Amhara Sayint woreda Communication Affairs/አምሐራ ሳይንት ወረዳ ኮሙኒኬሽን

  • Home
  • Ethiopia
  • Dessie
  • Amhara Sayint woreda Communication Affairs/አምሐራ ሳይንት ወረዳ ኮሙኒኬሽን

Amhara Sayint woreda Communication Affairs/አምሐራ ሳይንት ወረዳ ኮሙኒኬሽን ወረዳው ከባህር ወለል በላይ ከ596 እስከ 4247 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን በአባዛኛው ወጣ ገባና በፕላቶ መሬት የተከበበ ነው፡፡

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነዉ።በደቡብ ወሎ ዞን አማራ ሳይንት ወረዳ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጮች ድምጻቸውን እየሰጡ ነው።አጅባር:ግንቦት 24/2018(አማራ  ሳይንት ኮሙዩኒኬሽን)
01/06/2026

ኢትዮጵያ እየመረጠች ነዉ።

በደቡብ ወሎ ዞን አማራ ሳይንት ወረዳ ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መራጮች ድምጻቸውን እየሰጡ ነው።
አጅባር:ግንቦት 24/2018(አማራ ሳይንት ኮሙዩኒኬሽን)

ዜጎች ድምጽ ለመስጠት ወደ ምርጫ ጣቢያ ሲያቀኑ መያዝ ያለባቸው…ዜጎች ድምጽ ለመስጠት ወደ ተመዘገቡበት የምርጫ ጣቢያ ሲያመሩ የሚከተሉትን አስፈላጊ ነገሮች መያዝና ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡👉 ...
30/05/2026

ዜጎች ድምጽ ለመስጠት ወደ ምርጫ ጣቢያ ሲያቀኑ መያዝ ያለባቸው…

ዜጎች ድምጽ ለመስጠት ወደ ተመዘገቡበት የምርጫ ጣቢያ ሲያመሩ የሚከተሉትን አስፈላጊ ነገሮች መያዝና ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡

👉 የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ ካርድ፣

👉የማንነት ማረጋገጫ መታወቂያ፣

👉በመራጮች ምዝገባ ወቅት የተረጋገጠበት ሌላ ሰነድ ያላት/ው ወይም ማንነትዎ በምርጫ ምዝገባ ወቅት በምስክሮች ስለመረጋገጡ በመራጮች መዝገብ ላይ የሰፈረ፣

👉የመራጮች መዝገብ ላይ ስሙ የሰፈረ፣

👉ድምጽ ያልሰጡ መሆኑ ሲረጋገጥ ድምጽዎን የመስጠት መብት አለዎት፣

👉እንዲሁም የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ የጠፋበት መራጭ ጉዳዩን ለምርጫ ጣቢያው በማስረዳት ማንነቱን እንዲሁም በመዝገቡ ላይ ስሙ የሰፈረና ያልመረጠ መሆኑ ሲረጋገጥ ጉዳዩ በቃለ ጉባዔ ተይዞ እንዲመርጥ ይደረጋል፡፡

መረጃው ከደሴ ፋና ኤፍ ኤም 96.0 የተወሰደ ነው።

የአማራ ሳይንት ወረዳ ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት ከሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ጋር በመተባበር  ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ ነዋሪዎች   በጎችን በመግዛት ድጋፍ አደረገ።ግንቦት 22/20...
30/05/2026

የአማራ ሳይንት ወረዳ ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት ከሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ ነዋሪዎች በጎችን በመግዛት ድጋፍ አደረገ።

ግንቦት 22/2018ዓ.ም አጅባር(አማራ ሳይንት ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን)

የአማራ ሳይንት ወረዳ ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት ከሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለችግር ተጋላጭ ለሆኑ ነዋሪዎች በጎችን በመግዛት ድጋፍ አድርጓል።

የፅ/ቤቱ ሃላፊ ወ/ሮ መልሽው ሲሳይ እንደገለፁት ከሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ጋር በመተባበር በዛሬው ዕለት 18 ለሚደርሱ ወላጅ አልባና በከፋ ችግር ውስጥ ለሚገኙ የ06፤04እና 05 ቀበሌ ነዋሪዎች በ360 ሽህ ብር 61 በጎችን በመግዛት ድጋፍ ተደርጓል።

