Ethiopian AIR FORCE

Ethiopian AIR FORCE የኢትዮጵያ አየር ኃይል የኢትዮጵያ ደጀን

አየር ሀይል በ2030 የአፍሪካ ቁንጮ ለመሆን የሚያስችለውን ሪፎርም በማከናወን ላይ ነው፡፡ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ አየር ኃይል የ90ኛ ዓመት የምሥ...
30/01/2026

አየር ሀይል በ2030 የአፍሪካ ቁንጮ ለመሆን የሚያስችለውን ሪፎርም በማከናወን ላይ ነው፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ አየር ኃይል የ90ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን እያከበረ ይገኛል። ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በታሪኩ ከፍተኛው ደረጃ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ እ.ኤ.አ በ2030 የአፍሪካ ቁንጮ ለመሆን የሚያስችለውን ታሪካዊ ሪፎርም በማከናወን ላይ ነው፡፡

በኢትዮጵያ አየር ኃይል የአራተኛው አየር ምድብ አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ቸርነት መንገሻ ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ አየር ኃይሉ በአሁኑ ወቅት በታሪኩ ታይቶ የማይታወቅ ሁለንተናዊ የሪፎርምና የተቋም ግንባታ ምዕራፍ ላይ ይገኛል።

ተቋሙ የሀገርን ሉዓላዊነት ከማስከበር ባለፈ፣ የሌሎች ሀገራትን የአየር ክልል የመጠበቅና የመከላከል ብቃት መገንባቱን አረጋግጠዋል።

ይህም አየር ኃይሉን በ2030 በአህጉሪቱ ቀዳሚ ለማድረግ ለተያዘው ግብ እንደ ትልቅ መሠረት እንደሚቆጠር ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር ኃይል የቆየውን የፓን አፍሪካኒዝም ዐሻራ በማስታወስ፤ ቀደምት የአፍሪካ ሀገራት ከቅኝ ግዛት ነፃ እንዲወጡ ተቋሙ ከፍተኛ ድጋፍ ማድረጉንም አስታውሰዋል።

በአሁኑ ወቅትም የበርካታ የአፍሪካ ሀገራትን የአየር ኃይል አባላት በማሠልጠን የአህጉሪቱ የዕውቀት ማዕከል መሆኑን አብራርተዋል።

የአየር ኃይል አካዳሚ ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ገዛኸኝ ነጋሽ በበኩላቸው፣ የ90ኛ ዓመት ክብረ በዓሉ ተቋሙ ከሕዝብ ጋር ያለውን ትስስር ይበልጥ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።

ተቋሙ በትውልድ ቅብብሎሽ እዚህ የደረሰው በጠንካራ ሙያዊ ሥነ ምግባር መሆኑን አመላክተዋል።

አሁንም ይበልጥ በመስራት በርካታ ጀግኖችን እያፈራ ይገኛል ያሉት ኮሎኔል ገዛኸኝ፣ ዜጎች ስለ አየር ኃይላቸው ጥንካሬና ዝግጁነት በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ በዓሉ ትልቅ ዕድል መሆኑን ጠቁመዋል።

የዘንድሮው ክብረ በዓል ንስሮቹ ያለፉበትን ፈታኝ ውጣ ውረድ ከማስታወስ ባለፈ፣ ተቋሙ የታጠቀውን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለዓለም በማሳየት የኢትዮጵያን የሰማይ ላይ የበላይነት ዳግም ያረጋገጠበት ሆኖ ተመዝግቧል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ድረ-ገፅ
https://dfmc.mod.gov.et/

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/-9629?si=Av-sDKCopw1FfTW2

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

23/05/2025
23/04/2025
09/09/2024
ሶማሊላንድ ምን አይነት ግዛት ናት? የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 17 ቀን 2016 ዓ.ም ሱማሊላንድርዕሰ ከተማ - ሃርጌሳ ስፋት - 177 ሺህ ስኩዌር ኪሎሜትርየህዝብ ብዛት - 5 ነጥብ 7...
26/01/2024

ሶማሊላንድ ምን አይነት ግዛት ናት?

