ደብረብርሃን ከተማ አፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Debre Birhan
  • ደብረብርሃን ከተማ አፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት

ደብረብርሃን ከተማ አፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የደ/ብርሃን ከተማ በአፄ ዘርያእቆብ ዘመነ መንግስት በ1446 ዓ.ም የተቆረቆረች ጥንታዊ ከተማ ነች፡፡

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ59 ሺህ በላይ በጎፈቃደኞች በማሳተፍ ከ70 ሚሊየን ብር በላይ ሀብት ለማዳን መታቀዱ ተገለጸበደብረብርሃን ከተማ የ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎ...
20/06/2024

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ59 ሺህ በላይ በጎፈቃደኞች በማሳተፍ ከ70 ሚሊየን ብር በላይ ሀብት ለማዳን መታቀዱ ተገለጸ

በደብረብርሃን ከተማ የ2016 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በንቅናቄ በይፋ ተጀመረ

የደብረብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸት እንደገለጹት በ2015/16 የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣የአረጋውያን ቤት ጥገና፣የተፋሰስ ጽዳት፣ደም ልገሳ፣የማጠናከሪያ ትምህርትና ሌሎች በርካታ ተግባራትን ማከናወን መቻሉን አስታውሰዋል፡፡

በ2016/17 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ59 ሺህ በላይ በጎ ፈቃደኞች በማሳተፉ ከ154 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ ስራው መጀመሩን አብራርተዋል፡፡በዚህም ከ70 ሚሊየን ብር በላይ ሀብት ማዳን እንደሚቻልም አስረድተዋል፡፡

በተለይም ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ቤት እንደሚገነባ፣የአቅመ ደካማ ቤቶች በስፋት እንደሚጠገኑ፣ደም ልገሳ፣ከተማን የማስዋብና ደም ልገሳ፣የአረንጓዴና የኮሪደር ልማት፣የተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርትና ሌሎች የልማት ስራዎች እንደሚከናወኑ አብራርተዋል፡፡

ከተማው ባለፈው ዓመት በበጎ ፈቃድ ስራ ከክልሉ 1ኛ መወጥቶ ዋንጫ መሸለሙን አስታውሰዋል፡፡በዚህ ዓመትም ከባለፈው የበለጠ ስራ ለማከናወን ዛሬ በንቅናቄ ስራው መጀመሩን አመልክተዋል፡፡

በመሆኑም የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ችግር የሚፈታ በመሆኑ በስራው ሁሉም ሰው በመሳተፍ የድርሻውን ኃላፊነት እንዲወጣ ከንቲባ በድሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ቤታቸው የሚጠገንላቸው ወይዘሮ ቀለመወርቅ አክሊሉ በሰጡት አስተያየት የቤታቸው ቆርቆሮ አርጅቶ ስለተቀዳደደ ክረምት በመጣ ቁጥር ብዙ መቸገራቸውን አስረድተዋል፡፡

መንግስት ችግራቸውን አይቶ ዛሬ ቤታቸውን ስለጠገነላቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡

በአጼ ዘረያዕቆብ ክፍለ ከተማ በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር የአካባቢ ጽዳት ዘመቻ ተግባራዊ ተደረገ፡፡በአጼ ዘረያዕቆብ ክፍለ ከተማ በደብረኤባ ቀበሌ በወጣትና በሴት አደረጃጀት እንዲሁም በ...
13/07/2023

በአጼ ዘረያዕቆብ ክፍለ ከተማ በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር የአካባቢ ጽዳት ዘመቻ ተግባራዊ ተደረገ፡፡

በአጼ ዘረያዕቆብ ክፍለ ከተማ በደብረኤባ ቀበሌ በወጣትና በሴት አደረጃጀት እንዲሁም በሴፍትነት ተጠቃሚዎች እና በአካባቢው ማህበረሰብ ቅንጅት ነው የጽዳት ዘመቻው የተደረገው

የቀበሌውን ማህበረሰብ ፣ የወጣት እና የሴት አደረጃጀት እንዲሁም የሴፍትኔት ተጠቃሚ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማስተሳሰር የአካባቢ ጽዳት መካሄዱንም ነው የገለጹት የደብረኤባ ቀበሌ ስራ አስኪጅ አቶ አብርሃም ተፈራ

