አብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ

  • Home
  • Ethiopia
  • Debre Birhan
  • አብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ

አብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን  ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ ANRS ethics & anti-corruption commission
Debire Birhan branch

03/06/2026

‎በሐሰተኛ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ሰነድ ለመገልገል የሞከሩ ግለሰቦች በፅኑ እስራት ተቀጡ

‎ግንቦት 26/2018 ዓ.ም ‎​በወላይታ ዞን በሐሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀትና መገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ቀርቦባቸው የነበሩ ሁለት ግለሰቦች በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ ተቀጡ፡፡

‎ተከሳሾቹ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ 1ኛ ተከሳሽ የ2ኛ ተከሳሽ ጠበቃ ሲሆን 2ኛ ተከሳሽ ከአይናቴ ሎሪሶ ከተባለች ግለሰብ ጋር በነበረው የውርስ ክርክር ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ 47413 በሆነው በቀን 12/06/16ዓ.ም ለ2ኛ ተከሳሽ ውሰኔ የተወሰነ በማስመሰል ሐሰተኛ የጠቅላይ ፍ/ቤት ማህተምና የጠቅላይ ፍ/ቤቱ ምክትል ፐሬዝዳንት ፊርማ ያልሆነውን በማሳረፍ ሐሰተኛ የውሳኔ ግልባጭ ለ2ኛ ተከሳሽ የሰጠ ሲሆን 2ኛ ተከሳሽም የተዘጋጀውን ሐሰተኛ ውሳኔ እያወቀ በመገልገል የግል ተበዳይ አይናቴ ሎሪሶን የውርስ ክስ በመቃወም ለዳሞት ፑላሳ ወረዳ ፍ/ቤት ያቀረበ በመሆኑ ተከሳሾች በፈጸሙት ሐሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና መገልገል ወንጀል ተከሰዋል፡፡

‎የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን የክስ መዝገብ የመረመረው የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሾቹን ጥፋተኛ በማለት 2 አመት ከ9 ወር ጽኑ እስራት እና 1,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል፡፡
‎​"ይህ የቅጣት ውሳኔ ለሌሎች መሰል ድርጊት ለሚፈጽሙ አካላት አስተማሪ እንዲሆን ታስቦ የተላለፈ ነው፡፡ ማህበረሰቡም የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና አጥፊዎችን ወደ ሕግ ለማቅረብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል፡፡"
ዘገባው ‎የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ክፍል