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጥር 17 ቀን 2016 ዓ.ም

ሱማሊላንድ
ርዕሰ ከተማ - ሃርጌሳ
ስፋት - 177 ሺህ ስኩዌር ኪሎሜትር
የህዝብ ብዛት - 5 ነጥብ 7 ሚሊየን
ቋንቋ - ሶማሊኛ፣ አረብኛ፣ እንግሊዝኛ
ሶማሊላንድ የሶማሊያው ወታደራዊ መሪ ዚያድ ባሬ ከስልጣን በተወገደ ማግስት ከሶማሊያ ተነጥላ ነጻ ሀገር መሆኗን አውጃለች። ዚያድ ባሬ ኢሳቅ በተሰኘው የሶማሊላንድ ጎሳ አባላት ላይ የተከተለው ፖሊሲ ለውድቀቱ አንዱ ምክንያት ተደርጎ ይነሳል።

ሶማሊላንድ ዚያድ ባሬ እንደተወገደ በ1991 ከሶማሊያ መገንጠሏን ብታውጅም ሞቃዲሾም ሆነ ሌሎች ሀገራት እንደነጻ ሀገር እውቅና አልሰጧትም። አለማቀፉ ማህበረሰብ እውቅና ባይሰጣትም ሉአላዊ ሀገራት የሚያሰኙ ተግባራትን መፈጸም ከጀመረች ሶስት አስርት አመታት ተቆጥረዋል።

ራስ ገዟ ግዛቷ ከ1996 ጀምሮ የሶማሊላንድ ፓስፖርት አስተዋውቃለች፤ ህገመንግስት አጽድቃ፣ ምክርቤቶች አዋቅራም በየአምስት አመቱ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እያካሄደች ነው (ነጻነቷን ካወጀች ጀምሮ ሶስት ምርጫዎችን አድርጋለች)።

ከሀገራት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለመመስረት ጥረት እንደምታደርግም ትገልጻለች። በአሜሪካ፣ ብሪታንያ፣ አረብ ኤምሬትስ እና ታይዋን ጉዳይ ማስፈጸሚያ ቢሮዎች አሏት። የሶማሊያ መንግስት ግን እንግሊዝ በሞግዚትነት ያስተዳደረቻት ሶማሊላንድ “ከእናት ሀገሯ ሶማሊያ አልተነጠለችም፤ የግዛቴ አካል ናት” በሚለው አቋሙ እንደጸናች ያለች ይመስላል።

ሶማሊላንድን የሚመሩት ሙሴ ቢሂ አብዲ በህዳር ወር 2017 በተካሄደ ምርጫ አሸንፈው አህመድ ሲላንዮን ተክተዋል። ቢሂ የገዥው ኩልሚየ ፓርቲ መስራችና መሪው ሲላንዮ በ2010ሩ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ካሸነፉ በኋላ የፓርቲው ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል።

ከቅኝ ግዛት እስከ ነጻ ሀገር ምስረታ 1888 - ብሪታንያ ከወቅቱ የሶማሊላንድ መሪዎች (ሱልጣኖች) ጋር ስምምነት ደርሻለሁ በማለት አካባቢውን የቅኝ ግዛቷ አካል አድርጋ አወጀች 1899 - ሞሀመድ አብዱላህ የሃይማኖት አባት በብሪታንያ አገዛዝ ላይ አምጸው ደርቪሽ የተባለ ግዛት መስርተው ተዋጉ፤ በ1920 ተሸነፉ
1991 - የቀድሞዋ የብሪቲሽ ሶማሊላንድ ከሶማሊያ ሪፐብሊክ ተነጥላ ነጻ ሀገር መሆኗን አወጀች
2001 – 97 በመቶ ህዝቧ የሶማሊላንድ ህገ መንግስትን አጸደቀ ።

