26/12/2025
የደቡብ ኢትዮጽያ ክልል ትምህርት ቢሮ በት/ቤቶች ምገባ ፕሮግራም ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ነዉ
#ዲላ ታህሳስ 17/2018
የደቡብ ኢትዮጽያ ክልል ትምህርት ቢሮ በሀገር በቀል ትምህርት ቤቶች ምግብ ፕሮግራም በምግብ ደህንነት ፣ አያያዝና አጠቃቀም እንዲሁም አዘገጃጀት እና ንጽሕና አጠባበቅ ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና በዲላ ከተማ እየሰጠ ይገኛል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ የትምህርት ቤቶች ምገባ ፕሮግራም የተማሪዎች መጠነ መቅረት፣ መጠነ ማርፈድ እና መጠነ መድገም ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልጿል።
የት/ቤቶች ምገባ ከምግብነት ባለፈ የተማሪዎችን ውጤት ስለሚያሻሽል ምግቡ በሚዘጋጅበት ወቅት ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥቷል።
በመድረክ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የቢሮ ምክትል ኃላፊና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ኢሳያስ እንድርያስ ከምግብ ዝግጅትና አያያዝ ምግብ አዘጋጆች የግልና የማብሰያ ዕቃ ንጽሕና አጠባበቅ ፣ የመጸዳጃ ቤት አጠቃቀምና የውሃ ንጽሕና አጠባበቅ ልዩ ትኩረት ሊደረግበት እንደሚገባ ገልጿል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአለም ምገባ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ልዑልሰገድ ይመር የትምህርት ቤቶች ምገባ አላማዎች መካከል የተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ መጨመር፣ ወላጆች ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት እንድልኩ እንደሚያደርግ ፣ የአጭር ጊዜ ረሀብ እንደሚያሳታግስ ፣ የሴት ተማሪዎችን ተሳትፎ ማሳደግ ፣ የተማሪዎችን ጤና ማሻሻል እና የአርሶ አደሮችን ምርታማነት ማሳደግ ከአላማዎቹ እንደሚጠቀሱ መሆኑን ገልጸዋል
ስልጠናው ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን
ከክልሉ ከሁሉም ዞኖች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
@የጌዴኦ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን