south wollo zone women child and social affair

28/05/2026

የአካል ጉዳተኞችንና አረጋውያንን መብትና ደህንነት በማስጠበቅ ፤ ሁለንተናዊ ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት የማረጋገጥ የ5 አመት ጉዞ!

የአማራ ክልል ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከአጋር መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት፣ የአካል ጉዳተኞች እና የአረጋውያንን መብትና ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ባለፉት 5 ዓመታት አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግቧል።

ባለፉት አምስት ዓመታት በተቀናጀ ጥረት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት እና የተገኙ አውጤቶች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡-

⚖️ የመብት ማስከበር ስራዎች

የዜጎቻችንን ሰብአዊና ማህበራዊ መብቶች ከማስከበር አንጻር ጥሰት የደረሰባቸውን ወገኖች በመለየት የህግና የጥበቃ ስራዎች ተከናውነዋል፡-
3,054 (1,704 ሴት) አረጋዊያን የደረሰባቸው የመብት ጥሰት ተለይቶ የማስከበር ስራ ተሰርቷል።

2,187 (1,155 ሴት) አካል ጉዳተኞች የደረሰባቸው የመብት ጥሰት ተለይቶ የማስከበር ስራ ተሰርቷል።

🤝 የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ድጋፎች

ለአካል ጉዳተኞችና አረጋውያን ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በርካታ ሁለገብ ድጋፎች ተደራሽ ሆነዋል፡-

የአካል ጉዳተኞች ተሃድሶና የስነ-ልቦና ድጋፍ፦

ለ38,130 (13,012 ሴት) አካል ጉዳተኞች የአካላዊ ተሃድሶ ድጋፍ፣

ለ162,319 (95,615 ሴት) አካል ጉዳተኞች የማህበራዊ ተሃድሶ ድጋፍ፣

ለ31,281 (16,319 ሴት) አካል ጉዳተኞች የስነ-ልቦና ድጋፍ ተሰጥቷል።

የአረጋውያን ድጋፍ፦

ለ556,688 አረጋውያን ልዩ ልዩ ቋሚና ጊዜያዊ የማህበራዊ ድጋፎች ተመቻችቶላቸዋል።

🏡 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እና ሰብዓዊ ድጋፍ

የህዝባችንን የመረዳዳት እሴት በመጠቀም በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ታላላቅ ስራዎች ተከናውነዋል፡-

ከ7,740,951 በላይ የተቋማችን ደንበኞችን (ሴቶች፣ ህጻናት፣ አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞችን) በማሳተፍ ከ397,866,084 ብር በላይ ማሰባሰብ ተችሏል።

ከ33,923 ለሚበልጡ አቅመ ደካሞች አዲስ ቤት የመገንባት እና የማደስ ስራ ተሰርቷል።

ለ505,351 ለሚደርሱ አቅመ ደካሞች ልዩ ልዩ ጊዜያዊ ሰብዓዊ ድጋፎች ተመቻችተዋል።

በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ውጤቶች የጋራ ጥረታችን ፍሬዎች ቢሆኑም፣ እነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎች ካለባቸው ውስብስብ፣ ስር የሰደዱና ዘርፈ ብዙ ችግሮች አንጻር ገና ብዙ ሊሰሩ የሚገቡ ሰፊ ስራዎች መኖራቸውን ቢሯችን በሚገባ ይገነዘባል።

የአረጋውያንንና የአካል ጉዳተኞችን ዘላቂ ተጠቃሚነት ሙሉ በሙሉ ለማረጋገጥ አሁንም ሰፊ ርብርብ ይጠይቃል።

በመሆኑም በቀጣይም ከተለያዩ መንግስታዊ፣ መንግስታዊ ካልሆኑና ከአለም አቀፍ አጋር አካላት ጋር ያለንን ቅንጅት ይበልጥ በማጠናከር፣ ችግሮቹን በዘላቂነት ለመቅረፍ እና ሁለንተናዊ ተሳትፏቸውን ለማረጋገጥ በትጋት መስራታችንን እንቀጥላለን።

ልዩ ትኩረት ለአረጋዊያን እና ለአካል ጉዳተኞች

25/05/2026

ድምጽ ለመስጠት 8 ቀናት ብቻ ቀሩት ! ተዘጋጅተዋል?
"ይበጀናል" ለምንለው ድምፃችንን በመስጠት የዜግነት አሻራችንን እናኑር!

የኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር

23/05/2026

Good family, good generation, for a strong country!

The International Family Day Regional Celebration of the Women's Youth and Social Affairs Office in Ethiopia for the 34th time is being celebrated globally.Good family, good generation, strong country! under the motto, is celebrating in various programs at Bahadar City.

We will be bringing you more information.

May 15/2 025 ec

22/05/2026

ምክንያታዊነት በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ሂደት.......
+++
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በተቋቋመበት የመመስረቻ አዋጅ ላይ ምክንያታዊነት ከሀገራዊ ምክክሩ መርሆዎች አንዱ ተደርጎ መደንገጉ ይታወቃል። ይህ ፅንሰ-ሀሳብ በምክክር ሂደት ውስጥ በምን መንገድ እየተተገበረ እንዳለ ማወቁ እጅግ አስፈላጊ ነው።

በሀገራዊ ምክክር ዓውድ ውስጥ ምክንያታዊነት ከስሜታዊነት፣ ከጥላቻና ከሃሳብ ግትርነት የፀዳ፣ በአንፃሩ አመክንዮንና ማስረጃን መሰረት ያደረጉ ውይይቶችን ለማድረግና ውሳኔዎችን ለማሳለፍ የሚያግዝ ቁልፍ የሥነ-ምግባር መርህ ነው።

ይህም ዜጎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ የጋራ መፍትሔን ለመፈለግ የሚያደርጉትን በጎ ጥረት ያጠናክራል።

ይህንን መነሻ በማድረግ ምክንያታዊነት በሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ እንዴት ተፈፃሚ እንደሚሆን የሚከተሉት ሀሳቦች በዝርዝር ያብራራሉ፤

👉 አመክንዮንና ማስረጃን መሰረት በማድረግ

በዚህ ሂደት ዜጎችና ባለድርሻ አካላት ከስሜታዊነትና ከጥላቻ በፀዳ አኳኋን በውይይቶች ላይ ንቁ ተሳትፎ ያደርጋሉ። ይህም የምክክሩ ዓውድ ሙሉ በሙሉ ሰላማዊ እንዲሆን የማድረግ ከፍተኛ አቅም አለው።

👉 ገለልተኝነትንና ፍትሃዊነትን መሰረት በማድረግ

ምክንያታዊ የሆነ የሀገራዊ ምክክር ሂደት ሚዛናዊ የሆኑ ውይይቶች እንዲደረጉ ከማገዙም በላይ፣ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ድምፆቻቸው በእኩልነት ያለ አድልዎ እንዲሰሙ ትልቅ በር ከፋች ነው።

👉 በሰው ልጆች እኩልነት ማመንን በማበረታታት

በሀገራችን የሚደረጉ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ዜጎች በጋራ ችግሮቻቸው ላይ በግልጽ የሚወያዩባቸው በመሆናቸው፣ የሰዎችን እኩልነት እና ተፈጥሯዊ ማንነት በተገቢው መንገድ በማክበር እየተከናወኑ ይገኛሉ።

22/05/2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአንዳንድ ቃላት
ትርጓሜ

👉 “ቦርድ” ማለት በዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 መልሶ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው፡፡

👉 “ምርጫ” ማለት በፌዴራል እና በክልል ሕገ መንግሥታት እንዲሁም በሌሎች አግባብ ባላቸው ሕጎች መሠረት የሚካሄድ የጠቅላላ፣ የአካባቢ፣ የማሟያ ወይም የድጋሚ ምርጫ ነው፡፡

👉 “ጠቅላላ ምርጫ” ማለት አግባብ ባለው ሕግ መሠረት የሚካሄድ የሕዝብ ተወካዮች እና የክልል ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ነው፡፡

