South Wollo Zone High Court

South Wollo Zone High Court ይህ ገጽ የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህዝብ ግንኙነት ገጽ ነው
(1)

የከላላ ወረዳ ፍ/ቤት ለባህላዊ ፍ/ቤት ሽማግሌዎችና ፀኃፊዎች  የአቅም ማጎልበቻና የስራ ማስጀመሪያ ስልጠና ሰጠ።  ===============//==========ግንቦት 20/2018 ዓ.ም****...
31/05/2026

የከላላ ወረዳ ፍ/ቤት ለባህላዊ ፍ/ቤት ሽማግሌዎችና ፀኃፊዎች የአቅም ማጎልበቻና የስራ ማስጀመሪያ ስልጠና ሰጠ።
===============//==========
ግንቦት 20/2018 ዓ.ም
*********************
የከለላ ወረዳ ፍ/ቤት ከከለላ ወረዳ አስ/ር፣ ከከለላ ከተማ አስ/ር ፣ከከለላ ወረዳ መሬት ጽ/ ቤት ጋር በመተባበር በከለላ ከተማ እና በወረዳው ገጠር ቀበሌዎች በሚገኙ #10 ቀበሌዎች የባህላዊ ፍ/ቤት ሽማግሌዎችና ጸሀፊዎች የአቅም ማጎልበቻና የስራ ማስጀመሪያ ስልጠና ሰጥቷል።

የስልጠና መድረኩ የክብር እንግዳ የነበሩት የከለላ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ደምሴ በመክፈቻ ንግግራቸው፤ ይህ ስርዓት መዘርጋቱ በወረዳዉ፣ በከተማአስተዳደሩ ብሎም በሀገር ሰላም፣ደህንነትና መረጋግት እንዲኖር የማይተካ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።አክለውም ማህበረሰቡ ባህሉን፣ወጉንና እሴቱን በማስጠበቅ እንዲኖርና የሚያጋጥሙ አለመግባባቶችን በሽማግሌዎችና ሀይማኖት አባቶች በመፍታት፣የማህበረሰቡን ግንኙነት በማጠናከር ህብረተሱቡ የልማት፤የእርሻ ስራው ላይ እንዳተኩር በማድረግ ለሀገር እድግትና ሰላም መምጣት መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

የከለላ ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ አውነቱ አምባው በበኩላቸው ባስተላለፉት መልዕክት የባህል ፍርድ ቤቶች ከመደበኛው የሕግ ሥርዓት ጎን ለጎን ፍትሕን ተደራሽ በማድረግ ረገድ ያላቸውን የማይተካ ሚና ገልጸዋል።
በህጉ የተቀመጡትን መሰረታዊ መብቶችንና መርሆዎችን በማክበር፡ እውነታው ላይ ለመድረስ እና ጉዳዮችን ለመፍታት ለዘመናት በባህል የዳበረውን ጥበብን መጠቀም ከባህል ፍ/ቤት ሽማግሌዎች የሚጠበቅ መሆኑን አሳስበው፤የተዘጋጀው ሥልጠና ዋና ዓላማም አሠራርን በማዘመን የባህል ዳኝነቶች በሰነድ አያያዝ እና ተግባራትን በዘመናዊና ስልታዊ መልኩ እንዲሰሩ ለማስቻል፤ ከመደበኛው የዳኝነት ስራ ጋር የተናበበና የተቀናጀ ሥራ በመስራት ማኅበረሰቡ በዝቅተኛ ወጭ በአጭር ጊዜ በአቅራቢያው ተደራሽ የሆነ የደኝነት አገልግሎት እንዲያገኝ ማስቻል መሆኑን አብራርተዋል ።

የስልጠናውን ሂደት አስመልክቶም አስተያየታቸውን የሰጡ አጋርአካላት መካከል፡-
✍የከለላ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ኃላፊ ወ/ሮ አለም በበኩላቸው፣የከለላ ወረዳ ፍ/ቤት የባህል ፍርድ ቤቶችን ከማቋቋም ጀምሮ ለማጠናከርና ዓላማውን ከግብ ለማድረስ አብሮ በመስራት ረገድ እስከ አሁን ድረስ ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝና ወደፊትም ድጋፉ ተጠናክሮ እንሚቀጥል አሳስበዋል።

