North shoa zon revenues department

North shoa zon revenues department this page is information site of north shoa revenues department activities.

03/06/2026

ተጠቃሚዎች ለከፈሉት ገንዘብ ደረሰኝ ባለመሰጠታቸው ግብር ከፋዩች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ
በ2018 በጀት ዓመት በሁሉም ወረዳና ከተማ ግብር ከፋዮች ደንብና መመሪያን አውቀው እንዲሰሩ በመድረክና በገጽ ለገጽ ትምህርት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ የተሰጣቸውን ትምህርት በተግባር ስለማዋላቸው በተደረገ ክትትል 3 ነጋዴዎች 150 ሺ ብር ሲቀጡ 5 የሚሆኑትን በመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ታልፈዋል፣ ሲሉ የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የታክስ ኢንተለጀንስ ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ ገልፀዋል፡፡
የህግ ተገዥነትን ለማሣደግና አጥፊዎችን ተጠያቂ ለማድረግ በተሰራው ስራ 55 ጥቆማዎችን ከህብረተሰቡ በመቀበልና በማጥራት 7.9 ሚሊዬን ብር የግብይት መረጃ የተገኘ ሲሆን ይህም በገቢ አሰባሰብ በኩል ውሣኔ እንዲሰጥበት ተደርጓል፡፡ እንዲሁም 322 ደረሰኞችን በመመርመር 188 የሚሆኑት ሐሰተኛ ደረሰኝ ሆነው በመገኘታቸው 10.3 ሚሊዬን ብር የተጨማሪ እሴት ታክስ ተገኝቶ ውሣኔ ተሰጥቶበት እስከአሁን 3.6 ሚሊዬን ብር ገቢ ሆኗል፡፡ ከዚሁ ጐን ለጐን የግል ድርጅት ተቀጣሪ ሠራተኞች የስራ ግብር ቀንሶ ወደ መንግስት የማስገባት ስራ በ94 ድርጅቶች ላይ ክትትል በማድረግ ተሰውሮ የነበረ 17.9 ሚሊዬን ብር ገቢ ተሰብስቧል ሲሉ አስተባባሪው ገልፀዋል፡፡ ለዚህም ውጤት መምጣት ጥቆማ ሰጪዎቻችንና አጋሮቻችን ተመስጋኞች ናቸው፡፤ በሌላ በኩል የተቋሙ ባለሙያዎችና አመራሮች ከብልሹ አሰራር ነፃ ሆነው በታማኝነት ህዝብ እንዲያገለግሉ ይጠበቃል፣ ለዚህም ተከታታይ ስልጠናና ምክር ሲሰጥ ቆይቷል፣ ሆኖም ግን 1 የጽ/ቤት ኃላፊና 8 ባለሙያዎች በሁለት ወረዳ ያለአግባብ ተጠቃሚነት ላይ ተሰማርተው በመገኘታቸው ጉዳያቸው በህግ እየታየ ይገኛል፣ ሲሉ አስተባባሪው አስረድተው በቀጣይም ግብር ከፋዩ ለተጠቃሚ ደረሰኝ በመስጠት ግዴታቸውን እንዲወጡ እንዲሁም ሃሰተኛ ደረሰኝ ከመጠቀም አንዲጠበቁ ተከታታይ ትምህርትና ግንዛቤ እንዲሰጣቸው አሣስበዋል፡፡ በሌላ በኩል የግል ድርጅቶች ከተቀጣሪ ሠራተኞች ተገቢውን የስራ ግብር ሰብስበው ለመንግስት እንዲያስገቡ እንዲሁም በሌብነት ላይ የተሰማሩ የገቢ ተቋሙ ባለሙያና አመራር ከድርጊታቸው ታቅበው ህጋዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፣ ሲሉ የመምሪያው የታክስ ኢንተለጀንስ አስተባባሪ አሣስበዋል፡፡
ዘገባው የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የግብር ትምህርትና ኮሙንኬሽን ዋና የስራ ሂደት ነው ግንቦት 22/2018 ዓ.ም