👉 “የአካባቢ ምርጫ” ማለት አግባብ ባለው ሕግ መሠረት የሚካሄድ የብሔረሰብ ዞን፣ የዞን፣ የወረዳ፣ የከተማ፣ የክፍለ ከተማ ወይም የቀበሌ ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ነው፡፡

👉 “ማሟያ ምርጫ” ማለት በመራጮች ውሳኔ ከምክር ቤት መነሳትን ጨምሮ በማንኛውም ምክንያት በየደረጃው የሚገኙ የተጓደሉ የምክር ቤት አባላት መቀመጫዎችን ለመሙላት የሚካሄድ ምርጫ ነው፡፡

👉 “ድጋሚ ምርጫ” ማለት በዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 አንቀጽ 7(16) በተሰጠው ሥልጣን መሰረት ቦርዱ የምርጫ ውጤቱ እንዲሰረዝ ሲወስን፤ በዚህ ዐዋጅ አንቀጽ 154 መሠረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ ሲወስን፤ ወይም ዕጩ ተወዳዳሪዎች እኩል ድምጽ በማግኘታቸው ምክንያት አሸናፊውን ለመለየት የሚካሄድ ምርጫ ነው፡፡

👉 “ሕዝበ ውሣኔ” ማለት በኤ.ፌ.ደ.ሪ ሕገ መንግሥት ወይም አግባብ ባላቸው ሕጎች መሠረት ሲወሰን የሕዝብ ፍላጎት ለመለካት ወይም የሕዝብን ውሳኔ ለማወቅ የሚደረግ የድምጽ አሰጣጥ ሥርዓት ነው፡፡

ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

በጃማ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት  በአስተዳደር ፑል ስር የተገነባው የህጻናት ማቆያ ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ።በጃማ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በአስተዳደር ፑ...
21/05/2026

በጃማ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በአስተዳደር ፑል ስር የተገነባው የህጻናት ማቆያ ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ።

በጃማ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት በአስተዳደር ፑል ስር የተገነባው የህጻናት ማቆያ ግንባታ ተጠናቆ ተመርቋል።

በምርቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጃማ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ለወጠኝ ፀጋው ሴት የመንግስት ሰራተኞች ልጆቻቸውን በቅርብ ሆነው እንድንከባከቡ የህጻናት ማቆያ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው ፥ ለህጻናት ማቆያ የሚያስፈልጉ ግብአቶችን በማሟላት በአስተዳደር ፑል ስር ለሚገኙ ሴት የመንግስት ሰራተኞች የህጻናት ማቆያ መስራት መቻሉን ገልጸዋል።

የህጻናት ማቆያው ሴት የመንግስት ሰራተኞች ልጆቻቸውን በቅርብ በመንከባከብ ስራቸውን በአግባቡ እንድያከናውኑ የሚያግዝ መሆኑንም ተናግረዋል።

የጃማ ወረዳ ሴቶች ወጣቶች ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ወይንሸት ሰይድ በአስተዳደር ፑል ስር ለሚገኙ ሴት የመንግስት ሰራተኞች የህጻናት ማቆያ ግንባታ፣ የሚያስፈልጉ ግብአቶችና የሰው ሀይል በማሟላት አገልግሎት ለማስጀመር መመረቁን ገልጸዋል።

በቀጣይም በየ ፑሉ የህጻናት ማቆያ ግንባታ የማስፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ወ/ሮ ወይንሸት ገልጸው ፥ ሴት የመንግስት ሰራተኞች ስራቸውን በአግባቡ እንድወጡ የህጻናት ማቆያው ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር በመሆኑ ዕድሉን ሊጠቀሙ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የወረዳው የዞን ደጋፊ አቶ አብርሃም አሊ የህጻናት ማቆያ አንዱ የብልጽግና ፓርቲ ኤንሸቲቭ በመሆኑ ተግባሩን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል።