፣ ይህ የሽምግልና ዳኝነት ስራ በማኅበረሰቡ ዘንድ ትልቅ ቦታ እና አመኔታ የሚጣልበት ኃላፊነት በመሆኑ እና በወጣው ህግ ማዕቀፍ መሰረት የሚጠበቅባቸውን ድጋፍ በቀጣይነት እንደሚያደርጉ ለሰልጣኞች አሳስበዋል።

🔹የወረዳው መሬት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ እንድሪስ ሙህዬ በበኩላቸው ይህ አዋጅ የመሬት ግጭቶችን በቀላሉ ለመፍታት፣ሴቶችን፣ህጻናት፣ድጋፍና ትኩረት የሚሹ አካላትንም የመሬት ተጠቃሚ እንድሆን የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል

✔️በስልጠናው መጠናቀቂያም ላይ የሥልጠናው ተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያት አቅርበው ስልጠናውን በሰጡት አሰልጣኝና በፍርድቤቱ ፕሬዘዳንት በጋራ ምላሽና ማብራሪያ የተሰጠባቸውሲሆን፣ሰልጣኞች
በሰጡት አስተያየት፣ የተሰጠው ሥልጠና ግልጽና ከበቂ ማብራሪያ ጋር የተሰጠ መሆኑ የሕግ ግንዛቤያቸውን እንደሚያሳድግላቸው ገልጸዋል።

በመጨረሻም የስልጠና ሰነዱ፣አዋጆችና መመሪያዎች በየቀበሌያቸው እንደሚላክላቸው፣ቢሮና ለስራው አስፈላጊ የሆኑ የቢሮ ግብአቶችን በየቀበሌያቸው ሊቀመንበሮች በኩል ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሆኖ እንደሚያመቻች ቃል የተገባ መሆኑ፣ ምላሽ ተሰጥቶ፣የፍርድ ቤቱ ፕሬዘዳንት ክቡር አቶ እውነቱ አምባው ስልጠናው በስኬት እንዲካሄድ አስተዋፅኦ ያደረጉትን የከለላ ወረዳ አስተዳደር፣ የከለላ ከተማ አስ/ር ፣የከለላ ወረዳ መሬት ጽ/ ቤት ፣የከለላ ወረዳ ግብርና ጽቤት እና የየቀበሌ አስተዳደሪዎች በወረዳ ፍርድ ቤቱ ስም የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበው፡መሰል ድጋፎችና ትብብሮች ስራን በቅንጅት መስራት ወደፊትም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበው የዕለቱ ስልጠና ፕሮግራም በስኬት ተጠናቋል።

የዕለቱን ስልጠና የሰጡት የከለላ ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ የሆኑት ክቡር አቶ ሚካኤል አስራት ናቸው

መሬት የነካ ተግባርጀማ ወረዳ ደጐሎ ለባህል ፍርድ ቤቱ 9 መዝገቦች ተከፍተው ቀርበዋል======//=====የደጎሎ ከተማ አስተዳደር  01 ቀበሌ አማሬ ቁና የባህል ፍ/ቤት በይፋ ስራ ጀመረ። ...
30/05/2026

መሬት የነካ ተግባር
ጀማ ወረዳ ደጐሎ ለባህል ፍርድ ቤቱ 9 መዝገቦች ተከፍተው ቀርበዋል
======//=====
የደጎሎ ከተማ አስተዳደር 01 ቀበሌ አማሬ ቁና የባህል ፍ/ቤት በይፋ ስራ ጀመረ።

ደጎሎ፦ ግንቦት 22 ቀን 2018 /ጃማ ወረዳ ፍርድ ቤት/

የደጎሎ ከተማ አስተዳደር 01 ቀበሌ አማሬ ቁና የባህል ፍርድ ቤት በአዋጅ ከተቋቋሙ የባህል ፍርድ ቤቶች መካከል ሲሆን ፈጻሚ የባህል ሽማግሌዎችን ካስመረጠ እና የበጎ ፈቃደኛ ጸሃፊውን በቋማነት ቀጥሮ የስራ ማስጀመሪያ እና የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ከተሰጠ በኋላ በይፋ በዛሬው ዕለት ስራውን በደጎሎ ከተማ 01 ቀበሌ አደባባይ ላይ በተመረጡት የባህል ሽማግሌዎች ስራውን ጀምሯል።