በሚከተሉት #ሊንኮች በመግባት #ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ:-

https://www.facebook.com/AmharaSayintworedaCommunicationAffairs

ዩቲዩብ:-
https://www.youtube.com/channel/UC9q-EOZGRREV8kr104kL-Hw

ቴሌግራም:-

https://t.me/amharasayintcommunication

ኢንስታግራም:-
https://www.instagram.com/amharasayintworedacomm?igsh=dG9zcXprdGFtMGw=

ቲክቶክ:-
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8zZVyEvYbLR&_r=1

ቲውተር:-
https://x.com/AmharaSayintCom?t=RbymDS5h2-YpyQjR9Ykypw&s=09

ኢትዮጵያ ትመርጣለች! የሉዓላዊነት እና የሀገረ-መንግሥት ግንባታ ሕያው ማሳያ ******************* "ኢትዮጵያ ትመርጣለች!" የሚለው ሐረግ ከመፈክር እጅግ የላቀ ትርጉም አለው። ይህ...
30/05/2026

ኢትዮጵያ ትመርጣለች! የሉዓላዊነት እና የሀገረ-መንግሥት ግንባታ ሕያው ማሳያ
*******************

"ኢትዮጵያ ትመርጣለች!" የሚለው ሐረግ ከመፈክር እጅግ የላቀ ትርጉም አለው። ይህ ቃል የሉዓላዊነታችን እና የጽኑ ሀገረ-መንግሥት ግንባታችን ሕያው ማሳያ ነው።

የምርጫ ካርድን በሳጥን ውስጥ መጨመር፣ ኢትዮጵያ የራሷን እጣ ፈንታ በገዛ ልጆቿ ጥበብ እና እጅ የመወሰን የማያወላውል መብቷን ለዓለም በኩራት የምታውጅበት ታሪካዊ የክብር መድረክ ነው።

ይህ ሂደት የሀገራችንን የነገ አቅጣጫ በራሳችን ውሳኔ የምንቀርጽበት የማይናወጥ የሉዓላዊነት ምሰሶ ነው።

በዚህ ውብ የዴሞክራሲ ጉዞ፣ 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 861 ድምጻውያን ብሩህ ታሪክ ለመሥራት ተዘጋጅተዋል።

42 የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እንዲሁም 10 ሺህ 438 እጩዎች (80ዎቹን የግል እጩዎች ጨምሮ) የሕዝብን ድምፅ እና አደራ ለመቀበል በአደባባይ ቀርበዋል።

ይህ የነቃ እና ሰፊ ተሳትፎ ጠንካራ፣ አቃፊ እና ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት ያለንን ብሔራዊ ራዕይ በሚገባ ያንጸባርቃል።

የሂደቱን ግልጽነት እና ተዓማኒነት በተግባር ለማረጋገጥ 55 የሀገር ውስጥ ሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎች፣ 59 የአፍሪካ ኅብረት እና 26 የኢጋድ አባላት በስፍራው ተገኝተዋል።

68 የሚዲያ ተቋማት (56 ሀገር በቀል እና 12 የውጭ ሚዲያዎች) ይህንን የሉዓላዊነት ድል ለዓለም ይዘግባሉ።

እያንዳንዱ የምንሰጠው ድምፅ፣ የሀገራችንን ሉዓላዊነት የሚያጸና እና የተረጋጋች ኢትዮጵያን መሠረት የሚያጠነክር ቋሚ የሕዝብ ማኅተም ነው።

🗳️ ነጋችሁን በካርዳችሁ ምረጡ !ባሕር ዳር: ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በሕይወት ውስጥ ምርጫዎች አሉ። የወደደውን የመረጠ በወደደው ይኖራል። ያልመረጠ ግን በተመረጠለት የሚኖር ይኾ...
30/05/2026

🗳️ ነጋችሁን በካርዳችሁ ምረጡ !

ባሕር ዳር: ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (አሚኮ) በሕይወት ውስጥ ምርጫዎች አሉ። የወደደውን የመረጠ በወደደው ይኖራል። ያልመረጠ ግን በተመረጠለት የሚኖር ይኾናል።

ኢትዮጵያውያን ነጋቸውን በካርዳቸው እንዲመርጡ አማራጭ ቀርቦላቸዋል። አማራጩ ነገን የመምረጥ፣ ሀገርን ላመኑበት የመስጠት ጉዳይ ነው። ካርዱን በአግባቡ የተጠቀመ በሀገሩ እና በራሱ ነገ ላይ ይወስናል። ካርዱን በአግባቡ ያልተጠቀመ ግን የሀገሩን እና የራሱን ነገ ለሌሎች አሳልፎ ይሰጣል።

