South Ethiopia Regional State Water and Energy Bureau

South Ethiopia Regional State Water and Energy Bureau ይህ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ትክክለኛ የፌስቡክ ገፅ ነው።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊና የጎፋ ምርጫ ክልል 1 የክልል ምክር ቤት ዕጩ ክቡር ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ ድምፃቸውን ሰጡግንቦት 24/2018 ዓ.ም የቢሮው  ኃላፊ ክቡር ...
01/06/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊና የጎፋ ምርጫ ክልል 1 የክልል ምክር ቤት ዕጩ ክቡር ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ ድምፃቸውን ሰጡ

ግንቦት 24/2018 ዓ.ም

የቢሮው ኃላፊ ክቡር ኢንጂነር አክሊሉ አዳኝ በሚወዳደሩበት የምርጫ ክልል በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።
በከተማዋ የተለያዩ ጣቢያዎች ማህበረሰቡ ከማለዳው ጀምሮ በነቂስ በመውጣት ድምጹን እየሰጠ ይገኛል።

31/05/2026

ከ2018 ዓ.ም ስኬቶች መካከል፦

ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የወቻማ ንፁህ የመጠጥ ውሃና የመብራት ኃይል ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነግንቦት 18/2018 ዓ.ምበጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ ከ32 ሚ...
27/05/2026

ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የወቻማ ንፁህ የመጠጥ ውሃና የመብራት ኃይል ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ

ግንቦት 18/2018 ዓ.ም

በጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የወቻማ ንፁህ የመጠጥ ውሃና የመብራት ኃይል ፕሮጀክት ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

ፕሮጀክቱ በጌዴኦ ዞን መንግሥት ድጋፍ የተገነባ ሲሆን፣ በአካባቢው የነበረውን የንፁህ የመጠጥ ውሃ እጥረት በመቅረፍ ለበርካታ ነዋሪዎች እፎይታ እንደሚያመጣ ተገልጿል።

በማስመረቂያ ሥነ-ሥርዓቱ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የኢኮኖሚ ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ኢንጅነር ስለሺ ኮሬ (ዶ/ር)፣ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ግዞቸው አየለ፣ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴንን ጨምሮ ሌሎች የዞንና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

በኧሌ ዞን ኮላንጎ ዙሪያ ወረዳ ደጋ ማሽሌ ቀበሌ በክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ  ከ9.1 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ።ኮላንጎ ፤ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም(ኧዞመኮ) ...
26/05/2026

በኧሌ ዞን ኮላንጎ ዙሪያ ወረዳ ደጋ ማሽሌ ቀበሌ በክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ከ9.1 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ።

ኮላንጎ ፤ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም(ኧዞመኮ)

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኧሌ ኮላንጎ ዙሪያ ወረዳ ደጋማሽሌ ቀበሌ ከ9.1 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

በፕሮጀክቱ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባህልና ስፖርት ብሮ ሃላፊ ክቡር አቶ ኦላዶ ኦሎ እና የኧሌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አርሼሎ አርካሌ ጨምሮ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የደጋማሽሌ ቀበሌ ንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከአንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ በላይ ለሚሆኑ የቀበሌ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ እንደሆነ ተጠቁሟል።

በቀበሌው ከዚህ ቀደም ከውሃ አቅርቦት ጋር በተያያዘ ይነሳ የነበረውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ በመመለስ ረገድ የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።በኧሌ ዞን ኮላንጎ ዙሪያ ወረዳ ደጋ ማሽሌ ቀበሌ በክልሉ ውሃ ብሮ ከ9.1 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ።

መረጃው የዞኑ መ/ኮ/ጉ/አገልግሎት ነው።

የመረጃ ምንጮቻችንን ይጎብኙ
Face book: https://www.facebook.com/share/1CdGNHnV4G/
Telegram Channel: https://t.me/southethiopiawaterenergy2026

"መንግሥት የህዝቡን ጥያቄ በቅርበት እያዳመጠ እየፈታ ነው"- ዶ/ር መርሁን ፍቅሩበሁምቦ ወረዳ ፋንጎ ገልጬጫ ቀበሌ ከ46 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ ፋንጎ ገልጬጫ ንፁህ መጠጥ ው...
25/05/2026