በዕለቱም ባለጉዳዮች ጉዳያቸውን በአቤቱታ ለባህል ፍርድ ቤቱ አቅርበው በይፋ መዝገቦቹ ተከፍተው ስራ የተጀመረ ሲሆን በዕለቱም 9 መዝገቦች ለስራ ቀርበዋል።

ባህል ፍ/ቤቶች የፍትህ ተደራሽነትን የሚያሰፉ ፣ ክርክሮችን በዝቅተኛ ወጭና በአጭር ጊዜ የሚፈቱ ቀላል ስርዓትን የሚከተሉ ፣ በደልን የሚክሱ ፣ የሽብር ግንኙነትን የሚያክሙ ፣ባህል ፍ/ቤቶች በሰዎች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በማህበረሰቡ ውስጥ በሚኖሩና ተቀባይነት ባላቸው ሽማግሌዎች አማካኝነት እልባት የሚሰጡ በመሆናቸው ቅቡልነታቸው ከፍ ያለ በመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 298/2017 ተደንግጎ እንዲወጣ መደረጉ ይታወሳል።

የአልብኮ ወረዳ ፍ/ቤት በአማራ ክልል የባህል ፍ/ቤቶችን ለመቋቋምና እውቅና ለመሰጠት በወጣው አዋጅ ቁጥር 298/2017 እና ይህንን አዋጅ ለማሰፈፀም በወጣው መመሪያ ቁጥር  23/2018 ላይ...
30/05/2026

የአልብኮ ወረዳ ፍ/ቤት በአማራ ክልል የባህል ፍ/ቤቶችን ለመቋቋምና እውቅና ለመሰጠት በወጣው አዋጅ ቁጥር 298/2017 እና ይህንን አዋጅ ለማሰፈፀም በወጣው መመሪያ ቁጥር 23/2018 ላይ ከወረዳው ከተውጣጡ የባህል ፍ/ቤት ዳኞች ፣ፀሀፊዎች እና የቀበሌ አሰተዳዳሪዎችን ያካተተ ሰልጠና ሰጥቷል።
ሰልጠናው ግንቦት21-22 /2018 ዓ.ም ለሁለት ተከታታይ ቀናት የተሰተጠ ሲሆን የአልብኮ ወረዳ ፍርድ ቤት የፍታብሄር ዳኝነት አገልግሎት ዋና የሰራ ሂደት አሰተባቦሪና ዳኛ የሆኑት አቶ አህመድ ይመር ስልጠናውን ሰጥተዋል ።
የባህል ፍርድ ቤት መቋቋሙ ተደራሸ ፣ቀልጣፋ ፣ውጤታማ እንዲሁም በማህበረሰብ ዘንድ ማህበራዊ ግንኙነትን የሚያሰቀጥል በመሆኑ ትልቅ ሚና እንዳለው እና ተግባር ና ሀላፊነት በማስገንዘብ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄወችም ማብራሪያ እና መልስ በመሰጠት ተጠናቋል።

30/05/2026
30/05/2026
የህግ ውይይት ተካሄደ==============የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች የግንቦት ወር የመጀመሪያ ዙር መደበኛ የህግ ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱም1 በሁከት ይወገድልኝ ክርክር ...
26/05/2026

የህግ ውይይት ተካሄደ
==============
የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች የግንቦት ወር የመጀመሪያ ዙር መደበኛ የህግ ውይይት አካሂደዋል።

