Dejen Woreda Culture and Tourism Office

Dejen Woreda Culture and Tourism Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Dejen Woreda Culture and Tourism Office, Government Building, Dejen.

27/10/2025

የአለም ቱሪዝም ቀን
የዓለም ቱሪዝም ድርጅት (UNWT) በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በ1963ዓ. ም ተቋቁሟል፡፡ በየዓመቱ መስከረም 17 በዓለም አቀፍ ደረጃ የዓለም የቱሪዝም ድርጅት (UNWT) በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተቋቋመበት ቀን “የቱሪዝም ቀን” ተብሎ ስያሜውን በመያዝ እንዲከበር መወሰኑ ይታወቃል።
በዓሉ ሀገራት ለቱሪዝም ዘርፍ ተገቢውን ትኩረት በመስጠት ቱሪዝም በሚያስገኘው ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ አስተዋፅኦ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የማነሳሳት እና ግንዛቤ የመፍጠር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተነስቷል።
ሀገራችን ኢትዮጵያ የራሷ የሆነ አኩሪ ባህል፣ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ቅርሶች መገኛ ናት ያሉንን ቅርሶች መጠበቅ ፣ በማስተዋወቅ ከዘርፉ የሚገኛውን ሀብት ተጠቃሚ ለመሆን መስራትን ይጠይቃል፡፡

