ መዝገብ አያያዝ እና አስተዳደራዊ ቅጣቶች ዙሪያ የክሎት ስልጠና ተሰጠ ዲላ :ህዳር 27/2016 ዓ.ም በዲላ ዙሪያ ወረዳ...
07/12/2023

በዲላ ዙሪያ ወረዳ ለሚገኙ ለደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች በታክስ ሒሳብ መዝገብ አያያዝ እና አስተዳደራዊ ቅጣቶች ዙሪያ የክሎት ስልጠና ተሰጠ

ዲላ :ህዳር 27/2016 ዓ.ም በዲላ ዙሪያ ወረዳ ለሚገኙ በንግድ ሥራ ላይ ለተሰማሩ ለደረጃ “ሀ” ግብር ከፋዮች በታክስ ሒሳብ መዝገብ አያያዝ እና አስተዳደራዊ ቅጣቶች ዙሪያ የክሎት ስልጠና ተሰጥቷል ።

የስልጠናውን ሰነድ ያቀረቡት የዞኑ ገቢዎች መምሪያ የታክስ ትምህርትና ድጋፍ ባለሙያ ወ/ሮ ወይንሸት በቀለ ስሆኑ የስልጠናው ዓላማ በዋነኝነትም የዞኑ ገቢዎች መምሪያ በፈቃደኝነት ታክስ ግዴታውን የሚወጣ ማህበረሰብ ለመፍጠር ስልጠናው አስፈላጊ መሆኑን ገልጿል።

በስልጠና መድረክ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የዲላ ዙሪያ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ሀልቻዬ በበኩላቸው የክህሎት ስልጠናው ግብር ከፋዮች በፍቃደኝነት ግብራቸውን አሳውቀው ለመክፈል በታክስ ሂሳብ መዝገብ እና በተቀናሽ ወጪዎች ላይ የሚታይ ክፍተቶችን ለመሙላት ስልጠና አስፈላጊ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

በመድረኩ የወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ ሀልቻዬን ጨምሮ የተቋሙ ባለሙያዎች የዞኑ ገቢዎች መምሪያ የታክስ ትምህርት ኮሙኒኬሽን ቡድን መሪ አቶ አለማየሁ ህርቤ እንዲሁም የወረደው የደረጃ ''ሀ'' ግብር ከፋዮች ተሳታፊ ሆነዋል።

በስልጠናው ማጠቃለያ ከግብር ከፋዮች የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ስልጠናውን በሰጡ ባለሙያዎች ጨምሮ የዞኑ ገቢዎች መምሪያ የታክስ ትምህርት ኮሙኒኬሽን ቡድን መሪ አቶ አለማየሁ ህርቤ የዲላ ዙሪያ ወረዳ የንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ እና በወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ በአቶ አሸናፊ ሀልቻዬ በኩል ለቀረቡ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽ መሰጠታቸው የዘገበው የዞኑ ገቢዎች መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ነው ።

በቀን 19/02/2016 ዓ.ም በምጣኔ ጥ/የታ/ት/ትና የአገ ቅ/አ/ዳይሬክቶሬት በኩል በእርሻ ሥራ ገቢ ግብር ዙሪያ ከቀበሌ ለመጡ ሊቀ መናብርት እና ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ...
30/10/2023

በቀን 19/02/2016 ዓ.ም በምጣኔ ጥ/የታ/ት/ትና የአገ ቅ/አ/ዳይሬክቶሬት በኩል በእርሻ ሥራ ገቢ ግብር ዙሪያ ከቀበሌ ለመጡ ሊቀ መናብርት እና ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመወያየት ላይ ይገኛሉ:: በዉይይቱም የተለያዩ ሀሳቦች እየተነሱ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
የዲላ ዙሪያ ወረዳ ገቢዎች ባ/ቅ/ጽ/ቤት

በቀን 15/02/2016 ዓ,ም ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር ማለትም ከተማ ልማትና ኮ/ጽ/ቤት;የአንዲዳ እና የቱምትቻ መዘጋጃ ቤቶች እንዲሁም የወረዳዉ ገቢዎች ጽ/ቤት በጋራ በማዘጋጃ ቤ...
26/10/2023

በቀን 15/02/2016 ዓ,ም ከሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ጋር ማለትም ከተማ ልማትና ኮ/ጽ/ቤት;የአንዲዳ እና የቱምትቻ መዘጋጃ ቤቶች እንዲሁም የወረዳዉ ገቢዎች ጽ/ቤት በጋራ በማዘጋጃ ቤቶች ቀጣይ ስራዎችና በምጣኔ ተመኑ ተካተው መሰብሰብ ስገባቸዉ ባልተሰበሰቡ የገቢ ርዕሶች እንዲሁም መሻሻል በሚገባቸዉ የገቢ ኮዶች ዙሪያ በመወያየት የጋራ ግንዛቤ በመፍጠር በቀጣይ የህብረተሰቡን የመልማት ጥያቄ ለመመለስ የጋራ ጥረት እንደሚያስፈልግ መግባባት ላይ በመድረስ አጠናቀዋል::