በቀበሌው በሳምንት ሁለት ቀን ማክሰኞና ሀሙስ ቋሚ የጽዳት ቀን መያዙንም አቶ አብርሃም ጠቁመዋል፡፡

በጽዳቱም የተፋሰስ ቦይዎች፣ የአረንጓዴ አካፋይ መንገዶች እንዲሁም መደበኛ የቆሻሻ ብዛት ያለባቸው ቦታዎች መጸዳታቸውን አንስተዋል ስራ አስኪጁ

የደብረኤባ ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጋሻው ከበደ እንዳነሱትም ከነዋሪው ማህበረሰብ ከ6ሺ ብር በላይ በማሰባሰብ የተጸዳውን ቆሻሻ በመኪና እንዲነሳ አድርገናል አሁንም በሌሎች ጽዳት ፕሮግራሞችንም ተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት

የአካባቢ ጽዳት ዘመቻ በክረምት በጎ ፈቃድ ስራችን በትኩረት የምንሰራው ስራ ነው ብለዋል ዋና አስተዳዳሪው

የአጼ ዘረያዕቆብ ክፍለ ከተማ ጽዳትና ውበት አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ቤት ኀላፊ ወ/ሮ እጥፍወርቅ ደጀኔ እንዳሉትም ለማህበረሰባችን ግንዛቤ በመፍጠር በጽዳት የተዋጣለት ሞዴል ቀጠናን ለመፍጠር ይሰራልም ብለዋል፡፡

የተዋጣለት ያደገ ከተማ ለመፍጠር ሁሉም ነዋሪ አካባቢውን 20/50 ሜትር ራዲዬስ ቀጣናውን ያለማንም አስገዳጅነት ማጽዳት ሲችል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በጽዳት ዘመቻወም የምድረገነት ቀበሌ የደብረኢባ ቀበሌ ወጣትና ሴት አደረጃጀቶች እንዲሁም የሴፍትኔት ተጠቃሚዎች ተሳታፊ ነበሩ፡፡

•~•~•

አመራሩ  ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መፍታት ቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ ።ደብረ ብረሀን :-ሰኔ 19/2015ዓ.ም (ደብኮ)አመ...
26/06/2023

አመራሩ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መፍታት ቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ ።
ደብረ ብረሀን :-ሰኔ 19/2015ዓ.ም (ደብኮ)አመራሩ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መፍታት ተቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን እንደሚገባ ተገለፀ ።

በደብረብርሃን ከተማ መፍጠንና መፍጠር የወል እውነቶችን የማፅናት ቀጣይ የትግል ምዕራፍ በሚል መሪ ሃሳብ ከከተማ እስከ ቀበሌ ላሉ የፓርቲ አመራሮች ሲሰጥ የሰነበተው ስልጠና ተጠናቀቀ።

የደብረብርሃን ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ጌታቸው እንደገለጹት አመራሩ በመልካም ስነምግባር ህብረተሰቡን በቅንነት ማገልገል እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

የከተማው ሠላም በዘላቂነት ተጠብቆ እንዲዘልቅ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን ሆኖ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የማዳበሪያ አቅርቦት፣የኑሮ ውድነት፣የሥራ አጥነት ችግር እንዲፈታ በየደረጃው እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

የደብረብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ካሳሁን እምቢአለ መድረኩን ሲያጠቃልሉ እንደተናገሩት ስርቆትን በጽናት ታግሎ በማስተካከል እና የአመራር አንድነት በማጠናከር ለህዝብና ለመንግስት የሚጠቅም ተጨባጭ ስራ መፈጸም እንደሚጠበቅ አሳውቀዋል፡፡
በተለይም አመራሩ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መፍታት ቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡አመራር በተግባር ሰርቶ ውጤት ማምጣት እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
አሁን እንደ ሀገር ያለውን ዘርፈ ብዙ ችግሮች በመፍታት ለሀገረ መንግስት ግንባታ የምክክር ኮሚሽኑ ስራ ፋይዳው የጎላ መሆኑን አንስተው ለተግባራዊነቱ ሁሉም ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አመልክተዋል፡፡

በደብረ ብርሃን ከተማ ከ57 ሺህ በላይ ወጣቶችን በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማሳተፍ መታቀዱ ተገለጸበጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ -2 በሚል መሪ መልዕክት የደብረ ብርሃን ከተማ ወጣትና ስፖር...
23/06/2023

በደብረ ብርሃን ከተማ ከ57 ሺህ በላይ ወጣቶችን በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማሳተፍ መታቀዱ ተገለጸ

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ -2 በሚል መሪ መልዕክት የደብረ ብርሃን ከተማ ወጣትና ስፖርት መምሪያ የ2015ዓ.ም የክረምት በጎፈቃድ አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር እያካሄደ ይገኛል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ወጣትና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ኢንጂነር ቶማስ መኮንን የእንኳን ደህና መጣችሁ የመከፈቻ ንግግር አድርገዋል።