በዴሞክራሲያዊ ሂደት ውስጥ ዜጎች መንግሥታቸውን በካርዳቸው ይመርጣሉ፤ ሥልጣንንም በካርዳቸው አደራ ይሰጣሉ። ያለ ዜጎች ፈቃድ የሚገኝ ሥልጣን ሕጋዊ አይደለም፤ ቅቡልነትም የለውም። በተለይ በዚህ ዘመን ያለ ካርድ የሚገኝ ሥልጣን ከዘመኑ እሳቤ ጋር የሚሄድ አይደለም።

ኤፍሬም ማዴቦ "ኢትዮጵያና ሕግ መንግሥታዊ ምርጫዎቿ በተሰኘው መጻሕፋቸው እስከ ዛሬ ለብዙ ዘመናት ያለ ዴሞክራሲ ተጉዘን ሊኾን ይችላል። ከዛሬ በኋላ ግን ኢትዮጵያ ያለ ዴሞክራሲ የምታደርገው እያንዳንዱ እርምጃ አንድነቷን ያላላዋል" ሲሉ አስፍረዋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ዛሬ በደረሰበት ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ዕድገት ደረጃው ከዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ውጭ መተዳደር አይፈልግም።

ይህ ብቻ ሳይኾን ብዙ ብሔረሰቦች፣ የተለያዩ ሃይማኖቶች እና የባሕል ስብስቦች የሚገኙባትን ትልቅ ሀገር ከአሁን በኋላ ከዴሞክራሲ ውጭ ማሥተዳደር እንደማይቻል ያለፉት ዓመታት ታሪካችን በግልጽ አሳይቶናል ነው የሚሉት።

ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲኖር ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እና በምርጫ የተመረጠ መንግሥት ያስፈልጋል ማለት ነው።

ምርጫ ለሁሉም ዜጎች ዕኩል የተሰጠ መብት ነው። የአንድ ሀገር ዜጎች ይሕንን መብታቸውን በሚገባ እንዲጠቀሙ የምርጫው ሂደት ሁሉም የኅብረተሰብ አባል በቀላሉ የሚረዳው፣ ሳይቸገር እና ሳይጨነቅ ደስ ብሎት የሚሳተፍበት ግልጽ ሂደት መኾን አለበት ነው የሚሉት።

ዜጎችም መብታቸውን በአግባቡ መጠቀም አለባቸው። ሀገራቸውን የሚወዱ ሁሉ በነገዋ የሀገራቸው እጣ ፈንታ ላይ መወሰን አለባቸው።

ምርጫ የድምጽ ሰጪውን ኅብረተሰብ ጥቅም እና ፍላጎት በፖለቲካ ሥርዓቱ ውስጥ እንዲወክል ያደርጋል፤ ጠንካራ እና የተረጋጋ መንግሥት እንዲፈጠር ያደርጋል፤ ሕዝብ ብቃት ባላቸው አካላት እንዲወከል ያደርጋል፤ የፖለቲካ ባለድርሻዎችን እና ተከታዮቻቸውን ያቀራርባል ይላሉ።

ምርጫ በአንድ በኩል ብቸኛ የሕዝብ ሥልጣን መገለጫ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ በአንድ ሀገር ውስጥ ዴሞክራሲ ለመኖሩ እና ላለመኖሩ ማረጋገጫ መለኪያ ነው። ዴሞክራሲ እና ምርጫ ተለያይተው መኖር አይችሉምና።

ዴሞክራሲ ባለባቸው ሀገራት ውስጥ ሁሉ ምርጫ አለ። ምርጫ ባለበት ቦታ ሁሉ የምርጫ ሂደት አለ። ምርጫ በየትኛውም የዴሞክራሲ ሥርዓት ውስጥ አስፈላጊ ነው። ዴሞክራሲ ደግሞ ከፍተኛ ሕዝባዊ ተሳትፎን የሚጠይቅ ሂደት ነው ይላሉ።

ኢትዮጵያ ከቀናት በኋላ በታሪኳ ለሰባተኛ ጊዜ ጠቅላላ ምርጫ ታካሂደላች። ዜጎች በካርዳቸው ለቀጣይ አምስት ዓመታት ኢትዮጵያን ለሚመራት አካል ሥልጣን ይሰጣሉ። በዴሞክራሲያዊ ሂደት ውስጥ ሥልጣን የሕዝብ ነው፤ ሕዝብ ይሰጣል፤ ሕዝብም ይነሳል።

