South Wollo Zone Prosperity Party Office/የደቡብ ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Dessie
  • South Wollo Zone Prosperity Party Office/የደቡብ ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት

South Wollo Zone Prosperity Party Office/የደቡብ ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት South Wollo PP

በደቡብ ወሎ ዞን የምርጫና የሰላም ማስከበር ተግባራት አፈፃፀም ተገመገመ፤ ለቀጣይ የልማትና መልካም አስተዳደር ሥራዎችም አቅጣጫ ተቀመጠየደቡብ ወሎ ዞን የምርጫና የሰላም ማስከበር ተግባራት አ...
03/06/2026

በደቡብ ወሎ ዞን የምርጫና የሰላም ማስከበር ተግባራት አፈፃፀም ተገመገመ፤ ለቀጣይ የልማትና መልካም አስተዳደር ሥራዎችም አቅጣጫ ተቀመጠ

የደቡብ ወሎ ዞን የምርጫና የሰላም ማስከበር ተግባራት አፈፃፀምን የሚገመግም የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች መድረክ በደሴ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ በዞኑ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ በአቶ መሐመድ አሊ የቀረበውን ዝርዝር የአፈጻጸም ሪፖርት መነሻ በማድረግ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

እጅግ ስኬታማ ምርጫ መፈጸሙ ተነስቷል። በየደረጃው ያለ አመራር፣ የፀጥታ ኃይልና ሕዝቡ ለስኬቱ የነቃና የላቀ አበርክቶ ማድረጋቸው በውይይቱ ተረጋግጧል፡

በሂደቱም የተመዘገቡ ጠንካራ ጎኖችና ያጋጠሙ ውስንነቶች በዝርዝር የተለዩ ሲሆን፥ ጉድለቶችን በአስቸኳይ በማረም የተጀመሩ መልካም ተሞክሮዎችን በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል መግባባት ላይ ተደርሷል።

ዘላቂ ሰላምን የማረጋገጥና የሕግ የበላይነትን የማስከበር ሥራ ለአጠቃላይ ዕድገት ወሳኝ መሆኑ በመድረኩ የተሰመረበት ሲሆን፥ በቀጣይም የሰላም ሥራዎችን በቁርጠኝነት ከመስራት በተጓዳኝ የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በላቀ ውጤታማነት ለማከናወን የሚያስችል ስልታዊ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በዚህ ወሳኝ የውይይት መድረክ ላይ የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን፣ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግስቱ እንዲሁም ሌሎች የክልሉና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው የጋራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

03/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አለን - የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ የተሰማውን ደስታ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ገልጿል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የፀጥታ ኃይል አካላት እንዲሁም ሕዝቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሙሉ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ለተወጡት ሀገራዊ ኃላፊነት እና ላሳዩት ፅናትም ምክር ቤቱ ያለውን ምስጋና እና አድናቆት ገልጿል።

ምክር ቤቱ በመግለጫው፣ “ልዩነቶቻችንን እና ችግሮቻችንን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመፈታት በምርጫው የታየውን ሰላም በማስቀጠል የበኩላችንን ሚና እንወጣ፤ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ እንቁም” ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

"ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ  ሕዝባዊ ሉዓላዊነት  በተግባር የታየበት ነው" አቶ አሊ መኮንንየደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን በመላ ሕዝቡ ንቁ ተሳትፎ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ምር...
03/06/2026

"ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ሕዝባዊ ሉዓላዊነት በተግባር የታየበት ነው" አቶ አሊ መኮንን

የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን በመላ ሕዝቡ ንቁ ተሳትፎ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መካሄዱን ገልጸዋል።

ባለፈው ግንቦት 24 ቀን ኢትዮጵያ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውንና ታሪካዊ የተባለለትን ሰባተኛ ሀገራዊ ምርጫ በስኬት አስተናግዳለች፡፡ ይህ ምርጫ የሀገሪቱን የዴሞክራሲ ጉዞ አንድ እርምጃ ወደፊት ያሻገረ ከመሆኑም በላይ፣ በሕዝብና በመንግስት በኩል የተጣለውን ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ የመሆን ግብ ያሳካ ትልቅ ኩነት ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

የደቡብ ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን እንደገለጹት፣ ምርጫው ያለምንም የፀጥታና የፍትሐዊነት መጓደል በስኬት እንዲጠናቀቅ እንደ መንግስትም ሆነ እንደ ገዥ ፓርቲ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በልዩ ትኩረት ሲከወኑ ቆይተዋል፡፡

በጥንቃቄና በንቃት ሲከናወን በነበረው የቅድመ ምርጫ መርሃ ግብር ላይ በስፋት ሲሳተፍ የነበረው የዞኑ ማኅበረሰብ፣ በምርጫው ዕለት ያሳየው ቁርጠኝነት እጅግ የሚያስደንቅ ነበር ብለዋል፡፡

መራጩ ሕዝብ ማለዳ ጀምሮ እስከ ዕኩለ ለሊት ድረስ የጠዋቱን ብርድ፣ የቀኑን ፀሐይና የሌሊቱን ጨለማ ሳይበግረው በረጅም ሰልፎች በትዕግስት ጠብቋል፡፡

ይህ የሕዝብ መስዋዕትነት ተራ የመምረጥ ሂደት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን የሀገረ መንግስት ግንባታ ሒደት በፅኑ መሠረት ላይ ለመጣል የተደረገ ታሪካዊ አሻራ ነው ሲሉም አቶ አሊ አብራርተዋል፡፡