በወረዳችን በ 2015 ዓ.ም(በ2015 በጀት ዓመት) ሊሰበሰብ ከታቀደው 65,351,798 ዉስጥ ለመሰብሰብ የተቻለዉ 77,241,140.53 ሲሆን ይህም በመቶኛ ሲታይ 118.2% ማሳካት ተችሏል...
21/09/2023

በወረዳችን በ 2015 ዓ.ም(በ2015 በጀት ዓመት) ሊሰበሰብ ከታቀደው 65,351,798 ዉስጥ ለመሰብሰብ የተቻለዉ 77,241,140.53 ሲሆን ይህም በመቶኛ ሲታይ 118.2% ማሳካት ተችሏል።ይህ ውጤት ከ 2014 በጀት ዓመት ገቢ አንፃር ሲታይ በ 25,016,552.66(67.6%) በመብለጥ መሰብሰብ ተችሏል።ይህም ዉጤት የተመዘገበዉየሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት;የጽ/ቤቱ ማኔጅሜንት አካላት እንዲሁም ባለሙያዎች በጋራ በመረባረብ የመጣ ዉጤት መሆኑንም ለመግለፅ እወዳለዉ።
በ 2016 በጀት ዓመትም በ 2015 በጀት ዓመት ከነበረዉ ዕቅድ 65,351,798 ወደ 116,966,802 በማሳደግ በዚህ በጀት ዓመት ይህን 116,966,802 ለመሰብሰብ የጋራ ቅንጅት የሚያስፈልግ መሆኑን እየገለፅኩ የወረዳችንን ገቢ በማሳደግ የህብረተሰቡን የመልማት ፍላጎት ማሟላት ይገባል እላለዉ።

ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘራችሁ ዕጩ ተወዳዳሪዎች በቀን 25/09/2015 ዓ.ም በመገኘት የፅሁፍ ፈተና እንድትወስዱ ስንል እናሳውቃለን።
31/05/2023

ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘራችሁ ዕጩ ተወዳዳሪዎች በቀን 25/09/2015 ዓ.ም በመገኘት የፅሁፍ ፈተና እንድትወስዱ ስንል እናሳውቃለን።

በቀን 16/09/2015 ዓ.ም በምጣኔ ጥ/የታ/ት/ትና የአገ/ቅ/አ/ዳይሬክቶሬት በኩል በተደረገው የተገልጋዮች የአገልግሎት ዕርካታ ደረጃ ጥናት መነሻ ከወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ባለሙያዎች ጋር ...
24/05/2023

በቀን 16/09/2015 ዓ.ም በምጣኔ ጥ/የታ/ት/ትና የአገ/ቅ/አ/ዳይሬክቶሬት በኩል በተደረገው የተገልጋዮች የአገልግሎት ዕርካታ ደረጃ ጥናት መነሻ ከወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ባለሙያዎች ጋር የጋራ ዉይይት በማድረግ በጥናቱ የተነሱ ክፍተቶችን በመውሰድ እርማት የሚያስፈልጉ ጉዳዮችንም ለማረም በመስማማት፤በጥሩ ጎን የተነሱትንም በማስቀጠል በቀጣይ ለተገልጋዮች ምቹ አገልግሎት ለመስጠት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል::

16/05/2023
በቀን 16-06-2015 ዓ.ም በዲላ ዙሪያ ወረዳ ከሚገኙ አደረጃጀቶች (እድር፣የሀይማኖት ይት የተካሄደ ሲሆን የወረዳው ገቢ ጽ/ቤት ሀላፊ የሆኑት አቶ አሸናፊ ሀልቻዬ እንዳሉት ገቢን ማሳደግ ...
23/02/2023

በቀን 16-06-2015 ዓ.ም በዲላ ዙሪያ ወረዳ ከሚገኙ አደረጃጀቶች (እድር፣የሀይማኖት ይት የተካሄደ ሲሆን የወረዳው ገቢ ጽ/ቤት ሀላፊ የሆኑት አቶ አሸናፊ ሀልቻዬ እንዳሉት ገቢን ማሳደግ የምንችለው ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የጋራ ርብርብ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ አስረድተው ከዚህም ውስጥ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት አደረጃጀቶች በግብር አሰባሰብ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ ኖሯቸው ግብር ከፋዪን በግብር ዙሪያ ግንዛቤ እንዲያስጨብጡ መድረኩ መዘጋጀቱን አስረድተዋል።
በጽ/ቤቱ የምጣኔ ጥናት የታክስ ት/ትና የአገ/ቅ/አ/ዳይሬክቶሬት በኩል በሰነድ የቀረበ ስልጠና መስጠት ተችሏል። ተሳታፊውም የጋራ ግንዛቤና አቋም በመያዝ ስልጠናው ተጠናቋል።

Address

ዲላ ዙሪያ ጪጩ
Dilla

Telephone

+251955980632

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዲላ ዙሪያ ወረዳ ገብዎች ባለሥልጣን ቅ/ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share