ከትኩረት ማነስ የተነሳ የቱሪዝም ፀጋዎቻችን በአግባቡ አልተጠቀምንም በቀጣይ አልሚዎችን በማፈላለግ እና እኛም አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ከቱሪዝም ዘርፎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለመሆን መስራትን ይጠይቃል፡፡
የዓለም የቱሪዝም ቀን በየዓመቱ የሚከበር በዓል ሲሆን በዓሉን ለማክበር የዓለም የቱሪዝም ድርጅት በየዓመቱ ለበዓሉ የሚሆን መሪ ቃል ያዘጋጃል፡፡ የቱሪዝም ቀን በዓል በየዓመቱ በእኛ አቆጣጠር መስከረም 17/በፈረንጆች አቆጣጠር መስከረም 27 የሚከበር ሲሆን ቀኑ የተመረጠበት ምክንያትም የአለም የቱሪዝም ድርጅት ህገ ደንብ የፀደቀበት እና ወደስራ የገባበት ቀን በመሆኑ ነው ።
የ2018ዓ.ም የዓለም የቱሪዝም ቀን በዓል "ቱሪዝም ለዘላቂ ለውጥ" (Tourism and Sustainable Transformation) በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ46ኛ፣በሀገራችን ለ38ኛ፣በክልል ደረጃ ለ33 ጊዜ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡
የቱሪዝም ቀንን ማክበር ስለቱሪዝም ግንዛቤ ለመፍጠር ፣የጉብኝት ልምድን ለማስፋፋት እንዲሁም የቱሪዝም መዳረሻዎችን ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል ይፈጥራል ።
 የመስህብ ሀብቶቻችንን መጠበቅ እና መንከባከብ የሁላችንም ሃላፊነት ነዉ
 የቱሪዝም ሀብቶችን በማስተዋወቅ በኩል ማህበራዊ ሚዲያው ሠፊ ዕድል ስለሚሠጠን የመስህብ ሀብቶቻችንን በማስተዋወቅ እና ጎብኝዎችን በመሳብ ሁላችንም የቱሪዝም አምባሳደር መሆን ይገባናል።
 ቱሪዝም ለሀገር እድገት አለኝታ ነዉ፡፡ የመስህብ ሀብቶች የገቢ ምንጮች በመሆናቸው ይዘታዊና ቁሳዊ ባህሪያቸውን ሳይለቁ ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባል፡፡ ያልተመዘገቡና ያልተጠኑ ቅርሶችን እዉቅና ቢሰጣቸው እና ያሉትን እድሳትና ጥገና ቢደረግላቸው መልካም ነዉ፡፡
 ኢትዮጵያ ካላት እምቅ የቱሪዝም አቅምና መዳረሻዎች አንፃር እያገኘቸው ያለው ጥቅም እጅግ አነስተኛ ነው።
 መንግስት ነባራዊ ሁኔታውን ለመቀየርና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ ተገቢውን ድርሻ እንዲይዝ አስቻይ የሪፎርም ሥራዎችን እያከናወነ ነው፡፡
 ከአምስት የኢኮኖሚ አውታሮች አንዱ የሆነውን የቱሪዝምን ዘርፍ በከፍተኛ ትኩረት በመምራት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ስትራቴጂ ቁልፍ አካል እንዲሆን እየተሰራም ነው፡፡
 ቱሪዝም የአድናቆት ገበያ መሆኑን በመገንዘብ የኢትዮጵያን ቱሪዝም ዓለም ዓቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያሳድጉ ሥራዎች እንዲከናወኑ ይፈለጋል፡፡
የቱሪዝም ምንነት፡-
ቱሪዝም
ሁሉም ባለሙያዎች የተስማሙበት በአለም አቀፍ ደረጃ አንድ ወጥ የሆነ ፍች የለውም፡ምክንያቱም የቱሪዝም ትምህርት /discipline/ገና በማደግ ላይ ያለ በመሆኑ ነው፡፡
ይሁን እንጅ አብዛኛዎቹ ባለሙያዎች የተስማሙበትና በስፋት የሚገለገል ከአለም ቱሪዝም ድርጅት የተሰጠ ፅንስ ሃሳብ አለው፡፡