ውዝፍ የሚባል ግብር ወደ ቀጣይ በጀት ዓመት እንዳይዛወር  አልመን መስራት  አለብን ተባለዛሬ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የማኔጅመንት አባላት ከክልል ደጋፊ የ...
18/05/2026

ውዝፍ የሚባል ግብር ወደ ቀጣይ በጀት ዓመት እንዳይዛወር አልመን መስራት አለብን ተባለ
ዛሬ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የማኔጅመንት አባላት ከክልል ደጋፊ የቢሮው ባለሙያዎች ጋር የዞኑ የ10ወር እቅድ አፈፃፀም ተገመገመ::
አቶ ሽመልስ አዱኛ የክልሉ የሰው ሀብት ልማት ስራ አመራር ዳይሬክተር የግመገማውን አስፈላጊነት ሲያስረዱ በዋናነት የሚያተኩረው ገቢ የሚገኝባቸውን የገቢ አርዕስቶች ላይ የተደረሰበትን መጠን አውቀን በቀጣይ ሁለት ወራት በተለይ ውዝፍ የሚባል ግብር ወደ ቀጣይ ዓመት እንዳይዛወር የትኩረት ነጥቦችን መለየት ያስፈልገናል ሲሉ ደይሬክተሩ ገልጸዋል ::
ለግምገማው መነሻ የሚሆን አቶ ደምሴ አርአያ የዞኑ እቅድ አስተባባሪ የሂደቶችን አፈፃፀም በዝርዝር አቅርበው የግብር አሰባሰቡ በጥቅል 4.2 ቢሊዮን ብር 77.8% ገቢ ተሰብሰቧል ሲሉ የእቅድ ባለሙያ አስረድተዋል::
አቶ እንግዳወርቅ ገዛኸኝ የክልሉ የታክስ ጉዳዮች አማካሪ ሲያጠቃልሉ በአራት ጉዳዮች ላይ አተኩረን እንስራ በተለይ የሁሉንም ተግባራት አፈፃፀም ከፍ ማድረግ፤ የታክስ ስልጠናን ተከታትሎ መፈፀም፤ የቀን ገቢ ግምት ጥናቱን በጥራትና በጊዜ ሰርቶ ማጠናቀቅ እና ለ2019በጀት አመት የቅድመ ዝግጅት ስራውን በተሟላ መንግድ ልንፈፅም ይገባል ሲሉ አቶ እንግዳወርቅ ገዛኸኝ አስገንዝበዋል ፡፡
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ
የግብር ትምህር ኮምኒኬሽን ዋና የስራ ሂደት

የ2018 ዓ.ም የንግድ ትርፍና የኪራይ ገቢ ግብር በ33,810 ነጋዴዎች ላይ የቀን ገቢ ግምት ጥናት እንደሚጠና ተገለፀ ዛሬ ሚያዚያ 29/ 2018 ዓ.ም የ31 ወረዳና ከተማ የገቢዎች ማኔጅመ...
08/05/2026