ኢትዮጵያውያንም በካርዳቸው ነጋቸውን ይመርጣሉ። የያዙት ካርድ ዝም ብሎ አይደለም፤ ነገን የሚመርጡበት፤ የሥልጣን ባለቤታቸውን የሚያረጋግጡበት፤ ስለ ኢትዮጵያ የሚወስኑበት፤ በእነርሱ ቦታ እንደ እነርሱ ኾነው የሚሠሩላቸውን ወኪሎቻቸውን የሚመርጡበት፤ ሀገራቸውን እንደሚወዱ የሚያረጋግጡበት፤ የዴሞክራሲያዊ ሥራዓትን የሚያሰፉበት ነው።

በካርዳችሁ ነጋችሁን ምረጡ፤ የሥልጣን ባለቤትነታችሁንም አረጋግጡ።

#አሚኮ

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ:-1. 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 871 መራጮች ተመዝግበዋል፣2.በአጠቃላይ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች ይወዳደራሉ፤3. 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲ እጩዎች እንዲሁም4. 80 የ...
30/05/2026

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ:-

1. 54 ሚሊዮን 57 ሺህ 871 መራጮች ተመዝግበዋል፣

2.በአጠቃላይ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች ይወዳደራሉ፤

3. 10 ሺህ 438 የፖለቲካ ፓርቲ እጩዎች እንዲሁም

4. 80 የግል እጩዎች በምርጫው ይወዳደራሉ።

5. ፓርቲዎች በተደለደለላቸው የአየር ሰዓት 19 የክርክር መድረኮችን በአምስት ቋንቋዎች አካሂደዋል፤

6. ተፎካካሪ ፓርቲዎች ከ250 ሺህ በላይ ተወካዮቻቸውን የምርጫውን ሂደት እንዲከታተሉ ይልካሉ፤

7. ለታዛቢነት የአፍሪካ ሕብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) ተወካዮቻቸውን ልከዋል፤

8. 59 አባላት ያሉት የአፍሪካ ሕብረት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድን በቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት አሁሩ ኬንያታ እየተመራ ሥራውን ይሰራል፤

9. ኢጋድ 26 አባላት ያሉት የምርጫ ታዛቢዎች ቡድንን ያሰማራል፤

10. በሀገር ውስጥ የተደራጁ 55 ሲቪክ ማኅበራት ፈቃድ ወስደው ወደ ሥራ ገብተዋል፤ 55ቱ የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች 1 ሺህ 562 የምርጫ ታዛቢዎችን አሰማርተዋል።

11. የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭትን በተመለከተ በአዲስ አበባ ለ33፣ በአፋር ለ32፣ በአማራ ለ130፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ለ22፣ በማዕካላዊ ኢትዮጵያ ለ35፣ በድሬዳዋ ለ48፣ በጋምቤላ ለ14፣ በሐረሪ ለ3፣ በኦሮሚያ ለ179፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ለ56፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ለ22 ክልሎች የምርጫ ቁሳቁስ ተሰራጭቷል።

( )

ከነገ በስቲያ "ሰኞ" የት ነዎት?7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊከናወን የቀሩት  ቀናት 2 ብቻ ናቸው።ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመላው አገሪቱ ይከናወናል።ታዲያ እርስዎስ ድምፅዎን በ...
30/05/2026

ከነገ በስቲያ "ሰኞ" የት ነዎት?

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሊከናወን የቀሩት ቀናት 2 ብቻ ናቸው።

ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመላው አገሪቱ ይከናወናል።

ታዲያ እርስዎስ ድምፅዎን በመስጠት በአገርዎ የዴሞክራሲ ጎዞ ላይ አሻራዎን ለማሳረፍ ዝግጁ ነዎት?

EBC

 #ለወረዳችን  #ነዋሪዎች  #በሙሉ❗ በ2018  በጀት አመት በወረዳችን ለሚገኙ 119 ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የአይን ሞራ ግርዶሽ የነፃ ቀዶ ህክምና መሰጠቱ ይታወቃል።      በቀጣይም...
29/05/2026

#ለወረዳችን #ነዋሪዎች #በሙሉ❗

በ2018 በጀት አመት በወረዳችን ለሚገኙ 119 ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የአይን ሞራ ግርዶሽ የነፃ ቀዶ ህክምና መሰጠቱ ይታወቃል።

በቀጣይም ይህ ስራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ከሰኔ 15/2018ዓ.ም እስከ ሰኔ 20/2018ዓ.ም ድረስ በቦሩ ሜዳ ሆስፒታል የአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ይሰጣል።