ይኸውም፡- ቱሪዝም ማለት ሰዎች በተናጠል ወይም በቡድን በመሆን ከመኖሪያ ቀያቸው (አካባቢያቸው) ተነስተው ለተለያዩ ጉዳዮች ከአንድ አመት ላልበለጠና ከአንድ ምሽት (24 ስዓት) ላላነሰ ጊዜ ወደ ሌላ ከማንኛውም ገቢ ማስገኛ ስራ ውጭ የእረፍት ጊዜን ለማሳለፍ፣ ለመዝናናት፣ራስን ለማደስ ፣ ለንግድ ስራ ወይንም ለሌላ ተግባር የሚያደርጉት ጉዞ ነው፡፡
ነገርግን ሁሉም ተጓዦች ጎብኝዎች ሊባሉ አይችሉም ጎብኝዎች ለመባል የተለያዩ መስፈርቶች መሟላት አለባቸው ከእነዚህም መስፈርቶች
1.የጉብኝት አላማ ሲኖር /purposive criterion/
2.ጉብኝቱን የሚያደርገው ተጓዠ ከመኖሪያ አካባቢው ርቆ መሄድ እንዳለበትና ከቱሪስት ተቀባይ ወገን የተለያዩ አገልግሎቶች ሲያገኝ/spatial criterion/
3.የጉብኝት የጊዜ ገደብም/Temporal criterion/ መኖር ያለበት ሲሆን ከአንድ ምሽት ማነስ እንደለሌለበትና ከአንድ አመት መብለጥ እንደሌለበት የዓለም የቱሪዝም ድርጅት ያስቀምጣል፡፡ ከአንድ ምሽት ካነሰ ወይም ከአንድ አመት ከበለጠ ግን ቱሪስት ሳይሆኑ ሌላ ስያሜ ሊሰጣቸው ይችላል፡፡
የቱሪዝም አብይ ክፍሎች ወይንም አካላት
የቱሪዝም አብይ ክፍሎችና (አካላት) የሚባሉት፡- መስህብ፣ መጓጓዣና መስተንግዶ ናቸው፡፡
ሀ. መስህብ
መስህብ ማለት በአንድ አካባቢ የሚገኘ ተፈጥሮ ወይም ሰው ሰራሽ ቦታ (ስፍራ) አልያም ደግሞ ድርጊት (ክስተት) ሲሆን ጎብኝዎችን ከመኖሪያ ቦታቸው ቀስቅሶ ወደ ሌላ አካባቢ እንዲጓዙ የሚያደርግ ነገር ነው፡፡ለቱሪዝም ልማት ወሳኝና ያለመስህብ ሃብትም ቱሪዝም አይታሰብም፡፡የመስህብ ሃብት የቱሪስቶችን የመዳረሻ ምርጫ ለመወሰን የሚቻል የቱሪዝም ምርት አካል ነው፡
በአጠቃላይ፡- መስህብ ማለት የጎብኝዎችን ስሜት የሚስብ ተፈጥሮአዊና ባህላዊ ውጤት የሆነ ማንኛውም ነገር ነው፡፡
ለ. መጓጓዣ
መጓጓዣ ከመዳረሻ ቦታው መዳረሻና ከመዳረሻዎች ውስጥ ለውስጥም ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀሻ ዘዴ ነው፡፡ሁኔታውም የአንድ ተጓዥ ቱሪስት ከአንድ ነጥብ ሀ ወደ ሌላ ነጥብ ነጥብ ለ እንቅስቃሴ ላይ ያተኩራል፡፡በአሁኑ ስዓትም መጓጓዝ የመስህብ አካል ሆኖ በመታየት እየጨመረ መጥቷል፡፡
ሐ. መስተንግዶ
በመሰረታዊነት የምግብ፣ የመጠጥና ማረፊያ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ተቋማት ናቸው፡፡
በተጨማሪነት ደግሞ የጉብኝትና ጉዞ፣ የቱሪዝም መረጃ፣ የሱቅና ግላዊ አገልግሎቶች፣ የገንዘብ መለዋወጫና የህክምና አገልግሎቶች፣ የስብሰባ አዳራሽና ወዘተ አገልግሎቶች ይሰጣል፡፡
የቱሪዝም ጥቅሞች፡-
የቱሪዝም ምጣኔ ሃብት በጣም ብዙና በቁጥር ሊተመን የማይቻል ቢሆንም በጥቅሉ ግን እንደሚከተለው ማስቀመጥ ይቻላል፡፡
1. ለምጣኔ ሃብት (ኢኮኖሚ) እድገትና የምጣኔ ሃብትን በማብዛትና በማረጋገት ያግዛል፡፡
2. የስራ ዕድል ፈጠራ፣
3. ፍልሰትን በመቀነስ ሰፈርን መልሶ ይተካል፣
4. የህዝባዊ ተቋማት እንዲጠገኑና እንዲሻሻሉ ያደርጋል፣
5. የመሰረተ ልማት ተቋማትን ያሻሽላል፣
6. ዕደ ጥበባት፣ ልማዶችን፣ ወጎችንና ባህልን ይመልሳል፣
7. ማህበራዊ ግንኙነቶችና ልውውጦች እንዲጨምሩ ዕድል ይፈጥራል፣
8. የተፈጥሮና የህንፃ ግንባታዎች አካባቢ እንዲጠበቁና እንዲሻሻሉ ያደርጋል፣
------------------------------------//--------------------------------
"ቱሪዝም ለዘላቂ ለውጥ" (Tourism and Sustainable Transformation)