በ2014ዓ.ም በክረምት በጎፈቃድ አገልግሎት በክልሉ ከሚገኙ ከተሞች 1ኛ መውጣቱን አንስተዋል።በዚህ ዓመትም በተመሳሳይ የላቀ አፈፃጸም ለማስመዝገብ ተቀናጅቶ መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
በመጪው ክረምት በደብረብርሃን ከተማ 57 ሺህ 540 ወጣቶችን በማሳተፍ 57 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ግምት ያለው ሃብት ከወጪ ማዳን እንደሚቻል ተገልጿል።

በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳዳር ትጥቅ ይዘው ህውከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ የተደረሰባቸው ግለሰቦች በተኩስ ልውውጥ ከነ ጦርመሳሪያቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ። በከተማ አስተዳደሩ በእቴጌ ...
23/06/2023

በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳዳር ትጥቅ ይዘው ህውከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ የተደረሰባቸው ግለሰቦች በተኩስ ልውውጥ ከነ ጦርመሳሪያቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ።

በከተማ አስተዳደሩ በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ሳሪያ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቦሰና ምንጭ በሚባል አካባቢ ቁጥራቸዉ በርከት ያሉ ሰዎች በጦር መሳሪያ የተደገፈ ህውከትና ብጥብጥ ለመፍጠር እየተዘጋጁ መሆኑ መረጃው ለጸጥታ ሀይሉ ይደርሳል።
ጉዳዩን በመረጃ ያጠናከረው የጸጥታ ሀይሉ ሰኔ 14 ለ15/2015 ዓ/ም ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ድንገተኛ የተቀናጀ ስምሪት ተደርጎ ከሰዓታት ከባድ የተኩስ ምልልስ በኋላ የጥፋት ግለሰቦች ከነ መሳሪያቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በአካባቢው የከፋ ጉዳት እንዳይፈጠር የፀጥታ ሀይሉ እጅግ በከፍተኛ ጥንቃቄ በወታደራዊ ጥበብ ያለምንም ኪሳራ ያለ መስዕዋትነት ድል ማድረግ ችሏል።

በኦፕሬሽኑ 26 ግለሰቦች ከነ ትጥቃቸው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን አራት እስናይፐር ከ1261 ጥይት ጋር፣አንድ ድሽቃ ከ490 ጥይት ጋር፣5 ክላሽ ከሰባት ካርታና 530 ጥይት ጋር፣ 2 ብሬን፣ 3 የእጅ ቦንብ፣ ሁለት የቱርክ ሽጉጥ ከመሰል ስምንት ጥይት ጋር በቁጥጥር ስር ውሏል።

መረጃው የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ነዉ

የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚዛናዊና ፈጣን  መረጃ ለህብረተሰቡ በማድረስ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ ።ደብረ ብረሀን :- ሰኔ 13/2015ዓ.ም (ደብኮ)የኮሙንኬሽን ባለሙያዎች ሚዛናዊ...
20/06/2023

የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚዛናዊና ፈጣን መረጃ ለህብረተሰቡ በማድረስ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ ።
ደብረ ብረሀን :- ሰኔ 13/2015ዓ.ም (ደብኮ)የኮሙንኬሽን ባለሙያዎች ሚዛናዊና ፈጣን መረጃ ለህብረተሰቡ በማድረስ ሀላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለፀ ።
የደብረ ብርሃን ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ለኮሙኒኬሽን እና የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች በዜና አዘገጃጀት እና አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ሰጠ ።
ስልጠናው የዜና ዕቅድ፣ይዘት አመራረጥ፣አጭር ዜና አዘገጃጀት እና አጠቃቀም ዙሪያ ትኩረት ያደረገ ሲሆን በንድፈ ሀሳብ ተተንትኖ፤ በተግባር ልምምድ ተደግፎ ተሰጥቷል፡፡
ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ከስልጠናው መጠቀማቸውንና ደስተኛ መሆናቸውን ጠቅሰው ክፍተታቸውን የሞላ፣ለቀጣይ ስራ አቅም የሚገነባ መሆኑን አንስተዋል፡፡ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት አስቦ ስላዘጋጀው አመስግነው ቀጣይነት እንዲኖረውም ጠይቀዋል፡፡
የደብረብርሃን ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ መቅደስ ብዙነህ ስልጠናውን ሲያጠቃልሉ እንደተናገሩት እስካሁን የነበሩ ክፍተቶችን አርሞ ጥንካሬዎችን አጎልብቶ ተቀናጅቶ መስራት ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
በቀጣይ የኮሙኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ትክክለኛ፣ሚዛናዊና ፈጣን መረጃ ለህብረተሰቡ በማድረስ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