"መንግሥት የህዝቡን ጥያቄ በቅርበት እያዳመጠ እየፈታ ነው"- ዶ/ር መርሁን ፍቅሩ

በሁምቦ ወረዳ ፋንጎ ገልጬጫ ቀበሌ ከ46 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ ፋንጎ ገልጬጫ ንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

ግንቦት 17/2018 ዓ.ም

በምረቃው ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር መርሁን ፍቅሩ እንደተናገሩት መንግሥት የህዝቡን ጥያቄ በቅርበት እያዳመጠ እየፈታ ነው።

የህዝቡን የተለያዩ የልማት ጥያቄዎች ለመፍታት እየሠራ እንደሆነም በመግለጽ በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ ተቋማትን በመጠበቅ ኅብረተሰቡ የሚጠበቅበትን እንዲወጣ ጠቀዋል።

የወላይታ ዞን የመንግሥት ዋና ተጠሪ ዶክተር አማረ አቦታ ብልጽግና ፓርቲ ሰው ተኮር እና የሰው ልጅ መሠረታዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት በትኩረት እየሠራ የሚገኝ ፓርቲ ነው ብለዋል።

ፓርቲው የህዝባችንን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ፣ በጤናው ዘርፍ የእናቶችን እና የህፃናት ጤና ለማሻሻል እየሠራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

በብልጽግና ፓርቲ የሚመራው መንግሥት የህዝቡን ጥያቄ በየደረጃው በዕቅድ እየመለሰ መምጣቱን በመግለጽ የመንገድ እና የሌሎች መሠረተ ልማትም እንደሚጀመር አረጋግጠዋል።

የሁምቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ገቡ የፋንጎ ገልጬጫ ህዝብ በንፁህ መጠጥ ውሃ እጦት ምክንያት ለተለያዩ ችግሮች ሲዳረግ እንደነበረ በማንሳት ፕሮጀክቱ የዘመናት የህዝባችንን ጥያቄ የፈታ ነው ብለዋል።

ፕሮጀክቱ ከ16 ሺህ በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ በመግለጽ በዘላቂነት እንዲያገለግል የመጠበቅና የመንከባከብ ደርሻ ሁሉም እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

በአጠቃላይ ሀገራዊ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲን በመምረጥ የጀመረውን ልማት እንዲያስቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል ኃላፊዎቹ።

የአካባቢው ነዋሪዎች የዘመናት የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግር እንደተፈታላቸው እንዲሁም በመመረቁ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

በምረቃ ፕሮግራሙ የፌደራል የክልል የዞን የሁምቦ ወረዳ እና የጠበላ ከተማ አስተዳደር አመራሮች እና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

መረጃው የዞኑ ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ነው።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና በሕ/ተ/ም/ቤት የመንግስት ተጠሪ...
25/05/2026

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በተገኙበት የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በመካሄድ ላይ ይገኛል

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና በሕ/ተ/ም/ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፤ በተገኙበት 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ አስመልክቶ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ በክልሉ በጎፋ ዞን፤ በሳውላ ከተማ በታላቅ ህዝባዊ ተሳትፎ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

መደበኛ ጊዜውን ጠብቆ የሚካሄድ ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፤ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሰፊ ብዝኃነትን ባቀፉ ሀገራት ዲሞክራሲያዊ ስርዓትን በማስፋን፤ በዜጎች ተሳትፎ እና በሕዝቦች ትብብር ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥም ሆነ ለጠንካራ ኅብረ-ብሔራዊ ሀገረ-መንግስት ግንባታ ሚናው ከፍተኛ ነው፡፡

ምርጫ ዜጎች የዜግነት መብታቸውን ተጠቅመው በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ያላቸውን የመወሰን መብት በተግባር በመተርጎም የስልጣን ምንጭ ህዝብ መሆኑን ከማረጋገጥ ባለፈ በፀና መሠረት ላይ የተገነባች ሀገር ለትውልድ በማሻገሩ ረገድ ደማቅ አሻራቸውን በድምፃቸው የሚያኖሩበት ሂደት ጭምር ነው፡፡