ሴት የመንግስት ሰራተኞች የተሰጣቸውን የስራ ኃላፊነት በስኬት እንድያከናውኑ በአቅራቢያቸው የህጻናት ማቆያ ያስፈልጋል በማለት ለዚህም ወረዳው የጀመረው ተግባር የሚበረታታ መሆኑን አቶ አብርሃም ገልጸዋል።

*****

11/05/2026

ወጣቶች ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንዲካሄድ ንቁ ተሳትፎ ሊያደርጉ ይገባል።

ምርጫ ዜጎች በሀገራቸው የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ የሚወስኑበት ዴሞክራሲያዊ ሂደት ነው። ወጣቶች ደግሞ የዚህ ሂደት ንቁ እና ወሳኝ ተዋናይ ናቸው።

ወጣቶች የሰላም አምባሳደር በመኾን በሂደቱ ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለባቸው ይገለጻል። ምርጫው ነፃ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና አሳታፊ እንዲኾን የበኩላቸውን አስተዋፅዖ እንዲያበረክቱም ይጠበቃል።

​የባሕርዳር ከተማ አሥተዳደር ወጣቶች ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ ስኬት እና ለዘላቂ ሰላም እየሠሩ መኾናቸውን ለአሚኮ ዲጅታል ሚዲያ ተናግረዋል።

ወጣት ቤተልሄም ቦሩ እንደገለጸችው ማኅበረሰቡ በዕውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ምርጫውን እንዲያካሂድ ወጣቶች ኀላፊነታቸውን እየተወጡ ነው። የምርጫ ካርድ ከማውጣት ባለፈ በአካባቢያቸው ሰላምን የማስከበር፣ በአላስፈላጊ ወሬዎች አለመደናገር እና በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሠረተ የምርጫ ሥርዓት እንዲከናወን የመሥራት ኀላፊነት የወጣቶች ነው ብላለች።

ወጣቶች በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎችን በመከላከል ረገድ በንቃት በመሳተፍ ጥረት እያደረጉ ነው። ማኅበረሰቡ የምርጫ ካርድ እንዲያወጣ እና የአካባቢው ሰላም እንዲጠበቅ በቅንጅት እየሠሩ መኾናቸውን ገልጻለች።

​ ወጣት ሀብተማርያም የሻምበልም ሕዝቡ ያለምንም ፍርሃት እና ጭንቀት ምርጫውን እንዲያካሂድ አየሠሩ መኾኑን ነግሮናል። በያዙት የምርጫ ካርድ የሚፈልጉትን ፓርቲ እንዲመርጡ ግንዛቤ እየፈጠሩ መኾናቸውንም ገልጿል።

ወጣቶች ምርጫ ካርድ በመያዝ የራሳቸውን ዕድል የመወሰን መብታቸውን በምርጫ ማረጋገጥ ይገባቸዋል ብሏል።

ወጣቶች የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታን ለማጠናከር እና ሀገራዊ ግዴታቸውን ለመወጣት በምርጫ ሂደቶች ላይ በንቃት መሳተፍ ይጠበቅባቸዋል።

በዚህም የለውጥ ባለቤት፣ የሰላም አምባሳደር እና የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ዋልታ በመኾን ሚናቸውን መወጣት እንዳለባቸውም ተናግሯል።
​መጭው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊ እና አሳታፊ ኾኖ እንዲጠናቀቅ ወጣቶች በትጋት መሥራት ይገባቸዋል ነው ያለው።

በላቀ የሕዝብ ተሳትፎ ምርጫው እንዲሳካ በማድረግ ረገድ ወጣቶች በባለቤትነት መንፈስ እና በትጋት መሳተፍ እንዳለባቸውም ተገልጿል።

አሚኮ

ባሕር ዳር: ግንቦት 03/2018 ዓ.ም

05/05/2026

''ኢትዮጵያ በልጆቿ መስዋዕትነት ፀንታ ትኖራለች!”
እንኳን ለ85ኛው የአርበኞች የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!!!!