የ2018 ዓ.ም የንግድ ትርፍና የኪራይ ገቢ ግብር በ33,810 ነጋዴዎች ላይ የቀን ገቢ ግምት ጥናት እንደሚጠና ተገለፀ
ዛሬ ሚያዚያ 29/ 2018 ዓ.ም የ31 ወረዳና ከተማ የገቢዎች ማኔጅመንት አባላት ከዞን የማኔጅመንት አባላት ጋር በቨርቺዋል ሚቲንግ በተደረገ ውይይት ወ/ሮ ቀለም ተስፋዬ የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ ሲገልፁ የግብር ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ከ3 እስከ 5 ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ የቀን ገቢ መጠናት አለበት አሁን ለዚህ ጥናት ዋናው መነሻ የግብርና ታክስ አዋጆች ተሻሽለዋል ቀደም ሲል ከ1996 ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ለ5 ጊዜ ያክል ተጠንቷል፡፡ ያሁኑ በባለፈው የቁርጥ ግብር አይነት የሚጠና ሳይሆን በገቢ ተቋሙ ብቻ የሚጠና ሲሆንየዚህ ጥናት አስፈላጊነት የግብር ከፋይ ደረጃ መቀየር ፣ የማስከፈያ ምጣኔ መለወጥ ፣ ተርን ኦቨር ታክስ መሰረዙ ነው ስለዚህ በአዲስ መጠናት አለበት፡፡ ጥናቱ በገቢ ተቋሙ ሠራተኞችና በግብር ከፋዮች ቀጥተኛ ተሣትፎ የሚጠና ይሆናል፡፡ ስለዚህ ሌላ የሚደራጅ ኮሚቴ የለም በዋናነት ሀገራዊና ክልላዊ ኦኮኖሚ ጋር ሊጣጣም የሚችል የቀን ገቢ ይጠናል እንዲሁም በጦርነት ምክንያት የኢኮኖሚ መዋዥቅ ስለገጠመ ይኸንን ታሣቢ ያደረገ ጥናት ማጥናት ያስፈልጋል፡፡ የቀን ገቢ ጥናቱ ደረጃ "ለ" ን የሚለመከት ሲሆን ትክክለኛ የቀን ገቢ በማጥናትና ንግድ ትርፍ ግብር ማስከፈል የመንግስት ገቢ ማሣደግ አዲስ ግብር ከፋዮችን ወደ ንግድ መረቡ ማስገባት ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ያሉትን የደረጃ ሽግግር ለመስራት ዕድል ይሰጣል፡፡ በገቢ ተቋሙ መጠናቱ ያለው ጠቀሜታ ጊዜ ይቆጥባል፤ አስተደራዊ ወጪ ይቀንሳል ፣ የማጥናት ልምድ ስላላቸው ችግሮችን ይቀንሳል እንዲሁም የሙያዊ ትክክለኛነትን ያመጣል፡፡በአጠቃላይ የንግድ አይነት ፣ ቦታ ፣ መጠን፣ የደንበኛ ብዛት ፣ የሽያጭ መጠን ፣ የንግድ ሰዓት እና የወቅታዊ ሁኔታ እንደዋና መስፈርቶች በመጠቀም በአግባቡ ተለይቶ ነባሩን ብቻ ሣይሆን አዲሶቹን ጭምር የቀን ገቢ ግምቱ መጠናት አለበት፡፡ ይህንን ጥናት ለማጥናት የሚቋቋሙ ኮሚቴዎች እንደተጠበቀ ሆኖ የገቢ ተቋሙ የማኔጅመንት ኮሚቴ ባለቤት ሆኖ ጥናቱን ይመራል፡፡ የማስገንዘብ ሥራውንም በየደረጃ ላለ አመራር ፣ ለፈጻሚዎች ፣ ለግብር ከፋዮች ለአጋርና ባለድርሻ አካላት ቀድሞ የማስረዳት ስራ መስራት አለባችሁ ጥናቱ የሚፈጀውም ጊዜ 20 ቀን ብቻ ሲሆን የሚጀመርበትን ቀን ክልሉ ወደፊት በሚያሳውቀው ጊዜ ይሆናል፡፡ ሲሉ መምሪያ ኃላፊዋ አስገንዝበዋል፡፡
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ
የግብር ትምህርትና ኮሙንኬሽን ዋና የስራ ሂደት

ከታክስና ግብር 3.7 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡ ተገለፀበ2018 በጀት ዓመት ከነጋዴዎች ፣ ከመንግስትና የግል ድርጅት ሠራተኞች ፣ ከኪራይ ገቢ፤ ከመሬት ሊዝ እና ከእርሻ ሥራ  ሊሰበሰብ የታ...
14/04/2026