የአጼ ዘረያዕቆብ ክፍለ ከተማ የኡራኤል ቀበሌ አስተዳደር የውስጥ ለውስጥ የተፋሰስ ስራዎችን ከቀበሌው ልዩ ልዩ የማህበሠሰብ ክፍሎች  ጋር በመሆን ጥገና ማድረጉን አስተወቀ። በአፄ ዘርያዕቆብ ...
15/06/2023

የአጼ ዘረያዕቆብ ክፍለ ከተማ የኡራኤል ቀበሌ አስተዳደር የውስጥ ለውስጥ የተፋሰስ ስራዎችን ከቀበሌው ልዩ ልዩ የማህበሠሰብ ክፍሎች ጋር በመሆን ጥገና ማድረጉን አስተወቀ።

በአፄ ዘርያዕቆብ ክፍለ ከተማ በኡራኤል ቀበሌ አስተዳደር በወጣት አደረጃጀት፣በማህበረሰብ እና በቀበሌው አመራሮች ቅንጅት የውስጥ ለውስጥ የተፋሰስ ጥገና ተግባራትን ተግባራዊ መደረጉን ነው አስተዳደሩ የገለጸው

በቀጣይ በሚኖር የክረምት በጉ ፍቃድ ስራ ሁሉም የቀበሌውን ወጣቶች እንዲሁም ማህበረሰብ በጋራ በመተጋገዝ አካባቢውን የፀዳ ማደረግ ፣ተፋሰሶችን ከመደፈን ማዳን፣ የአረጋውያንና የአቀመ ደካሞችን የመኖሪያ ቤቶችኝ የመጠገን እንዲሁም የመስራት፣ መሸጋገሪያ ድልድዮችን የማጠናከር እና ሌሎችም በርካታ የሚከናወኑ ተግባራት መኖራቸውን የኡራኤል ቀበሌ አስተዳደር አስታውቋል።

ስለሆነም በዚህ የበጉ ተግባር ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆን የኡራኤል ወጣት ሊግ ሰብሳቢ ወጣት አማኑኤል ንጉሴ ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ ግሩም በላይነህ የቀበሌው የማህበራዊ ዘርፍ ኃላፊ በቀበሌው በርካታ የበጉ ፍቃድ ስራዎችን እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

ወጣቶች በየትምህርት ዘርፋቸው በቀበሌ አስተዳደሩ እየመጡ እንዲመዘገቡም ጥሪ አቅርበዋል

"ፈተናዎችን ወደ እድል በመቀየር ህዝባችንን እናሻግራለን" በሚል መሪ- ቃል የአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ የመንግሰት ሰራተኛ አባላት ኮንፈረንስ  መካሄድ ጀመረ። በኮንፈረንሱ የእንኳን ደህና...
01/06/2023

"ፈተናዎችን ወደ እድል በመቀየር ህዝባችንን እናሻግራለን" በሚል መሪ- ቃል የአፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ የመንግሰት ሰራተኛ አባላት ኮንፈረንስ መካሄድ ጀመረ።

በኮንፈረንሱ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር አረንጓዴ ልማት ተጠሪ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ደበበ እሸቴ በክልላችን የተከሰተውን ውሰብሰብ ችግር ለመፍታትና አንድነታችንን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያሰችል እንዲሁም የችግሮች መፍትሄ ለማመንጨት የአባላት ኮንፈረንስ ሚና የጎላ ነው ብለዋል።

ሃላፊው አክለው እንደገለፁትም በአማራ ክልል የሚፈጠሩ ችግሮችን በዴሞክራሲያዊ መንገድና በውይይት በመፍታት ችግሮችን ወደ ዕድል በመቀየር ህዝባችንን ወደ ብልፅግና ማሻገር ይገባል ነው ያሉት

ሃላፊው አክለውም እንደተነገሩት የችግሮች ሁሉ መፍትሔ ዴሞክራሲያዊ የሆነ ውይይት እና ሃሳብን በሃሳብ ማሸነፍ ሲቻል ብቻ ነው ብለዋል።