ፋሺስት ጣሊያን በ1888 ዓ.ም በዓድዋ ጦርነት የደረሰበትን አሳፋሪ ሽንፈት ለመበቀል ከ40 ዓመታት በኋላ ኢትዮጵያን ዳግም ለመውረር ያደረገው ሙከራ በጀግኖች አርበኞች ተጋድሎ ከሽፏል።

ሞሶሎኒ በአፍሪካ ስትራቴጂካዊ ስፍራ ላይ የምትገኘውን ኢትዮጵያን በመውረር የጣሊያን ቅኝ ግዛት አካል ለማድረግና የራሱን ስምም ለማደስ ከፍተኛ ዝግጅት አድርጎ ነበር።

ለዚህም ከ300 ሺህ ያላነሱ ወታደሮች፣ እስከ 500 የሚደርሱ ተዋጊ አውሮፕላኖችና በመቶዎች የሚቆጠሩ ታንኮችን ቢያሰልፍም፣ ነጻነቷን አስከብራ የኖረችውን ታላቋን አገር ኢትዮጵያን መቆጣጠር ግን አልቻለም።

ጥቂት ሆድ አደሮች ከወራሪው ጋር በማበር የባንዳነት ታሪክ ቢሰሩም፣ አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን በቆራጥነት ለነጻነቱ ተፋልሟል።

ሴት አርበኞች ስንቅ በማዘጋጀትና ግንባር ድረስ በመሳተፍ፣ ሕፃናትም ሳይቀሩ ዕድሜና የአካል ጥንካሬ ሳይገድባቸው ለነጻነታቸው የከፈሉት ዋጋ ምንጊዜም የማይዘነጋ የክብር ታሪክ ነው።

ጣሊያን በቆየባቸው አምስት ዓመታት የኢትዮጵያውያንን የነጻነት ወኔ ለመስበር ትምህርት ቤቶችን ዘግቷል፤ ታዋቂ የሃይማኖት አባቶችን፣ የአገር ሽማግሌዎችንና አርበኞችን በግፍ ጨፍጭፏል።

በተለይም የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም (እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር 1937) በአዲስ አበባ ማርሻል ግራዚያኒን ለመግደል በተደረገ ሙከራ ማግስት የተካሄደው አስከፊ ጭፍጨፋ፣ የሕዝቡን የትግል መንፈስ እንደ ብረት አፅንቶታል።

በንጉሠ ነገሥት አፄ ኃይለስላሴ መሪነት መላው ሕዝብ ያደረገው ተጋድሎ የጣሊያን ቆይታ ከአምስት ዓመት እንዳይዘልና ኢትዮጵያ በሉዓላዊነቷ እንድትቀጥል አድርጓል።

ዛሬም ይህንን የድል በዓል በ2018 ዓ.ም ለ85ኛ ጊዜ“ኢትዮጵያ በልጆቿ መስዋዕትነት ፀንታ ትኖራለች!” በሚል መሪ ቃል እናከብረዋለን።

በዓሉን ስናከብር እንደ አገርም ሆነ እንደ ክልል የባንዳና የባዕዳንን ቅንጅት በመበጣጠስ በማክሸፍ የተፈጠረውን የሰላም እጦት በዘላቂነት በመፍታት፣ የጀመርነውን የልማት ጉዞ አጠናክረን ማስቀጠል ይኖርብናል።

በተጨማሪም ከፊታችን ያለው 7ኛው አገራዊ ምርጫ ፍጹም ሰላማዊና ፍትሃዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ መላው የክልላችን ሕዝብ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የክልሉ መንግሥት ጥሪውን ያስተላልፋል።

ይህ የድል በዓል ለትውልድ አገር ጠባቂነት፣ አይበገሬነትንና ድል አድራጊነትን የምናወርስበት፣ "ኢትዮጵያን ወደተምሳሌት ሀገር" ከፍ ለማድረግ የሚደረገውን የዘመናችንን የአርበኝነት ተጋድሎ በመፈፀም መሆን ይኖርበታል።

ኢትዮጵያ በልጆቿ መስዋዕትነት ፀንታ ትኖራለች!