03/06/2026

ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት የሙስና ወንጀል የሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነት
****************
ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት በተገልጋዩ ህብረተሰብ እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል ባለ ግንኙነት የሚፈጸም ተገቢነት የሌለው ተግባር ነው፡፡ ተገልጋዩ የህብረተሰብ ክፍል በህግ ክርክሮች እና በአስተዳደር አካላት የሚሰጡ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን ለማግኘት ወደ ተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ፊት ይቀርባሉ፡፡
በዚሁ ሁኔታ አገልግሎት ፈልጎ የቀረበው ተገልጋይ እንደ ጉዳዩ ባህሪ በህግ እና አሰራር በተቀመጠ ምክንያታዊ ጊዜ ውስጥ ለጉዳዩ እልባት አግኝቶ መሸኘት አለበት፡፡ ይህ የማይሆን ከሆነ ተገልጋዮችን ተገቢ ላልሆነ እንግልት በመዳረግ ጊዜያቸውን፣ ገንዘባቸውን እና ጉልበታቸውን እንዲያባክኑ በማድረግ፣ ለከፋ ምሬት እና ተስፋ በመቁረጥ በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሻክር ይሆናል፡፡
ያለአግባብ ጉዳይ ማጓተት በሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 18 መሰረት ማንኛውም የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ኃላፊ ወይም ሠራተኛ በኃላፊነቱ በሥራው ምክንያት በቀረበለት ጉዳይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ጥቅም ለማግኘት ሲል በጉዳዩ ላይ ጥቅም ያለውን ማንኛውንም ሰው ለመጥቀም ወይም ለመጉዳት በማሰብ ከህግ፣ ከመመሪያ ወይም ከተለመደው አሰራር ውጪ ያለበቂ ምክንያት ጉዳዩን ያልወሰነ፣ ያዘገየ ወይም ባለጉዳይን ያጉላላ እንደሆነ እንደ ጉዳዩ ታይቶ በገንዘብ ወይም በእስራት ይቀጣል፡፡
በአዋጁ እንደተደነገገው ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት የሙስና ወንጀል የሆነበትን መሠረታዊ ምክንያት ነው፡፡ በዚህም መሰረት የሙስና ወንጀሎች በመሰረታዊነት የሚፈጸሙት የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለአንዱ ወገን በተለያዩ ምክንያቶች በማዳላት ሌላውን ወገን ለመጥቀም በማሰብ ነው።
የዚህ ወንጀል ፈጻሚዎች ጉዳይን አለአግባብ የማጓተት ተግባር የሚፈጽሙት ባለጉዳዩ በመመላለስ ምክንያት ከሚደርስበት እንግልት ለማምለጥ ሲል ገንዘብ እንዲከፍላቸው ተጽእኖ ለማሳደር አልያም ባለጉዳዩ ተማሮ ጉዳዩን መከታተሉን እንዲተወው በማድረግ የባለጉዳዩን መብት ለመረጡት ሌላኛው ሰው በማስተላለፍ በዚህም የሚከፈላቸውን ተገቢ ያልሆነ የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ ነው ማለት ይቻላል፡፡
የመንግስት መስሪያ ቤቶችም ሆኑ የልማት ድርጅቶች እንዲሁም የህዝባዊ ድርጅቶች ተገልጋዮቻቸውን ሲያስተናግዱ አገልግሎት ወይም ውሳኔ የሚሰጥበት ጉዳይ ያለውን ልዩ ባህሪ ግምት ውስጥ በማስገባት በህግ እና በአሠራር ሥርዓት እንዲሁም የተለመዱ አካባቢያዊ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ለተገልጋዮቻቸው በተገቢው ጊዜ ውሳኔ የመስጠት ግዴታ አለባቸው፡፡
ይህ ሳይሆን ቀርቶ ያለ በቂ ምክንያት ህግ እና አሰራርን በመጣስ ተገልጋዮችን ለማንገላታት እና ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት እንዲሁም አገልግሎት ጠያቂው ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ ጉዳይን ያለበቂ ምክንያት ማጓተት በህግ የሚያስጠይቅ እና የሚያስቀጣ የሙስና ወንጀል ተግባር መሆኑን መረዳት ይገባል፡፡
ተገልጋዩ ማህበሰረብ በመንግስትም ይሁን ህዝባዊ ተቋማት አገልግሎት ለማግኘት ሲሄድ በህግ እና አሠራር ስርዓት የተቀመጡ የአሰራር ደረጃዎችን ተረድቶ በዛ ውስጥ ውሳኔ እንዲያገኝ መጠየቅ እና ይህ በማይሆንበት ጊዜ ጉዳዩን ያለ በቂ ምክንያት የሚያጓትቱ የመንግስት እና ህዝባዊ ድርጅት ሠራተኞች እና ኃላፊዎች ላይ የህግ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት በመጠቆም ተባባሪ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

02/06/2026

በርካታ የመንግስት ሠራተኞች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ታሰሩ

****************

(ፌ.ሥ.ፀ.ሙ.ኮ ግንቦት 25/2018 ዓ.ም) የሳዑዲ አረቢያ የተቆጣጣሪ እና የፀረ-ሙስና ባለስልጣን (ናዛሃ) ባለፈው ግንቦት ወር በሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው 160 የመንግስት ሰራተኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቋል።

በቁጥጥር ስር የዋሉት ክትትሎችን በማድረግ፣ የተጠረጠሩባቸውን ጉዳዮችን በማጣራት እና በርካታ የወንጀል እና አስተዳደራዊ ጉዳዮችን መጣሳቸውን ተከትሎ ነው።

ባለፈው ወር ናዛሃ በሀጅ ሰሞን በቅዱሳን እና የአገልግሎት መስጫ ቦታዎች ከ15 ሺህ ከሚጠጉ ክትትሎች በተጨማሪ በመንግስት መስሪያቤቶች 2,365 ሠራተኞች ላይ ክትትሎችን አድርጓል።

ከእነዚህ ክትትሎች በ480 ሠራተኞች ላይ በተጠረጠሩባቸው ጉዳዮች ላይ ምርመራ ከተደረገባቸው መካከል 160 የሚሆኑት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል የማዘጋጃ ቤትና ቤቶች ሚኒስቴር፣ የትምህርት ሚኒስቴር፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና የእስልምና ጉዳዮች የጥሪ እና መመሪያ ሚኒስቴር እንዲሁም የዘካት፣ የታክስ እና ጉምሩክ ባለስልጣን ሰራተኞች ይገኙበታል ተብሏል።