በምስራቅ ጎጃም  ዞን በደጀን ከተማ የ2018ዓ.ም የመስቀል በዓል በደመቀና በአማረ መልኩ በርካታ ምእመናን በተገኙበት ተከበረ፡፡በእለቱም ልዩ ልዩ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓቶችና በወጣቶች ባህላዊ...
29/09/2025

በምስራቅ ጎጃም ዞን በደጀን ከተማ የ2018ዓ.ም የመስቀል በዓል በደመቀና በአማረ መልኩ በርካታ ምእመናን በተገኙበት ተከበረ፡፡በእለቱም ልዩ ልዩ ሀይማኖታዊ ስነ ስርዓቶችና በወጣቶች ባህላዊ ጭፈራም ደምቆ በዓሉ ተከብሯል፡፡

እንኳን ለ2018 ዓ.ም የደመራና የመስቀል በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!!የደጀን ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት እንኳን ለ2018 ዓ.ም የደመራና የመስቀል በዓል በሰላም አደረሰን አደረ...
26/09/2025

እንኳን ለ2018 ዓ.ም የደመራና የመስቀል በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!!!
የደጀን ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት እንኳን ለ2018 ዓ.ም የደመራና የመስቀል በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ እያለ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የደስታ እንዲሆንላችሁ ምኞቱን ይገልጻል፡፡!!!
የመስቀል በዓል በኢትዮጵያ እና በሌሎች የክርስትና ዕምነት ተከታይ ሃገራት ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩ ሃይማኖታዊ በዓላት አንዱ ነው፡፡ በዓሉ በየዓመቱ መስከረም 17 ቀን እና መስከረም 16 ቀን የደመራ በዓል ተብሎ ደመራ በመደመር፣ በችቦ ማብራት፣ በካህናት ወረብና ሽብሻቦ፣ በወጣቶች መንፈሳዊና ዓለማዊ ዝማሬ እና ልዩልዩ ፕሮግራሞች በድምቀት ተከብሮ ይውላል፡፡ በዓሉ ዓለማቀፋዊ ዕውቅና አግኝቶም በመንፈሳዊ ቅርስንት ወይም የማይዳሰስ ቅርስ ተብሎ በዓለም አቀፍ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት/UNESCO/ ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ ተመዝግቧል፡፡
የደመራ ትርጉም
ደመራ የሚለው ቃል–ደመረ፣ ጨመረ፣ አንድ አደረገ፤ ከሚለው የግእዝ ቃል የተወረሰ ሲሆን መቀላቀልን፣ መገናኘትን፣ መሰብሰብን፣ መጣመርን፣ መዋሐድን በአጠቃላይ አንድነትን እና ኅብረትን ያመለክታል፡፡ ቅዱስ መስቀሉ በተገኘበት ቦታም ስለሆነም ደመራ እንጨቶች የሚደመሩበት የበዓለ መስቀል ዋዜማ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ከምታከብራቸው ዘጠኙ የጌታችን ንዑሳን በዓላት አንዱ በዓል ነው፡፡ መስቀል የሰላማችንና የድኅነታችን የመቀደሳችን ዓርማ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጆች ለማዳን፥ የዘላለም ሕይወትን ለመስጠት መስዋዕትነት የከፈለበት ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ያፈሰሰበት መንበር ሲሆን አምላካችንን የምንመለከትበት መስታወት ነው። በሀገራችን በኢትዮጵያ የመስቀልን በዓል ደመራ በመደመርና ችቦ በማብራት ቅዳሴ በመቀደስና ማኅሌት በመቆም የምናከብረው ለዚህ ነው። በዚሁም ላይ ይህን ታላቅ ዕፀ መስቀል በወቅቱ የነበሩ ታላላቅ ነገሥታት የሚያደርጓቸውን ተዓምራት በማየት ለእያንዳንዳቸው ይደርሳቸው ዘንድ ከአራት ክፍል ሲከፍሉት ከአራቱ አንዱ የቀኝ እጁ ያረፈበት ግማድ /ክፋይ/ ብቻ በደብረ ከርቤ ግሸን ማርያም ሲገኝ ሌሎች ሦስቱ ግን የት እንደደረሱ አይታወቅም ይላሉ ሊቃውንተ ቤተክርሰቲያንና የሃይማኖት አባቶች።
የመስቀል በዓል ታሪካዊ አመጣጥ
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ለማዳን የተሰቀለበት ቅዱስ መስቀል ሕሙማንን በመፈወሱ ምክንያት በርካታ አህዛብ ክርስቲያን እንዲሆኑ አስችሏል፡፡ በታምራዊነቱና በክርስቲያኖች ዘንድ ከፍተኛ ክብር የተሰጠው በመሆኑና ይህን የተመለከቱ አይሁድ ቅዱስ መስቀሉን በአንድ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ቦታ እንዲቀበር አደረጉ፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች በየቀኑ ቆሻሻ ስለሚጥሉበት ቦታው ወደ ተራራነት ተቀየረ፡፡ ምንም እንኳን መስቀሉን ለማውጣት ባይችሉም በኢየሩሳሌም የነበሩ ክርስቲያኖች ቦታውን ያውቁት ነበር፡፡ በሰባ ዓመተ ምሕረት በጢጦስ ወረራ ኢየሩሳሌም ስለጠፋች በዚያ የነበሩ ክርስቲያኖች ተሰደዱ፡፡ የተቀበረበትን ቦታ የሚያውቅ ባለመገኘቱ መስቀሉ ከ300 ዓመታት በላይ ተዳፍኖ /ተቀብሮ/ ኖረ፡፡