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ

አማራ ኮሙኒኬሽን

በደቡብ ወሎ ዞን በሴቶች ልማት ኅብረት የተደራጁ ሴቶች በዘጠኝ ወራት ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ ቆጠቡደሴ፤ ሚያዝያ 22 ቀን 2018 ዓ.ም የደቡብ ወሎ ዞን ሴቶች ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ መም...
30/04/2026

በደቡብ ወሎ ዞን በሴቶች ልማት ኅብረት የተደራጁ ሴቶች በዘጠኝ ወራት ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ ቆጠቡ

ደሴ፤ ሚያዝያ 22 ቀን 2018 ዓ.ም

የደቡብ ወሎ ዞን ሴቶች ወጣቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ መምሪያ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙን በደሴ ከተማ ገመገመ።

በመድረኩ ላይ ሴቶችን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግና የቁጠባ ባህልን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት በዝርዝር ቀርበዋል።

የመምሪያው ኃላፊ ቤተልሔም ብርሃኑ እንደገለጹት፤ ሴቶች በኢኮኖሚ ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ በተከናወነ ሰፊ ተግባር 65 ሺህ 328 ሴቶችን በአዲስ በተደራጁ 2 ሺህ 209 የሴቶች የልማት ኅብረቶች ውስጥ ማደራጀት ተችሏል።

በዚህም 55 ቀበሌዎች በሴቶች ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ ጠንካራ አፈጻጸም በማሳየት ሞዴል ሆነው መፈጠራቸውን አስረድተዋል።

የቁጠባ ባህልን ለማጎልበት በተሰራው ሥራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን የጠቀሱት ኃላፊዋ፣ የቁጠባ ዘርፉን በሦስት ምድብ ከፋፍለው አብራርተዋል፡-

በራስ አገዝ ቡድን ደረጃ፦ ከ13 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሴቶች 83 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ መቆጠብ ችለዋል።በልማት ኅብረት ደረጃ፦ ከ33 ሺህ በላይ ሴቶች 21 ሚሊዮን ብር በላይ ቆጥበዋል።በቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበራት፦ ከ27 ሺህ በላይ ሴቶች 19 ሚሊዮን ብር በላይ መቆጠብ ችለዋል።

በአፈጻጸም ረገድ ሐይቅ፣ ከለላ፣ መሐል ሳይንት እና ደላንታ በራስ ገዝ ቡድን ቁጠባ ላይ ምንም ዓይነት አፈጻጸም ያላሳዩ ሲሆን፤ ለጋምቦ፣ መካነ ሰላም፣ ደጎሎ፣ ጅማ፣ ወረኢሉ ከተማ እና አልብኮ ደግሞ ዝቅተኛ አፈጻጸም አስመዝግበዋል። ቀሪዎቹ ወረዳዎች በተሻለ አፈጻጸም ላይ እንደሚገኙ ተመልክቷል።

የሴቶችን ገቢ ለማሳደግ 139 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር አገልግሎት ላይ እንዲውል በማድረግ 7 ሺህ 210 ሴቶች በተለያዩ ገቢ ማስገኛ ተግባራት ተሰማርተው ተጠቃሚ ሆነዋል።

በማኅበረሰብ ድጋፍና እንክብካቤ ጥምረት በኩልም 17 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ተሰብስቦ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች ውሏል። በተጨማሪም 140 አረጋውያን እና 269 አካል ጉዳተኞች በገቢ ማስገኛ ሥራዎች ላይ እንዲሰማሩ ተደርጓል።

ተቋሙ ልዩ ልዩ ኢንሼቲቮችን ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን የጠቀሱት መምሪያ ኃላፊዋ፤ እስካሁን 455 ሺህ 708 ሴቶች እና ከ53 ሺህ በላይ ሕፃናት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመጨረሻም መድረኩ ያለፉትን ዘጠኝ ወራት ጥንካሬዎችና ድክመቶች በመለየት፤ የታዩ ጎደሎዎችን ለመሙላት በቀጣይ ሦስት ወራት በሁሉም ዘርፎች በርብርብ እንዲሠራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።

Address

Dessie
Dessie

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when south wollo zone women child and social affair posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share