በዚህ ረገድ ግንቦት 24 በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ፤ የመራጪነት ካርድ የወሰዱ 50 ሚሊዮን ዜጎች በምርጫው በመሳተፍ፤ በድምፃቸው መፃይ የሀገራቸውን ማህበረ-ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ የፖሊሲ አቅጣጫ ከመወሰን ባሻገር በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ጉዞ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ይከፍታሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

መንግስት ባለፉት የለውጥ አመታት ለዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ በቁርጠኝነት በመስራት በሀሳብ ልዕልና ላይ የተመሰረተ አካታችና አሳታፊ የፖለቲካ ባህል የሚያጎለብቱ እና የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታን የሚያጠናክሩ ተቋማዊ ሪፎርሞችን በማድረግ ጭምር ተጨባጭ ለውጥ ማስመዝገብ መቻሉ ይታወቃል፡፡

7ኛው ሀገራዊ ምርጫም የተጀመሩ ጥረቶችን በማጎልበት እንደ ሀገር ለሰነቅነው ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ማበብ አንድምታው ከፍተኛ ነው፡፡

ለዚህም መንግስት ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ፤ ፍትሃዊ፤ ነፃና ሁለንተናዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ በቁርጠኝነት ሲሰራ የቆየ ሲሆን፤ በሁሉም ረገድ በቂ ዝግጅት ማድረግ መቻሉም ታወቋል፡፡

በዛሬው ዕለት ክቡር ርዕሰ መስተዳድሩን እና በሕ/ተ/ም/ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፤ ጨምሮ የክልሉ አስተባባሪ አካላት፤ በጎፋ ዞን የፓርቲው ዕጩ ተወዳዳሪዎች፤ ደጋፊዎች እና አባላት በተገኙበት፤ ፓርቲው የምረጡኝ የምርጫ ቅስቀሳውን በሳውላ ከተማ በከፍተኛ ህዝባዊ ተሳትፎ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

ምንጭ፦የክልሉ መ/ኮ/ጉ/አገልግሎት

ብልፅግና ፓርቲ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግናና ለህዝብ ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ በርካታ ፕሮግራሞችንና አጀንዳዎችን በመቅረጽ በሀገር ደረጃ በርካታ ለውጦችን እያስመዘገበ መሆኑን ኢንጅነር አክ...
24/05/2026

ብልፅግና ፓርቲ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልፅግናና ለህዝብ ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ በርካታ ፕሮግራሞችንና አጀንዳዎችን በመቅረጽ በሀገር ደረጃ በርካታ ለውጦችን እያስመዘገበ መሆኑን ኢንጅነር አክሊሉ አዳኝ ተናገሩ ።

ግንቦት 15/2018 ዓ.ም

በጎፋ ዞን ደምባ ጎፋ ወረዳ በወይዴ ውርኪ ማዕከል ላይማ ፃላ ክላስተር የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳና የእጩዎች ማስተዋወቅ መርሃ ግብር በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ እና ለክልል ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በእጩነት የቀረቡት ኢንጅነር አክሊሉ አዳኝ እንደገለጹት፣ብልፅግና ፓርቲ ሀገርን መምራት ከጀመረ ወዲህ በብዙ ዘርፎች ውጤታማ ለውጦችን አስመዝግቧል ተባለ።

እንደ ገለጻቸው፣ፓርቲው በበርካታ ፈተናዎችና ውስብስብ ችግሮች ውስጥ አልፎ ሀገሪቱን እየመራ ሲሆን፣የህዝብ ችግሮችን በመፍታት እና የልማት ሥራዎችን በማፋጠን ረገድ አበረታች ውጤቶችን መኖሩን አብራርተዋል።

ኢንጅነር አክሊሉ አክለውም፣የጎፋ ሕዝብ በሥራው ታታሪና ጀግና መሆኑን ገልጸው፣ መላው ሕዝብ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ብልፅግና ፓርቲን በመምረጥ ለሀገሪቱ ብልፅግና የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

የጎፋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ቦረና ቦላዶ በበኩላቸው፣ፓርቲው በ“መደመር” እሳቤ በመመራት በሁሉም ዘርፎች እድገት ለማምጣት እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

የደምባ ጎፋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ያዕቆብ ደበላ በበኩላቸው፣ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት ዓመታት ያከናወናቸውን ሥራዎችና ወደፊት ለመፈጸም ያቀዳቸውን ዕቅዶች ለህዝቡ በዝርዝር መብራራታቸውን ገልጸዋል።

አቶ ያዕቆብ አክለውም፣ፓርቲው ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር ለማሸጋገር ያቀዳቸው ዕቅዶች እውን እንዲሆኑ ህብረተሰቡ በሚቀጥለው ሀገራዊ ምርጫ ብልፅግና ፓርቲን እንዲመርጥ ጥሪ አቅርበዋል።

በመጨረሻም አስተዳዳሪው መላው ህዝባችን በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ብልፅግና ፓርቲን መምረጥ የሀገረቱን ብልፅግና እንዲያረጋግጥ ጥሪ አቀርባለሁ ብለዋል።

በዕለቱ በተካሄደው መርሃ ግብር የክልል፣የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና አካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል ።
የደምባ ጎፋ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን

መረጃው የወረዳው መ/ኮ/ጉ/አገልግሎት ነው።

በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የቂሻ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ለአገልግሎት በቃ‎‎ግንቦት 15-2018 ዓ/ም)፦ዲላበዞኑ ጮርሶ ወረዳ በዞን ድጋፍ ከ15 ሚ...
23/05/2026

በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የቂሻ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ለአገልግሎት በቃ

‎ግንቦት 15-2018 ዓ/ም)፦ዲላ
በዞኑ ጮርሶ ወረዳ በዞን ድጋፍ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የቂሻ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።

‎ፕሮጀክቱ ከ2 ሺህ በላይ ህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ተገልጿል።

‎በምረቃ መርሃግብር የጌዴኦ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ኢንጂነር ተመስገን ጥላሁን፣ የጮርሶ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ መኮንን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት ኃላፊዎች እና የአከባቢ ህብረተሰብ ክፍል ተገኝቷል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተገባደደው በጀት ዓመት በከተማና በገጠር 65 የውሃ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ከ418 ሺህ በላይ ህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ መሆናቸውን የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ መረጃ ያመላክታል።

የቢሮ ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት

የመረጃ ምንጮቻችንን ይጎብኙ
Face book: https://www.facebook.com/share/1CdGNHnV4G/
Telegram Channel: https://t.me/southethiopiawaterenergy2026


በጌዴኦ ዞን ቡሌ  ወረዳ ከ10.6 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነባ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ‎‎ግንቦት 14/2018 ዓ.ም ፦ዲላ ‎በዞኑ ‎ቡሌ ወረዳ ባሡራ-ዳሮ ቀበሌ ከ10.6 ሚሊዮን ብ...
22/05/2026

በጌዴኦ ዞን ቡሌ ወረዳ ከ10.6 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነባ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ

‎ግንቦት 14/2018 ዓ.ም ፦ዲላ

በዞኑ ‎ቡሌ ወረዳ ባሡራ-ዳሮ ቀበሌ ከ10.6 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነባ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በመመረቅ ላይ ይገኛል።

‎የጌዴኦ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተገኝ ታደሴ፣የቡሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በራቆ በራሶ፣ ጨምሮ ከፍተኛ የዞን፣ የወረዳና የቡሌ ከተማ አስተዳደር ስራ አስፈፃሚ አካላት በተገኙበት የምረቃ ስነስርዓት ተካሂዷል።

መረጃው የወረዳው መንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ነው።

የቢሮ ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት

የመረጃ ምንጮቻችንን ይጎብኙ
Face book: https://www.facebook.com/share/1CdGNHnV4G/
Telegram Channel: https://t.me/southethiopiawaterenergy2026