ከታክስና ግብር 3.7 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡ ተገለፀ
በ2018 በጀት ዓመት ከነጋዴዎች ፣ ከመንግስትና የግል ድርጅት ሠራተኞች ፣ ከኪራይ ገቢ፤ ከመሬት ሊዝ እና ከእርሻ ሥራ ሊሰበሰብ የታቀደው 5.4 ቢሊየን ብር ሲሆን በአለፉት 9 ወራት የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ 3.7 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን የመምሪያው ገቢ አሰባሰብና ክትትል ዋና የሥራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ተሾመ ዳኜ ገልፀዋል፡፡
ዞኑ በሰሩ የሚገኙ 22 ወረዳና የከተማ አስተዳደሮችን በማስተባበር ከመደበኛ ገቢ 4,803,391.94 ብር እና ከከተማ አገልግሎት ገቢ ብር 578,628,981 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ገቢውን ለመሰብሰብ በየደረጃው ያለ ገቢ ተቋሙ ባለሙያና አመራር፤ የንግድና ዘርፍ ማህበራት አመራሮች፤ አጋርና ባለድርሻ አካላትና ከወረዳ እስከ ዞን ያሉ አመራሮች በተከታታይ በተደረገ ክትትል፤ ግምገማና ድጋፍ
ከመደበኛ ገቢ 3,390,148,169 ብር ከከተማ አገልግሎት ገቢ 300,854,076 ብር በድምሩ 3,691,002,245 ቢሊዮን ብር የተሰበሰበ ሲሆን አፈጻጸሙም 68.6 % ደርሷል እንዲሁም በ9 ወር ለመሰብሰብ ካቀድነው 4,115,849,923 ብር ውስጥ 3,390,148,169 ቢሊየን ብር ሰብስበን አፈጻጸሙን 89.7 % ማድረስ ችለናል ብለዋል አያይዘውም ባለፈው 2017 በጀት ተመሳሳይ ወቅት ከተሰበሰበው 2,503,222,838 ብር ገቢ ጋር ሲነጻጸር በብልጫ 1,187,779,407 ቢሊየን ብር የተሰበሰበ ሲሆን ማለትም 45.5% እድገት ተመዝግቧል ሲሉ አቶ ተሾመ ዳኜ ገልፀዋል፡፡
በመጨረሻም በቀጣይ 3 ወራት በውዝፍ ግብር ፣ በመሬት ሊዝና በእርሻ ሥራ ገቢ ግብር አሰባሰብ ላይ ሁሉም ባለሙያና አመራር ትኩረት አድርጎ በመስራት የዕቅድ አፈጻጸማችንን ከፍ ማድረግ አለብን ሲሉ የገቢ አሰባሰብና የክትትል የሥራ ሂደት አስተባባሪው አስገንዝበዋል፡፡
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ
የግብር ትምህርትና ኮሙዩንኬሽን ዋና የሥራ ሂደት
ሚያዚያ 06/2018 ዓ.ም

የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በዓል በሰላም በጤና አደረሣችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መም...
09/04/2026

የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በዓል በሰላም በጤና አደረሣችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የዞኑን የግብር አስተዳደር አዋጅ በመጠቀም በ2018 በጀት ዓመት እስከ አሁን 5.4 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰብስቦ የዞኑን ልማት ለማፋጠን እየሰራ ይገኛል፡፡
ስለሆነም እስከአሁን ከአመቱ ዕቅድ 3.5 ቢለዮን ብር 65.4% ለመፈፀም የቻልን ሲሆን ለደረስንበት አፈፃፀም አስተዋጽኦ የነበራችሁን ህግ አክባሪ ግብር ከፋዮች፣ ታታሪ የገቢ ተቋሙ ባለሙያና አመራር ፤ ከዞን እስከ ወረዳና ከተማ የተሰማራችሁ አመራሮች እንዲሁም አጋርና ባለድርሻ አካላት የላቀ ምስጋና እያቀረብን መልካም የትንሳኤ በአል ይሁንላችሁ እያልን ከበአሉ ጋር በተያያዘ አገልግሎት ሲሰጡና ሲጠቀሙ ሲገዙና ሲሸጡ ደረሰኝ በመስጠትና በመቀበል የታክስ ድርሻችሁን እንድትወጡ ለመላው የዞኑ ግብር ከፋዮችና ህብረተሰብ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ መልካም በዓል ይሁንላችሁ ፡፡

’’ ግብሬን ደስ ብሎኛ እከፍላለሁ ’’
መልካም በዓል የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ
2018 ዓ.ም

የገቢ ተቋሙን ከፍተኛ ጥረት የሚጠይቁ የገቢ አርዕስቶች ላይ ርብርብ በማድረግ ገቢ እንደሚሰበሰብ ተገለፀ ዛሬ መጋቢት 17/2018 ዓ.ም. የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ ከወረዳና ከተማ ጠቅ...
26/03/2026