2016 - ሶማሊላንድ ከሶማሊያ የተነጠለችበትንና ነጻነቷን ያወጀችበት 25ኛ አመት ተከበረ፤ ይሁን እንጂ ለራስ ገዟ ግዛት እውቅና የሰጣት የለም ከእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ከተላቀቀች በኋላ የቅኝ ግዛት ድንበሯን አስጠብቃ መቆየቷን የምትገልጸው ሶማሊላንድ እንደሀገር የሚያስቆጥሩ ነገሮችን ሁሉ አሟልቻለሁ ትላለች፤ ሀገራት እውቅና እንዲሰጧትም ብርቱ ጥረት በማድረግ ላይ ትገኛለች።

ሶማሊላንድ ለኢትዮጵያ በሊዝ ወደብና የጦር ሰፈር ስታከራይ ከኢትዮጵያ በምትኩ የምቴገኘቸው ጥቅሞች እሥዳሉም አሳውቃለች።

በአባቱ ወልደማርያም

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
https://youtube.com/channel/UCgcF4HWzgNZRsmMlUlb8ebQ

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቴሌግራም
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ፌስቡክ
https://www.facebook.com/fdredefense.official

# የመከላከያ ሠራዊት ቁልፍ እሴቶች፡-1, ከራስ በፊት ለህዝብና ለሀገር ጥቅም፣2, ምንጊዜም የተሟላ ስብዕና፣3, ያልተሸራረፈ ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ፣4, በማንኛውም ግዳጅ ወይም ተግባር የላ...

05/06/2022
 #ጥቆማበሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ በአውሮፕላን አብራሪነት እና በቴክኒሽያንነት ሙያ ፍላጎት ያላቸውንና የምልመላ መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶችን መልምሎ ማ...
12/05/2022

#ጥቆማ

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ በአውሮፕላን አብራሪነት እና በቴክኒሽያንነት ሙያ ፍላጎት ያላቸውንና የምልመላ መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶችን መልምሎ ማሰልጠን ይፈልጋል፡፡

ለዚሁ የተለያዩ መስፈርቶች የወጡ ሲሆን ከነዚህ መካከል የትምህርት መመዘኛ #ለአብራሪዎች፦ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆኖ/ሆና በ2012 እና በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና ወስዶ/ወስዳ አጠቃላይ ውጤት 350 እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት እንዲሁም በእንግሊዘኛ፣ በሂሳብ እና በፊዚክስ የትምህርት አይነት አማካኝ ውጤት 70% እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት መሆን አለበት / አለባት።

እንዲሁም የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰደበትን/የወሰደችበትን የትምህርት ማስረጃ ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችል/የምትችል መሆን አለበት / አለባት።

ከሌሎች መመዘኛዎች መካከል ቁመት 1.65 ሜ እና ከዛ በላይ የሆነ/የሆነች፣ ክብደት ከ50-60 ኪ.ግ የሆነ/የሆነች፣ የአየር ኃይል አካዳሚን የመግቢያ ፈተና ወስዶ/ዳ ማለፍ የሚችል/የምትችል መሆን አለበት/አለባት።

#የቴክኒሽያኖች መመልመያ፦ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆኖ/ና በ2012 እና በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዶ/ዳ አማካይ ውጤት 300 እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት እንዲሁም በእንግሊዘኛ፣ በሂሳብ እና በፊዚክስ ትምህርት አማካኝ ውጤት 60% እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት መሆን አለበት / አለባት።

ሌሎች መመዘኛዎች ከላይ የተገለፀው ጋር ተመሳሳይ ነው።

የምዝገባ ቦታ ከላይ በዝርዝር የተቀመጠ ሲሆን የምዝገባ ጊዜ ከግንቦት 10 ጀምሮ እስከ ግንቦት 20/2014 ዓ.ም ድረስ ባሉ ተከታታይ የስራ ቀናት መሆኑን ተገልጿል።

NB. እድሜ ከ18-24

(ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን ከላይ ያንብቡ)

Address

Debre Zeyit

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian AIR FORCE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category