የአማራ ሕዝባዊ ግንባር - Amhara Popular Front

የአማራ ሕዝባዊ ግንባር - Amhara Popular Front Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from የአማራ ሕዝባዊ ግንባር - Amhara Popular Front, Armed forces, Dejen.

20/03/2024
የጃንደረባው ትውልድ መሪ ለነጻነቱ ለሚዋደቀው የአማራ ፋኖ መካሪ ከሆነው ከመምህር ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ ጎን እንቆማለን።
18/01/2024

የጃንደረባው ትውልድ መሪ ለነጻነቱ ለሚዋደቀው የአማራ ፋኖ መካሪ ከሆነው ከመምህር ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ ጎን እንቆማለን።

10/01/2024

የጎጃም ዕዝ ፋኖ ባወጣው መግለጫ ላይ ያላችሁን አስተያየት አጋሩን።

ሰበር ዜና! ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት ሆነች**************** ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በር ለማግኘት እና ለማልማት የሚያስችላትን ስምምነት ከሶማሊ ላንድ ጋር ፈፅማለች። ጠቅላይ ሚኒስትር...
01/01/2024

ሰበር ዜና!

ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት ሆነች
****************

ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በር ለማግኘት እና ለማልማት የሚያስችላትን ስምምነት ከሶማሊ ላንድ ጋር ፈፅማለች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊ ላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ ባሂ ሁሉን አካታች የሆነውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።

በዚሁ መሠረት ለብዙ ዘመናት ወደብ አልባ ሆና የቆየችው ሀገራችን ከሶማሊ ላንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት በሊዝ የወደብ ባለቤት መሆን ችላለች።

05/08/2023

የአማራ ህዝባዊ ሀይል ፋኖ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ታጋይ አስረስ ማረ ሚሊዮን ጀግኖችን ሚሊዮን አስረሶችን ያፈሩ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ ናቸው።

ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር እና ጋዜጠኛ አዲሱ ደርቤ የአማራ ሕዝባዊ ግንባርን መልእክት በመያዝ ለጊዜው መግለጽ ወደማንፈልገው አገር እንዲጓዙ አድርገናል። የብልጽግና ተከፋዮች ሁለቱን ታጋዮች ...
25/07/2023

ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር እና ጋዜጠኛ አዲሱ ደርቤ የአማራ ሕዝባዊ ግንባርን መልእክት በመያዝ ለጊዜው መግለጽ ወደማንፈልገው አገር እንዲጓዙ አድርገናል። የብልጽግና ተከፋዮች ሁለቱን ታጋዮች ከትግል ሸሹ ፈረጠጡ በሚል በሚነዙት የተጠና ፕሮፓጋንዳ እንዳትታለሉ የአማራ ሕዝባዊ ግንባር ለማሳሰብ ይወዳል።

29/05/2023

ለአርቲስት ሀሊማ አብዱርሃማን የለገስነው 1,000,000 ብር ድጋፍ አነስተኛ ቢሆንም አርቲስቷ ከህመሟ አገግማ ወደ ኢትዮጵያ በመመለሷ በድርጅታችን በ WA ቢዝነስ ኮርፖሬት ስም የተሰማንን ደስታ እንገልጻለን።

WA ቢዝነስ ኮርፖሬት ለአርቲስት ሀሊማ የግል ተሽከርካሪና መኖሪያ ቤት ለመስጠት ወስኗል።

ባለሃብቱ ወርቁ አይተነው ለ JFM ራዲዮ 106.7 ጋዜጠኛ የተናገሩት

21/05/2023

የአማራ ሕዝባዊ ግንባር ተመሥርቷል!

ከአማራ ሕዝባዊ ግንባር የተሰጠ መግለጫ (ግንቦት 12 ቀን 2015 ዓ/ም)

መነሻችን የአማራ ህልውና፣ መዳረሻችን የኢትዮጵያ አንድነት!

በአማራው ሕዝብ ሕልውና እና በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የተደቀነው አደጋ ወደ ከባድ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። በሀሰት ትርክትና በጭፍን ጥላቻ የሚነዳው ጽንፈኛው የኦሮሙማ ፖለቲካ ታላቋን ኦሮሚያ ለመፍጠር ስትራቴጂካዊ ግብ አስቀምጦ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ይገኛል።