የገቢ ተቋሙን ከፍተኛ ጥረት የሚጠይቁ የገቢ አርዕስቶች ላይ ርብርብ በማድረግ ገቢ እንደሚሰበሰብ ተገለፀ
ዛሬ መጋቢት 17/2018 ዓ.ም. የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ ከወረዳና ከተማ ጠቅላላ ሠራተኛ በዙም /Verchual meeting/ የ8 ወር ዕቅድ አፈጻጸም ተገምግሟል፡፡ አቶ ደምሴ አርአያ የመምሪያ ዕቅድ ዝግጅት አስተባባሪ አፈጻጸሙን ሲያቀርቡ ከመልካም አስተዳደር ሥራዎች የሂሣብ መዝገብ ምርመራ በወቅቱ በመደረጉ የተሻለ ሥራ ተሰርቷል፡፡ እንዲሁም ቅሬታና ይግባኝ ፈጣን ምላሽ እየተሰጠ ነው ከዚሁ ጎን ለጎን በኢንተለጀንስ የተገኙ መረጃዎችን አጥርቶ የመወሰን የማስከፈል ሥራ ትኩረት የተሰጠው ሲሆን 726 መዝገብ ተመርምሮ ገቢው እየተሰበሰበ ነው፣ የመረጃ ቴክኖሎጂ ሥራችን ተቀናጅቶ መሠራት ያለበት በመሆኑ ሌሎች ባለሙያዎችን በማሰልጠን በሲስተም ሥራዎችን የመስራት ክህሎቶች ከፍ እያለነው፡፡ የግብር ህጎችን የማስተማር ሥራው ለነጋዴው ብቻ ሣይሆን ለአጋርና ለባለድርሻ አካላት እንዲሁም ለመንግስት ሠራተኞች በመድረክና በተናጠልም እየተከናወነ ነው፡፡ በገቢ አሰባሰብ መደበኛ ገቢ 3.2 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል አፈጻጸሙም 66.4% ከከተማ አገልግሎት ገቢ 284.2 ሚሊየን ብር ተሰብስቧል አፈጻጸሙም 50% ነው በአጠቃላይ 3.5 ቢሊየን ብር 65% ገቢ ተሰብስቧል፡፡የተሻሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ 9 ወረዳና ከተሞች አሉ ልዩነታችሁ እየሰፋ ስለሆነ የተቀራረበ ውጤት ለማምጣት ጥረት አድርጉ ሲሉ አቶ ደምሴ አርአያ ገልፀዋል፡፡ ዞኑ ባቀረበው ሪፖርት ላይ ተመስርቶ ወረዳና ከተሞች ጥያቄና አስተያየት ሰጥተው የግምገማ ሃሳቡን መቀበላቸውን ገልፀዋል፡፡
በቀጣይ መከናወንና ትኩረት የሚገቸው ነጥቦች ወ/ሮ ቀለም ተስፋዬ የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ ሲገለፁ በዚህ ወቅት 75% አፈጻጸም መድረስ ነበረብን ነገር ግን 66% ላይ ብቻ ተቀምጠናል፡፡ በዚህም ከዞን አማካይ በታች ያላችሁ ወረዳና ከተሞች የገቢ ተቋሙን ጥረት የሚጠይቁ ገቢዎች ላይ ትኩረት አድርጋችሁ እንድትሰሩ እንዲሁም ውዝፍ ግብር ያለባችሁ የንገድ ትርፍ ፣ የሊዝና የኪራይ ገቢ ዋነኛ የትኩረት ማዕከል ናቸው የሮያሊቲ ገቢ አሰባሰብ አዝጋሚ ሆኗል፡፡ ስለዚህ አጋር አካላት በማስተባበርና በመቀናጀት ገቢው በወቅቱ ሊሰበሰብ ይገባል በሌላ በኩል የተመረመሩ የሂሣብ መዝገቦች ወስኖ የማስከፈል ሥራ የቅድሚያ ተግባራችን ነው፡፡ ይኸንን ተግባር ለመፈፀም የተነቃቃ የሰው ሀይል ያስፈልጋል ለዚህ ደግሞ በተደረገው የደመወዝ ጭማሪ እየቆዘማችሁ ነው ትክክል አይደለም እየሰራን ነው መብታችንን መጠየቅ ያለብን የመረጃ ቴክኂዎሎጂን ተግባራዊ ለማድረግ የግብአት ማሟላት ሥራ በተለይ አመራሩ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው ሲሉ የመምሪያ ኃላፊዋ አሳስበዋል፡፡
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ
የግብር ትምህርትና ኮሙዩንኬሽን ዋና የሥራ ሂደት