በውይይቱም
1 በሁከት ይወገድልኝ ክርክር ላይ የሚቀርቡ ክሶች ይዘትና ባህሪ፤ እንዲሁም በአተገባበር ያለዉ ሂደት
2 ከወንጀል ስነ ስርአት ህግ ጋር በተያያዘ የሚሰተዋሉ የአሰራርና ክፍተቶች ማለትም ፦
*ተከሳሽ በሌለበት የሚወሰንበት ሰርአት እና መዝገቡን የምንከታተልበት አሰራር
*ዐ.ህግ ምስክር በማያቀርብባቸው ከባድ የወንጀል ክሶች በአሰራር የሚያጋጥሙ ችግሮች በሚሉ ጉዳዮች ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ተደርጓል።

መነሻ የመወያያ ጽሑፎች በክቡር ዳኛች ተስፋዬ ከበደ እና ታርቆ ብርሀኑ ቀርቦ የህጉ ይዘት፣ ዓላማ እና በተግባር የሚፈጠሩ የህግ አተገባበር ጉዳዮች በስፋት ተዳሰዋል።

ተሳታፊ ዳኞችም በርዕሱ ላይ ልምዳቸውንና የህግ እይታቸውን በማካፈል ገንቢ ሃሳቦችን አቅርበዋል።

ውይይቱ የህግ ትርጓሜን እና የፍርድ አሰጣጥ ተመሳሳይነትን ለማጠናከር፣ እንዲሁም የዳኝነት ሥራ ጥራትና ቅልጥፍናን ለማሻሻል ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል።

የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት
ግንቦት 18/ 2018 ዓ.ም.

እንኳን ለ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 🌙✨የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፣ ለፍርድ ቤታችን ዳኞችና ሰ...
26/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው ዓመተ ሂጅራ የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 🌙✨

የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፣ ለፍርድ ቤታችን ዳኞችና ሰራተኞች፣ ለፍትህ አካላት እና ለዞናችን ማህበረሰብ በሙሉ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እንዲሆን ይመኛል።

ዒድ ሙባረክ! 🐏🕌
መልካም በዓል!

⚖️ የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት

የተሁለደሬ ወረዳ ፍርድ ቤት በሃይቅ ከተማ አስተዳደር ለተቋቋሙ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች እና ፀሀፊዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ ፤==========//============ግንቦት 17/2018 ዓ.ም...
25/05/2026

የተሁለደሬ ወረዳ ፍርድ ቤት በሃይቅ ከተማ አስተዳደር ለተቋቋሙ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች እና ፀሀፊዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ ፤
==========//============
ግንቦት 17/2018 ዓ.ም (ሀይቅ )
**********************
በሀይቅ ከተማ አስተዳደር ለተቋቋመ የባህል ፍርድ ቤት ዳኞች እና ፀሀፊዎች ከUNDP peace support Facility በተገኘ የበጀት ምንጭ ከግንቦት 17-19/2018 ዓ.ም ለተከታይ ሶስት ቀናት የሚቆይ ስልጠና በዛሬው ቀን ተጀምሯል ።

ስልጠናውን የተሁለደሬ ወረዳ ፍ/ቤት ኘሬዝደንት አቶ ደረጀ ደምሴ የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ያስጀመሩት ሲሆን የተሁለደሬ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ
አህመድ መሀመድ ለተሳታፊዎች መልዕክት አስተላልፈዋል ።

የሀይቅ ከተማ አስተዳደር የሰላምና ደህንነት ጽ/ቤት ኃላፊ ኮማንደር ክንዱ ዓሊ እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።

ስልጠናውን እየሰጡ የሚገኙት የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት ባዘጋጀው የስልጠና ማንዋል መሰረት የተሁለደሬ ወረዳ ፍ/ቤት የፍትሐብሔር ዳኛ የሆኑት አቶ ዑስማን መሀመድ ናቸው ።

የሚሰጠው ስልጠና የአብክመ የባህል ፍርድ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 298/2017 እና ይህን አዋጅ ለማስፈፀም በወጣው መመሪያ ቁጥር 23/2018 ላይ ያተኮረ በመሆኑ ስራቸውን ለመጀመር የሚያስችል በቂ ግብዓት የሚያገኙበት ይሆናል።

Address

Dessi
251

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South Wollo Zone High Court posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to South Wollo Zone High Court:

Share