በ326 ዓ.ም. የንጉሥ ቆስጠንጢኖስ እናት ንግሥት ዕሌኒ ቅዱስ መስቀሉን ለመፈለግ ወደ ኢየሩሳሌም ጉዞ አደረገች፡፡ እዚያም ደርሳ ጉብታ የሆነውን ሁሉ ብታስቆፍር መስቀሉ ያለበትን ቦታ ማግኘት አልቻለችም፤ ሰውም ብትጠይቅ የሚያውቅ አልተገኘም፡፡ በመጨረሻም የመስቀሉ መገኘት የእግዚአብሔር ፈቀድ ነበርና አንድ ይሁድ አረጋዊ የታሪክ አዋቂና ሽማግሌ አግኝታ ቅዱስ መስቀሉ የተቀበረበትንና የተጣለበትን አካባቢ ያውቅ ዘንድ ጠየቀችው፡፡ ሽማግሌውም “አንቺም በከንቱ አትድከሚ ሰውንም አታድክሚ እንጨት አሰብስበሽ እጣን አፍሽበት በእሳትም አያይዢው የእጣኑ ጢስ ወደላይ ወጥቶ ወደታች ሲመለስ አቅጣጫውን አይተሽ አስቆፍሪው በዚህ ምልክት ታገኚዋለሽ” አላት እርሷም ያላትን ሁሉ አደረገች። እንጨት ደምራ በዚያ ላይም ዕጣን ጨምራ በእሳት ለኮሰችው፤ የዕጣኑ ጢስ ወደ ላይ ወጥቶ ወደ ታች ሲመለስ መስቀሉ ያለበትን ቦታ በጣት ጠቅሶ እንደማሳየት ያህል አመለከተ፡፡ ንግሥት ዕሌኒም ጢሱ ያረፈበት ቦታ ቅዱስ መስቀሉ የተቀበረበት እንደሆነ አመነች፡፡ ይህ አይሁድ አረጋዊ የታሪክ አዋቂና ሽማግሌ በኋላ በክርስቶስ አምኖ ተጠምቋል ስሙም ኪርያኮስ ተብሏል፡፡
በዚህም መሠረት ከመስከረም 17 ቀን አስጀምራ እስከ መጋቢት 10 ቀን ሌሊትና ቀን ለሰባት ወራት ያህል የጉድፍን ኮረብታ ቆፍረው ቆሻሻውንም ካስወገዱ በኋላ ሦስት መስቀሎች ተገኙ፡፡ የጌታም መስቀል ሙት በማስነሣቱ ተለይቶ ታውቋል፡፡ መስቀሉ የተገኘው መጋቢት 10 ቀን 326 ዓ. ም. ነበር፡፡ ቅድስት ዕሌኒ ይህን ተአምር በማየቷ እጅግ ደስ አላት፡፡ ሕዝቡም ሁሉ መስቀሉን እየዳሰሱ ኪርያላይሶን እያሉም በመዘመር ደስታና ሀሴት አደረጉ፡፡ ቀኑ መሽቶ ጨለማ በሆነ ጊዜም የኢየሩሳሌም ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስና ንግሥት ዕሌኒ፣ ሠራዊቱና ሕዝቡ በሰልፍ በችቦ መብራት መዝሙር እየዘመሩ ቅዱስ መስቀሉን ወደ ቤተ ክርስቲያን ወስደው በአንድ የጸሎት ቤት አኖሩት፡፡ በኋላም በንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ዕብነ መሠረት ወይም የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦ ለመሰቀሉ መታሰቢያ ቤተክርስቲያን ተሠርቶ ተመርቆ የገባው (ቅዳሴ ቤቱ) የተከበረው መስከረም 17 ቀን 327 ዓ.ም. ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ሁለቱም ዕለታት ይከበራሉ፤ በደማቅ ሁኔታና በመጀመሪያ ደረጃ የሚከበረው ግን መስከረም 17 ነው፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት መጋቢት 10 ቀን ሁልጊዜም በዐቢይ ጾም ወቅት የሚውል መሆኑና ለመስቀሉ የተሠራው ቤተ መቅደስ የከበረው መስከረም 17 በመሆኑ ነው፡፡ይህ ዕለት ከ300 ዓመታት በላይ ጠፍቶ የነበረውን ቅዱስ መስቀል በንግሥት ዕሌኒ አማካኝነት መገኘቱን የምንዘክርበት በዚህም ደስ የምንሰኝበት ዕለት ነው፡፡ ይህን መነሻ በማድረግ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ደመራ በመደመር የመስቀል በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዐት ይከበራል፡፡
የ2018ዓ.ም የመስቀል በዓል በደጀን በደማቅና በአማረ ሁኔታ በልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ ስነስርዓት የእምነቱ ተከታዮች(ምዕመናን)እና የሀይማኖት አባቶች በተገኙበት ይከበራል፡፡
በድጋሚ እንኳን ለመስቀል በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል
የደጀን ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት!!!
መስከረም 16/2018 ዓ.ም

Address

Dejen

Telephone

+251587760784

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dejen Woreda Culture and Tourism Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share