የእርሻ ስራ ግብር በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አጠቃሎ ለመሰብሰብ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡በዛረው እለት መጋቢት 09/ 2018 ዓ.ም አቶ ተሾመ ዳኜ የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የገቢ አሰባ...
18/03/2026

የእርሻ ስራ ግብር በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አጠቃሎ ለመሰብሰብ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡
በዛረው እለት መጋቢት 09/ 2018 ዓ.ም አቶ ተሾመ ዳኜ የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የገቢ አሰባሰብና ክትትል ዋና ስራ ሂደት አስተባባሪ እንዳሉት መምሪያው በስሩ ያሉትን 22 የገጠርና 9 ከተማ አስተዳደሮች በማስተባበር በያዝነው 2018 የግብር ዘመን ብር 5.4 ቢሊዮን ለመሰብሰብ አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ያለ ሲሆን እስከ አሁን የእቅዱን 3.4 ቢሊዮን ብር /64%/ መሰብሰብ ተችሏል፡፡ ገቢው ከሚሰበስብባቸው ዘርፎች አንዱ እርሻ ስራና ገጠር መሬት መጠቀሚያ ግብር ሲሆን፡- በዞኑ ውስጥ ከ390‚803 አርሶ አደሮች ይገኛሉ ከነዚህ አርሶ አደሮች ብር 60‚545‚690 ለመሰብሰብ በእቅድ ተይዞ እስከ አሁን 87‚348 አርሶ አደሮች ብር 15‚102‚245 በማስከፈል መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን አፈፃፀሙ በገንዘብ /25%/ ነው፡፡ ይህ አፈፃፀም ከባለፋው አመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረው በሰው 174‚597 በገንዘብ 26‚825‚624 ጋር ሲነፃፀር የዚህ በጀት ዓመት ክንውን ቀንሷል፡፡ ለዚህ አፈፃፀም ማነስ ዋነኛው ምክንያት በየአካባቢው ገጠራማ ቀበሌዎች እንዲሁም የግሼ ሙሉ ወረዳ የፀጥታ ችግር ያለባቸው በመሆኑ በነፃነት ተንቀሳቅሶ ግብሩን ለመሰብሰብ አለመቻሉ ነው፡፡ ብለዋል አቶ ተሾመ ዳኜ አያይዘውም በቀጣይ ይህንን አፈፃፀም ለማሻሻልና ገቢውን ለመሰብሰብ አጠቃላይ የየወረዳ አመራሩ ተግባሩን የቼክሊስት አካል በማድረግ የተለያዩ ስልቶችን ለመጠቀም /ከግብአት ስርጭት ጋር/በማያያዝ ለመሰብሰብ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡ እንዲሁም የገቢ ተቋሙ አመራርና ባለሙያም መረጃውን አደራጅቶ ለአመራሩ የመስጠትና ከእጀቢዎች ጋር ተንቀሳቅሶ ለመሰብሰብ እየተደረገ ያለው ጥረት መልካም ጅምር ነው ስለሆነም በመጭው አንድ ወር ጊዜ የተሸለ ውጤት ለማምጣት እየተሰራ ነው ሲሉ የመምሪያው የገቢ አሰባሰብ ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪው ገልፀዋል፡፡
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የግብር ትምህርትና ኮሙንኬሽን ዋና የስራሂደት

በገቢ ተቋሙ እና በየደረጃው ባለ አመራር ተከታታይ ድጋፍና ክትትል በመደረጉ ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተገለፀየሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የበጀት ዓመቱ ዕቅድ   5,382,02...
10/03/2026