"ሀገር መንግስት አልባ እንድትሆን የሚሹ ፀረ-ሰላም ኃይሎች የፈጠሩት ውዥንብርና ትንኮሳ በሕዝቡ ፅናት የእንቧይ ካብ ሆኗል፡፡"

ጥቂት የዞኑ አካባቢዎች የሕዝብን የዴሞክራሲያዊ መብት አጠቃቀም ለማስተጓጎልና ሀገሪቱን ወደ ቀውስ ለመክተት የሞከሩ የውስጥና የውጭ ፀረ-ሰላም ኃይሎች ነበሩ፡፡ ይሁን እንጂ የደቡብ ወሎ ሕዝብ በእነዚህ ትንኮሳዎች ሳይደናገጥ፣ በሰከነና በበሰለ መንገድ ድምጹን ሰጥቷል፡፡

ዕድሜያቸው ለመምረጥ የደረሰና የድምፅ መስጫ ካርድ ያወጡ ዜጎች በሙሉ ያሳዩት ንቁ ተሳትፎ "ባዳና ባንዳዎችን አንገት ያስደፋ" ትልቅ የፖለቲካ ትምህርት የሰጠ እንደነበር አቶ አሊ አክለው ገልጸዋል፡፡

ይህ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በተግባር ያረጋገጠው አንድ ትልቅ እውነት አለ፦ የመንግስታዊ ስልጣን ምንጭና ባለቤቱ የሀገሪቱ ሉዓላዊ ሕዝብ ብቻ መሆኑን ነው፡፡ ማኅበረሰቡ ለሰላም፣ ለነጻነትና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የማይከፍለው መስዋዕትነት እንደሌለ በተግባር አሳይቷል፡፡ ስልጣንን በኃይል ወይም በሴራ ሳይሆን በሕዝብ የድምፅ ካርድ ብቻ መያዝ እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ ተሰጥቶበታል፡፡

ለዚህ ታሪካዊ ስኬት መገኘት የሁለት አካላት ጥምረትና አበርክቶ በእጅጉ የላቀ እንደነበር የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አብራርተዋል፦

የደቡብ ወሎ ሕዝብ የታገሰ፣ በነቂስ የወጣ፣ በሰላማዊ መንገድ ድምፁን የሰጠ እና የዴሞክራሲ ባለቤትነቱን ያረጋገጠ፡፡
ጥምር የፀጥታ ኃይሉ ማናቸውንም የጸረ-ሰላም ኃይሎች ትንኮሳ በንቃት በመከላከል፣ የምርጫ ጣቢያዎችንና መራጮችን ደህንነት ያስጠበቀ እንደነበረም፣ አመልክተዋል፡፡

በአጠቃላይ የሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በደቡብ ወሎ ዞን በታላቅ ስኬት መጠናቀቅ የሕዝብን አሸናፊነትና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ያደመቀ ክስተት ነው፡፡ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ መኮንን መልዕክታቸውን ሲያጠቃልሉ፤ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ስኬት ሌሊት ከቀን ለደከመው መላው የዞኑ ሕዝብና ለአስተማማኙ የጥምር ፀጥታ ኃይል ያላቸውን የላቀ ምስጋና እና ክብር በድጋሚ ገልጸዋል፡፡

03/06/2026
03/06/2026
03/06/2026
ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ መርጣለች! ሀገራችን ባከናወነችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ረዣዥም የመራጮች ሰልፍ መስተዋሉ፣ ዜጎች በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳታፊ ስለ...
03/06/2026

ኢትዮጵያ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ መርጣለች!

ሀገራችን ባከናወነችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ረዣዥም የመራጮች ሰልፍ መስተዋሉ፣ ዜጎች በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳታፊ ስለመሆናቸው ጉልህ ማሳያ ነው።

የዕድሜ መግፋት ፣ የጤና ሁኔታ መታወክ፣ አራስነት፣ ከቤት መቆየትን የግድ ያለው አሰገዳጅ ክስተት ሳይበግራቸው ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ይበጀኛል ያሉትን መርጠዋል።

አንድ ድምፅ ዋጋ እንዳለው በመረዳት ከሌሊት እስከ ሌሊት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

በምርጫው ዕለት የታዩ ረዣዥም የመራጮች ሰልፎች የሕዝብ የፖለቲካ ፍላጎት እና የዴሞክራሲ ተሳትፎ መጉላትን የሚያሳዩ ናቸው።

03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረትና አጋር ሀገራት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሒደት አደነቁ

የአውሮፓ ኅብረት እና አጋር ሀገራት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አድንቋል፡፡

ምርጫውን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ የኅብረቱ አባል ሀገራትና በኢትዮጵያ የካናዳ፣ የኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ ኤምባሲዎች የጋራ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ሀገራቱ በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ እጩዎችና የሲቪል ተቋማት ጠቅላላ ምርጫው በስኬት እንዲካሄድ ያደረጉትን አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት እና የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) በምርጫው ላይ ለነበራቸው የታዛቢነት ሚና እውቅና እንደሚሰጡም ሀገራቱ አረጋግጠዋል፡፡

Address

Dessie

Telephone

+251911875396

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Wollo Zone Prosperity Party Office/የደቡብ ወሎ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share