የተከሰሱባቸው ወንጀሎችም ጉቦ እና የመንግስት የሥራ ቦታዎችን አላግባብ መጠቀምን ያጠቃልላል ሲል ሳውዲ ጋዜጣ ዘግቧል።

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

30/05/2026

በሙስና ወንጀል የተከሰሱ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች በእስራት ተቀጡ።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿

የአብማ ክፍለከተማ አመራር እና ባለሙያዎች ከመሬት ጋር በተያያዘ ሙያቸውንና ስልጣናቸውን ተጠቅመው የሰነድ አልባ በማጽናት እና በማጽደቅ ሂደት የመንግስትን መሬት ለሌላ ግለሰብ አሳልፈው መብት የፈጠሩ 10 ተከሳሾች በፈፀሙት የሙስና ወንጀል በሁለት መዝገብ በማጣራትና በማደራጀት በቁጥጥር ስር ውለው አስፈላጊው የምርመራ በማጣራት መዝገቡን ለምስራቅ ጎጃም ዞን አቃቢ ህግ መምሪያ መላክ መቻሉን የደብረማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የሙስና ወንጅሎች ምርመራ ዋና ክፍል ሃላፊ ኮማንደር ጌታነህ አሰፋ ገልጸዋል ።

የምስራቅ ጎጃም ዞን አቃቢ ህግ መምሪያ ከፖሊስ የደረሰውን የምርመራ መዝገብ በማደራጀትና ክስ በመመስረት በህግ አግባብ ሲታይ ከቆየ በኋላ የምስራቅ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀን በ19/9/2018 ዓ,ም በዋለው ችሎት ተከሳሾች ጥፋተኛ መሆናቸው በሰውና በሰነድ ማስረጃ በመረጋገጡ
1ኛ አቶ አላምር ተስፋዬ በሁለት መዝገብ በ10 አመት
2ኛ ወይዘሮ ሀይማኖት ታሪኩ በሁለት መዝገብ በ10አመት
3ኛ አቶ መኳንንት ጠለለ በሁለት መዝገብ በ10 መት
4ኛ አቶ እንዳልካቸው በሁለት መዝገብ በ10 አመት
5ኛ አቶ ተሻለ መብራቴ በሁለት መዝገብ በ10 ዓመት
6ኛ አቶ ዮሴፍ ጌትነት በሁለት መዝገብ በ10 አመት
7ኛ አቶ ስላንተ ጥበቡ በሁለት መዝገብ በ10 አመት

8ኛ ወይዘሮ ታሪክ ሞትባይኖር በተለዬ መንገድ ከግለሰቦች ጋር በመመሳጠር የቴክኒክ ኮሚቴውንና የአብይ ኮሚቴውን በማሳመን ለግለሰቦች መብት ከመፍጠር ባሻገር በራሷ ልጆች ስም የመንግስትን መሬት በማዘወር መብት የፈጠረች መሆኑን በማስረጃ በመረጋገጡ በሁለት መዝገብ በ12 አመት እንዲሁም ወይዘሮ ሶሊያና መሀሪና ወይዘሮ አብዮት እጅጉ እያንዳንዳቸው በ3 አመት ገደብ መቀጣታቸውን ገልጸዋል ።

የሙስና ወንጀል የመልካም አስተዳደር ችግር ከመፍጠሩም በላይ በሀገር ኢኮኖሚ ፣ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮችን በማስከተል በህዝብ እና በመንግስት መካከል መተማመን እና ተቀራርበው እንዳይሰሩ የሚያደርግ መጥፎ በሽታ በመሆኑ ማንኛውም ህብረተሰብ የሙስና ወንጀል ሲፈፀም ሲያውቅ ወይም ሲመለከት ጥቆማ በመስጠት እና ለህግ ተባባሪ በመሆን የዜግነት ድርሻቸውን መወጣት እንደሚገባ ገልጸዋል ።

የደብረማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የሙስና ወንጀሎች ምርመራ ዋና ክፍል ሙስና ጠል ህብረተሰብ ለመፍጠር እና ለመገንባት እንዲሁም የመንግስት አገልግሎት ያለምንም ዳረጎት እና ክፍያ ዜጎች የማግኘት መብት ያላቸው መሆኑን ተገንዝበው ህገወጥ የመንግስት ሀብት ምዝበራ እና ሌሎች የሙስና ወንጅሎ ሲፈፀሙ በስልክ ፣በአካል በመቅረብ አቤቱታ ማቅረብ የሚቻል መሆኑን ገልጸው የሙስና ወንጀል መከላከል የፖሊስ ወይም ለተወሰነ አካል የሚሰጥ ባለመሆኑ የመንግስት ሰራተኞች ፣ባለሙያዎች፣ የመንግስት አመራሩ እና መላው ህብረተሰቡ ሙስናን ለመከላከል በሚሰራው ስራ መሪ ተዋናይ ሊሆኑ እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