በገቢ ተቋሙ እና በየደረጃው ባለ አመራር ተከታታይ ድጋፍና ክትትል በመደረጉ ከ3 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተገለፀ
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የበጀት ዓመቱ ዕቅድ 5,382,020,929 ብር ሲሆን እስከ የካቲት 30/2018 ዓ.ም ድረስ የተሰበሰበ ገቢ መደበኛ 2,951,715,066 ብር አፈፃፀም 61.45% የከተማ አገልግሎት 280.004,389 ብር አፈፃፀም 48.39% በድምሩ 3,231,719,456 ብር አፈፃፀም 60.05% ሲሆን ከ2017 ዓ.ም ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በብልጫ በ1,019,445,751 ብር ወይም 46.1% እድገት አሳይቷል ሲሉ ወ/ሮ ቀለም ተስፋዬ መምሪያ ሀላፊዋ ገልፀዋል አያይዘውም ለውጤቱ መምጣት በአመቱ መጀመሪያ ተገቢ የሆነ የእቅድ መግባባት በመፍጠር በትልቅ መድረክ የታክስ ንቅናቄ በማድረግ እና በተሰጠው ዕቅድ ላይ ከሁሉም ወረዳና ከተማ ጋር መግባባት በመፈጠር፤ ለሁሉም ወረዳና ከተማ የቀን የገቢ ዕቅድ ቆጥሮ መሰጠት፤ የመምሪያው የማኔጅመንት አባላትና ባለሙያዎች ወረዳና ከተማን በቀጠና በመከፋፈል በአካል እና በየቀኑ በስልክ መደገፍና መከታተል በመቻሉ፤ እንዲሁም በየቀኑ ለስራ የሚያነሣሣ ግብረ-መልስ በመስጠትና የተሻለ ለፈፀሙ ወረዳና ከተማ እውቅናና ማበረታቻ በመስጠት ፉክክር ውስጥ ማስገባት በመቻሉ፣ በሁሉም ወረዳና ከተማ ከፖለቲካ አመራሩ ጋር የጋራ በማድረግ ጥረት የሚጠይቁ ገቢዎችን በመለየት ግብር ከፋዮን የመቀስቀስ ስራ በየጊዜው በመሠራት፤ በየሣምንቱ ወረዳና ከተማን በዙም በመደገፍ የተደረሰበትንና የገጠሙ ችግሮችን ለይቶ መፍታት በመቻላችን የተሸለ ውጤት አስመዝግበናል፡፡ እንዲሁም ከዞን አስተባባሪዎች ጀምሮ የገቢ ስራን ከፀጥታ ስራው ቀጥሎ በመያዝ የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ ከንቲባዎችና ሌሎች በየደረጃው ያሉ አመራሮች ገቢ በመሰብሰብ ልማታችንን የማስቀጠል ጉዳይ ወሳኝነት በመረዳት በትኩረት ተቋሙን እየደገፉና እያገዙ ሲሆን በዋናነት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ወረዳና ከተማን በዙም ሚቲንግ ጭምር በመገምገም በትኩረት እየደግፉ ስራውን እንዲያግዙ በማድረጋቸው ለመጣው ውጤት ባለድረሻ ናቸው፡፡ አጋር አካላትም የገቢ መሰብሰብ ስራውን በሁሉም ዘርፍ በመደገፍና በማገዝ ላይ ናቸው፡፡ የንግዱ ማህበረሰብም ቢሆን በአዳዲስ አሰራሮች ላይም በሚጠሩ ውይይትና መድረኮች በመገኘት ሃሣብ የመስጠትና ግብር የምከፍለው ለራሴ እና ለሃገሬ ልማት ነው የሚለው አስተሳሰቡ በመሻሻሉ የገቢ አሰባሰቡ የተሸለ እንዲሁን አግዟል ብለዋል መምሪያ ሀላፊዋ በቀጣይም ትኩረት የሚደረግባቸውን ነጥቦች ሲያነሱ በሁሉም የገቢ አርእስት ያልተሰበሰበ ገቢን በትኩረት በለየነው መሠረት ወረዳና ከተማ ገቢውን እና ውዝፍን ቆጥሮ መሰብሰብ እንዲሁም የንግድ ትርፍ፤ የኪራይ ገቢ፤ የደረጃ “ለ” እና “ሀ” በዝርዝር ለይቶ በትኩረት መሰብሰብ በዚሁ ጎን ለጎን ሁሉም የገቢ ተቋሙ አመራሮችና ሙያተኞች ስራውን በየቀኑ እየገመገሙ መምራት፣ ጥቅል የፖለቲካ አመራሩና ባለድርሻ አካላት ገቢ መሰብሰብ የህልውና ጉዳይ ነው በማለት ተቋሙን ማገዝ፣ የከተማ አገልግሎት ገቢ በአዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ መሠረት በትኩረት መስራት ይገባል ሲሉ ወ/ሮ ቀለም ተስፋዬ አሳስበዋል፡፡
የግብር ትምህርትና ኮሙንኬሽን ዋና የስራ ሂደት 01/07/2018 ዓ.ም