የብሔራዊ አንድ ዋሽ ፕሮግራም የ6 ዓመትና የ2018 ዓ.ም አፈጻጸም ግምገማ  ተካሄደ።ግንቦት 13/2018 ዓ.ም  የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በብሔራዊ አንድ ዋሽ ፕሮግራም ከ6 ዓመታት በላይ ሲ...
21/05/2026

የብሔራዊ አንድ ዋሽ ፕሮግራም የ6 ዓመትና የ2018 ዓ.ም አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ።

ግንቦት 13/2018 ዓ.ም
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በብሔራዊ አንድ ዋሽ ፕሮግራም ከ6 ዓመታት በላይ ሲከናወኑ የቆዩ ተግባራትን እና የ2018 ዓ.ም አፈጻጸምን ከባለድርሻ አካላት ጋር በሀዋሳ እየገመገመ ነው።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ታምሩ ገደፉ፣ ፕሮጀክቶች በመጀመሪያና በመጨረሻ ደረጃ ላይ ፈተና እንደሚያጋጥማቸው ጠቅሰው፣ የተጀመሩ ስራዎችን በቀሪው አጭር ጊዜ በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።

አቶ ታምሩ ፕሮግራሙ ከ6 ዓመታት በላይ ሲተገበር በተከታታይ ግምገማ እየተመራ መሆኑን ገልጸው፣ በመጠጥ ውሃ ዘርፍ በገጠር 94 በመቶ እና በከተማ 69 በመቶ ተደራሽነት መመዝገቡን አስታውቀዋል። በሳኒቴሽን ዘርፍም 80 በመቶ እንዲሁም በአጠቃላይ 75 በመቶ ተደራሽነትን ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል።

እንዲሁም ለ2019 ዓ.ም እቅድ ክልሎች በየክልላቸው ባለው ተጨባጭ ሁኔታ መሠረት የፕሮጀክቶች ቀጣይነት ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

የአንድ ዋሽ ፕሮግራም የምዕራፍ ሶስት አተገባበር ከቀደሙት በተለየ መልኩ እንደሚተገበር የገለጹት አቶ ታምሩ፣ ለፕሮግራሙ ቀጣይ ስኬት 103 ወረዳዎችና 48 ከተሞች እንደመነሻ መለየታቸውን ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል የሲዳማ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀይለየሱስ ተፈራ፣ መድረኩ በአንድ ዋሽ ፕሮግራም ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ስራዎችን በጥልቀት የሚገመገም አስፈላጊ መድረክ መሆኑን ገልጸው፣ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ በማጠናቀቅ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በውይይቱ ላይ የውሃ ዘርፍ የ3ኛ ሩብ ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት፣ የግዢ ሂደት፣ የጤናና የትምህርት ዘርፎች የ3ኛ ሩብ ዓመት እና የድምር አፈጻጸም ሪፖርቶች፣ የፋይናንስ ስርጭትና አጠቃቀም፣ የ2019 ዓ.ም ረቂቅ በጀት እንዲሁም የምዕራፍ ሶስት የአንድ ዋሽ ፕሮግራም አተገባበር ላይ የተዘጋጁ ጥናታዊ ጽሁፎች ለውይይት ቀርበዋል።

የውይይቱ ዋና ዓላማ እስካሁን የተመዘገቡ ውጤቶችን በመገምገም የምዕራፍ ሶስት የአንድ ዋሽ ፕሮግራምን በተሻለ አፈጻጸም ለማስፈጸም የሚያስችል ግንዛቤ መፍጠር መሆኑ ተጠቁሟል።

በመድረኩ ከውሃና ኢነርጂ፣ ከጤና፣ ከትምህርትና ከፋይናንስ ሚኒስቴሮች እንዲሁም ከክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮዎች ኃላፊዎችና የዘርፉ ሙያተኞች እየተሳተፉ ነው።

መረጃው የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ነው።

የቢሮ ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት

የመረጃ ምንጮቻችንን ይጎብኙ
Face book: https://www.facebook.com/share/1CdGNHnV4G/
Telegram Channel: https://t.me/southethiopiawaterenergy2026

Address

Dila
153

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Ethiopia Regional State Water and Energy Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share