በመጨረሻም የምርመራ መዝገቡ ውጤታማ እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ በክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የሙስና ወንጀሎች ዋና መምሪያ እና ለምስራቅ ጎጃም ዞን አቃቢ ህግ መምርያ ከፍተኛ ምስጋና ያቀረቡ መሆኑን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተ/ር ፖሊስ መምሪያ በማህበራዊ ተስስር ገጹ መረጃዉን አጋርቷል ።

29/05/2026
29/05/2026
28/05/2026

የሃብት ምዝገባ አይነቶች
🚎🚎🚎🚎🚎🚎🚎
1. የመጀመሪያ ምዝገባ
2. የምዝገባ ዕድሳት በየሁለት አመት ተኩል
3. የአገልግሎት መቋረጥ
• አገልግሎቱ በተቋረጠ በ30 ቀናት ውስጥ
• አገልግሎት ከተቋረጠ ከ2 ዓመት በኋላ -የመጨረሻ ምዝገባ
ሃብትን የማሳወቅና የማስመዝገብ ግዴታ
ማንኛውም ተሿሚ፣ ተመራጭ ወይም የመንግሥት ሠራተኛ፡-
• በራሱና በቤተሰቡ ባለቤትነት ወይም ይዞታ ሥር የሚገኝ ሀብትን ፣ እና
• የራሱንና የቤተሰቡን የገቢ ምንጮች፣ የማሳወቅና የማስመዝገብ ግዴታ አለበት፡፡
• ሃብት ምዝገባ የሚካተቱ ሃብቶች
ደመወዝና አበል
- ወርሀዊ ደመወዝ /ግሮስ /
- ወርሀዊ አበል(የቤት፣የትራንስፖርት፣የነዳጅ፣ የቀለብ አበልወዘተ)
• የማይንቀሳቀስ ሀብት
ህንፃ /ቤት ፣የቤት መስሪያ ቦታ ፣የመሬት ይዞታ / ከኢንቨስትመንት ጋር የተያያዘ/፣የአርሶ/አርብቶ አደር የመሬት ይዞታ ፣የንግድ ድርጅ
• የሚንቀሳቀስ ሀብት
እንስሳት፣ ተሽከርካሪ ፣የግንባታና የግብርና መሣሪያዎች
ሌሎች ሀብቶች
ጀልባ ፣የአእምሮ ሀብቶች፣ወዘተ
ልዩ ልዩ ገቢዎች
• ከውጭ አገር የተገኘ ገቢ፣ ከንግድ የተገኘ ገቢ፣ ከአክስዮን /ቦንድ የተገኘ ገቢ/ ፣በባንክ /በብድር ቁጠባ ማህበር ያለ ተቀማጭ ገንዘብና ወሊድ ፣ከቤት ኪራይ የሚገኝ ገቢ፣ከሎተሪ የሚገኝ ገቢ፣ ከውጭ ሀገር ጉዞና ሌሎች፣
• ህጋዊ ዕዳ / ያበደርነው ሳይሆን በህጋዊ መልኩ የተበደርነው/
በሃብት ምዝገባ የማይካተቱ ሃብቶች
• የቤት ዕቃዎችና የግል መገልገያዎች፤
• ከጡረታ የሚገኝ ገቢ፡፡
• በውርስ ተገኝቶ በጋራ የተያዘና ለወራሾቹ የግል አገልግሎት የሚውል ንብረት፤
ነገር ግን በጋራ የተያዘው ንብረት በወራሾች መካከል እንደተከፋፈለ ድርሻው መመዝገብ አለበት

ለመላው  የእስልምና እምነት ተከታዮች  እንኳን  ለ ለአረፋ  በዓል አደረሳቹሁ !!
27/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ ለአረፋ በዓል አደረሳቹሁ !!

25/05/2026
25/05/2026

በድጋሚ የወጣ የስራ ማስታወቂያ

ኮሚሽኑ ከስር በተጠቀሰው የስራ መደብ ላይ አመልካቾችንን በኮንትራት አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል። በመሆኑን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ግንቦት 12/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 የስራ ቀናት መመዝገብ ትችላላችሁ።

Address

Asmara Road
Debre Birhan
2510116375964

Telephone

+251920082315

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to አብክመ ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደብረ ብርሃን ቅርንጫፍ:

Share