17/06/2020
የደሴ ዙሪያ ወረዳ ም/ቤት ጽ/ቤት ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ከቀበሌ ም/ቤት አፈ-ጉባኤ ቋሚ ኮሚቴዎች ስለ መልካም አስተዳደር ልማት እና ስለ ወቅታዊ ሁኔታ ውይይት አደረጉ፡፡
እንደሚታወቀው የምክር ቤት ጉባኤ በወቅቱ ባጋጠመው የኮሮና ቫይረሰ ሳቢያ ጉባኤዎች ተቋርጧል ይሁን እንጅ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዳይከሰቱ የልማት የልማት ስራዎች እንዳይቋረጡ ስራዎች እየተገመገሙ መሄድ የግድ ይላል በመሆኑም የቀበሌ ቋሚ ኮሚቴዎችም ይህን በመገነንዘብ የህዝብ ውክልናቸውን እንዲወጡ ተገለልጻለል፡፡
በተጨማሪም የኮሮና ቫይረስ አገራችን ከገባ ጀምሮ ስርጭቱ እየተፋጠነ በመሆኑና እያደረግን ያለው ጥንቃቄ አናሳ በመሆኑ ቋሚ ኮሚቴው እና አፈ-ጉባኤዎች በቀበሌው ውስጥ ኮማንድ ፖስቱ ጋር በጋራ በመሆን የህብረተሰቡን ግንዛቤ ፈጠራ ስራ በመስራት የሀብት ማፈላለግ ስራ እንዲሰሩ እና ራሳቸውን ብሎም ሀገራቸውን ከኮሮና ቫይረሰ እንዲጠብቁ የግንዛቤ ሰስራ ተሰርቷል፡፡