በኢታክስ ግብር ከፋዩ ባለበት ቦታ ሆኖ ኢንተርኔት በመጠቀም ግብሩን መክፈል እንደሚችል ተገለፀየሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ በስሩ ከሚገኙት 9 ከተማ አስተዳደሮች የመረጃ ቴክኒዎሎጂ ባለሙያ...
06/03/2026

በኢታክስ ግብር ከፋዩ ባለበት ቦታ ሆኖ ኢንተርኔት በመጠቀም ግብሩን መክፈል እንደሚችል ተገለፀ
የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ በስሩ ከሚገኙት 9 ከተማ አስተዳደሮች የመረጃ ቴክኒዎሎጂ ባለሙያዎች የካቲት 27/2018 ዓ.ም. ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡ ስልጠናውንም ያስጀመሩት አቶ ግርማ ተስፋዬ የመምሪያ የመረጃ ቴክኒዎሎጂ አስተባባሪ ሲሆኑ የስልጠናው አላማ ኢታክስን ጥቅም ላይ ማዋል ነው ፡፡ በዚህ ተጠቃሚ የሚሆኑት በአሁኑ ሰዓት የደረጃ ሀ ግብር ከፋዮች ሲሆኑ ጠቀሜታውም ኢታክስ ግብር ከፋዮ ማንኛውንም ክፍያ ባለበት ቦታ ሆኖ በኢንተርኔት ተጠቅሞ መክፈል እንዲችል በዚህም በሣምንት ሰባት ቀናትና 24 ሰዓት ስለሚሰራ መጠቀም ይችላል፡፡ የተሻለ አገልግሎት ግብር ከፋዩ እንዲያገኝ እንዲሁም ህገ-ወጥ ደረሰኝን ይከላከላል በዚሁም ጎን ለጎን ያደገ ገቢ ለመሰብሰብ ያስችላል ሲሉ አቶ ግርማ ተስፋዬ አብራርተዋል፡፡
በተጨማሪም በተባባሪ አሰልጣኝነት የተጋበዙት የደ/ብርሃን ከተማ የመረጃ ቴክኒዎሎጂ አስተባባሪ አቶ ሻምበል ጋሻው እንዳሉት ማንኛሉም ግብር ከፋይ በገቢ ተቋሙ በሲስተም ፋይል የተከፈተለት ኢንተርኔት ባለበት ቦታ ሆኖ ግብርና ታክሱን በመክፈልና ክሊራንስ በመውሰድ አገልግሎቱን ያለእንግልትና ጊዜ በመቆጠብ የግል ሥራውን እንዲሰራ ያስችለዋል በማለት አቶ ሻምበል ጋሻው ገልፀዋል፡፡
በአጠቃላይ የመረጃ ቴክኒዎሎጂ ባለሙያዎች ለ3 ቀናት በተግባር የተደገፈ ስልጠና ውስጥ እንደሚያልፉ የመምሪያው የመረጃ ቴክኒዎሎጂ አስተባባሪ አቶ ግርማ ተስፋዬ ገልፀዋል፡፡

የሰሜን ሸዋ ዞን ገቢዎች መምሪያ የግብር ትምህርትና ኮሙንከሽን ዋና የስራ ሂደት

04/03/2026

Address

Debre Birhan

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when North shoa zon revenues department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share