ብልፅግና ፓርቲን የተቆጣጠሩት እና በዐብይ አህመድ የሚመሩት አክራሪ የኦሮሞ ብሄርተኞች "ታላቋ" የሚሏትን ኦሮሚያ ለመፍጠር በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈጽሙትን የዘር ፍጅት (ጄኖሳይድ) በማስፋፋት እና አዋሳኝ የሆኑ ክልሎችን ወርረው መሬት ለመቀማት እየተንቀሳቀሱ ነው። በዚህ ሂደት ሰለባ እንዲሆኑ ካሰቧቸው መካከል ከአማራ ክልል በተጨማሪ ሲዳማ፣ አፋር፣ ሱማሌ፣ ቤንሻንጎል፣ ጌዴዮ፣ ጉራጌ፣ ጋሞ፣ ድሬዳዋ እና አዲስ አበባ ይገኙበታል። "አገረ ኦሮሚያ የባህር በር ያስፈልጋታል" ብለው ስላመኑም፣ የሶማሌ ክልልን ለሁለት ቆርጠው ወደ ቀይ ባህር ለመዝለቅ ዕቅድ አዘጋጅተዋል። አዲሲቷ ኦሮሚያ ከሌላ ብሔሮች የጸዳች ብቻ ሳትሆን፣ ከኦርቶዶክስ እምነትና ከነባሩ እስልምና የጸዳችም እንድትሆን አልመው በመስራት ላይ መሆናቸው ፀሐይ የሞቀው ሃቅ ነው።

ባለፉት አምስት ዓመታት በተበታተነ መልኩም ቢሆንም ውጥናቸውን ተግባራዊ ለማድረግ በተደረገ እንቅስቃሴ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አማራዎች በኦሮሚያ ክልል የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ የመፈናቀል እና የጅምላ ግድያ ሰለባ ሆነዋል። በሀገራችን ላይ ያንዣበበው አደጋ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ እነዚህ ተጨባጭ ማስረጃዎች ናቸው። ሁኔታዎች በዚሁ ከቀጠሉም የወደፊት እጣ ፈንታችን ከሩዋንዳ የዘር እልቂት የከፋ እንደሚሆን በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል።

ይህንን በመላው ኢትዮጵያ፣ በተለይም የውጥኑ ዋና እንቅፋት ይሆናል ተብሎ በተሰጋውና የዘር-ፍጅት (ጄኖሳይድ) በታወጀበት የአማራ ሕዝብ ላይ የተነሳውን ከባድ አደጋ ለመቀልበስ የሚያስችል ሀገራዊ እና ሕዝባዊ ትግል የመጀመሪያ ምዕራፍ የሚያቀናጅ የአማራ ሕዝባዊ ግንባር (Amhara Popular Front) ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

የግንባሩ ዓላማ:-
1. የአማራ ሕዝብ ራሱን ከጅምላ ፍጅት (ጄኖሳይድ) ለመከላከል የሚያደርገውን የህልውና ትግል ቀዳሚ መነሻ ማድረግ፤

2. የአማራ ሕዝብ የህልውና ማስጠበቅ ትግል መዳረሻው የኢትዮጵያን እንደሃገር ለሚቀጥለው ትውልድ ማስተላለፍ፤

3. ለአማራ ሕዝብም ሆነ ለኢትዮጵያ የህልውና ስጋት የሆነውን ህገ-መንግስት ለኢትዮጵያ ሕዝብ አብሮነት ዋስትና በሚሰጥ መንገድ እንዲሻሻል ማድረግ፤

4. በሕዝባዊ ትግል ነፃ በሚወጡና የብልፅግና ፓርቲ አስተዳደር በሚፈረሰባቸው ቦታዎች ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከፋኖ እና የሕዝቡን ትግል ከተቀላቀሉ የመንግሥት ሹማምንት በተውጣጡ አካላት የአካባቢ አሥተዳደሮችን መመሥረት፤

5. በሚቋቋሙት የአካባቢ አሥተዳደሮች አማካኝነት የሕዝብን ሠላም፣ ዲሞክራሲያዊ መብቶችና ፀጥታ ማስጠበቅ፤

6. በአማራ ሕዝብ ላይ ያንዣበበውን የጅምላ የዘር ፍጅት (ጄኖሳይድ) እና የሀገር ብተናን አደጋ ለመግታት ከሚንቀሳቀሱ ሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ኃይሎች ጋር ተባብሮ መስራት ናቸው።
በአብይ አህመድ የሚመራው የብልፅግና ፓርቲ ብቃት እና ሕዝባዊ መሠረት የሌለው፣ ከእውቀት የፀዳ፣ በጥላቻ የተመረዘ፣ ለሰው ልጅ ክብር የሌለው እና ሙሰኛ ድርጅት ነው። ህወሓት-መራሽ በሆነው የኢህአዴግ ዘመን የነበረውን ሥርዓት በከፋ ሁኔታ አጠናክሮ አስቀጠለው እንጂ አለወጠውም።

21/05/2023

ትክክለኛው የአማራ ሕዝባዊ ግንባር ገጽ ይሄ ነው።

Address

Dejen

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአማራ ሕዝባዊ ግንባር - Amhara Popular Front posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category