ለዚህም የቅድመ ልየታ ስራ በአምሐራ ሳይንት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ስለሚሰራ የችግር ተጠቂ የማህበረሰባችን ክፍሎች በተገለፀው ቀን በወረዳችን ሆስፒታል በመገኘት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንድትሆኑ በማለት ጥሪአችንን እናስተላልፋለን።

ይህ መረጃ የደረሳችሁም መረጃውን ለሚመለከታቸው በማድረስ የተለመደ ትብብር ታደርጉልን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን ሲል የአማራ ሳይንት ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት መልዕክቱን አስተላልፏል።

አይነ- ስውርነትን በጋራ እንከላከል

ከ2ሽህ 5መቶ በላይ ተማሪዎችን አገር አቀፍና ክልል አቀፍ  ፈተናዎችን ለማስፈተን የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የአማራ ሳይንት ወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት ገለፀ።አጅባር። ግንቦት ...
29/05/2026

ከ2ሽህ 5መቶ በላይ ተማሪዎችን አገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፈተናዎችን ለማስፈተን የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የአማራ ሳይንት ወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት ገለፀ።

አጅባር። ግንቦት 21/2018ዓ.ም(አማራ ሳይንት ኮሙዩኒኬሽን)

ከ2ሽህ 5መቶ በላይ ተማሪዎችን አገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፈተናዎችን ለማስፈተን የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የአማራ ሳይንት ወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት ገለፀ።

የወረዳው ትምህርት ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ትዕዛዙ አድማሡ እንደገለፁት ከሰኔ 8/2018ዓ.ምጀምሮ በሚሠጡ የክልል አቀፍ ፈተናዎች 1ሽህ 343የ6ኛ ክፍል ተማሪዎችእና 853የ8ኛክፍል ተማሪዎች ክልል አቀፍ ፈተናቸውን ይወስዳሉ።

በወረዳው የሚገኙ በ3የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመማር ላይ የሚገኙ 415ተማሪዎችደግሞ ከሰኔ 24/2018ጀምሮ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚወስዱ መሆኑን ሃላፊው ገልፀዋል።

በአጠቃላይ በሁሉም የክፍል ደረጃዎች 2ሽህ6 11ተማሪዎች አገር አቀፍና ክልል አቀፍ ፈተናዎችን እንደሚወስዱ የገለፁት ሃላፊው በትምህርት ተቋማት ደረጃ ተማሪዎች ለፈተና የሚያዘጋጁ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

በየደረጃው የሚሠጡ ፈተናዎች
ያለምንም ችግር እንድጠናቀቁ ሁሉም ባለ ድርሻአካላት የበኩላቸውን ድጋፍእንድያደርጉ አቶ ትዕዛዙ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በሚከተሉት #ሊንኮች በመግባት #ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ:-

https://www.facebook.com/AmharaSayintworedaCommunicationAffairs

ዩቲዩብ:-
https://www.youtube.com/channel/UC9q-EOZGRREV8kr104kL-Hw

ቴሌግራም:-

https://t.me/amharasayintcommunication

ኢንስታግራም:-
https://www.instagram.com/amharasayintworedacomm?igsh=dG9zcXprdGFtMGw=

ቲክቶክ:-
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8zZVyEvYbLR&_r=1

ቲውተር:-
https://x.com/AmharaSayintCom?t=RbymDS5h2-YpyQjR9Ykypw&s=09

ዜጎች ድምፅ መስጠት እንዲችሉ ለሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መደበኛ  ስራን በተመለከተ ምን የተመቻቸ ነገር አለ? #የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት፣ በፌዴራል እና በክልሎች ...
28/05/2026

ዜጎች ድምፅ መስጠት እንዲችሉ ለሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም መደበኛ ስራን በተመለከተ ምን የተመቻቸ ነገር አለ?

#የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት፣ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት ዝግ ይሆናሉ።

#የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አያስገድድም።

#የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ያበረታታል።

መረጃው ከደሴ ፋፋ ኤፍ ኤም 96.0 የተወሰደ ነው።

Address

Dessie

Telephone

+251914057840

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Sayint woreda Communication Affairs/አምሐራ ሳይንት ወረዳ ኮሙኒኬሽን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Sayint woreda Communication Affairs/አምሐራ ሳይንት ወረዳ ኮሙኒኬሽን:

Share