በኮንፈረንሱ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይም የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኀላፊ በነበሩት በአቶ ግርማ የሽጥላ እና አብረዋቸው ለተሰዉ የስራ ባልደረቦቻቸው የሻማ ማብራትና የህሊና ፀሎት በማድረግ ኮንፍረንሱ ተጀምሯል።

የመውያያ ሰነዱ ቀርቦ ውይይት እየተደረገበት ነው።

"የጎሃ ቃልኪዳናችን የከፍታችን ልክ ፤ ቃላችንን ፈፅመን ከፍታው ላይ እንገናኝ"

‹‹የኢትዮጵያ መዳኛ ትርክት አብሮነት፣ወንድማማችነትና በጋራ ሀገርን የመገንባት ትርክት ነው፡፡ ››  አቶ ግዛቸው ሙሉነህ***የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ በክልሉ የሚገኙ የዞንና የከተማ አስ...
22/05/2023

‹‹የኢትዮጵያ መዳኛ ትርክት አብሮነት፣ወንድማማችነትና በጋራ ሀገርን የመገንባት ትርክት ነው፡፡ ›› አቶ ግዛቸው ሙሉነህ
***
የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ በክልሉ የሚገኙ የዞንና የከተማ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ወቅታዊ ክልላዊ ሁኔታዎችን መሰረት ያደረገ ውይይት በባህር ዳር ማካሄድ ጀምሯል፡፡

በውይይቱ የተገኙት የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰት ቀውስ የአመራር መናጋትን ይፈጥራል፤ በዚህ ምክንያት የመልካም አስተዳር ችግሮችን የሚያባብስ እና የአካባቢን ሠላም የሚያደፈርስ በመሆኑ ለዚህ የሚመጥን የሚዲያና የተግባቦት ሥራ በሁሉም አካባቢዎች በአግባቡ መሰራት አለበት ብለዋል፡፡

አሁን ላይ በአገራችንም ሆነ በክልሉ ብዙ አይነት የትርክት መዛነፍ እንዳለ ያነሱት ቢሮ ኃላፊው ሀገርን ሊያድን የሚችለውን ትርክት ማጽናት ያስፈልጋል ብለዋል ፡፡

‹‹የኢትዮጵያ መዳኛ ትርክት አብሮነት፣ወንድማማችነትና በጋራ ሀገርን የመገንባት፣ኢኮኖሚን የማሳደግ ትርክት ነው›› ያሉት አቶ ግዛቸው ከዚህ ውጪ ያሉ ትርክቶች ሀገርን የሚያፈርሱና ለጠላት አጋልጠው የሚሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት አድርጎ የተግባቦት ሥራ አለመስራት በኮሙኒኬሽን መዋቅሩ የሚታይ የተግባቦት ዝንፈት መሆኑን የገለጹት ቢሮ ኃፊው የአብሮነት እሳቤዎችን በሚያጎሉ ክልላዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በትኩረት መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል፡፡

ለህዝቡ መድረስ የሚገባውን ወቅታዊ መረጃ ተግባቦትን በሚያጠናክር መልኩ ሁሉንም የመገናኛ አማራጮች በመጠቀም የኮሙኒኬሽን መዋቅሩ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡


አማራ ክልል ኮሙኒኬሽን

ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በደቡብ ወሎ ዞን አማራ ሳይንት ወረዳ የምትገኝ ታላቅ ደብር ናት። ተድባበ ...
08/05/2023

ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም

ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በደቡብ ወሎ ዞን አማራ ሳይንት ወረዳ የምትገኝ ታላቅ ደብር ናት።

ተድባበ ማርያም ከደሴ በ225 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ከአማራ ሳይንት ርዕሰ ከተማ አጅባር በ25 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች።

ደብሯ ዙሪያዋ ገደል ሆኖ በግራና ቀኝ በጉንዳና ገዳማይ ጅረቶች እንዲሁም በሽሎ ወንዝ ታጅባ የምትገኝ ውብ የታሪክ አምባ ነች፡፡ አምባው ለመውጣት 12 በሮች አሉት፡፡ ፊት በር፣ ቦካ፣ ገተም፣ ሞገራ ግራኝ፣ ታሪኳ፣ የዘንጌ፣ አሳስት፣ አጎና፣ አምጣ ፈረሴን፣ አህያ መደብለያና የጌለት ናቸው፡፡ አምባው ላይ በዮሐንስ ራዕይ ላይ የ7ቱ ቤተ-ክርስቲያን አምሳያ 7 ቤተ ክርስቲያኖች አሉ፡፡

በኢትዮጵያ መስዋዕተ ኦሪት ከተሰዋባቸው አራት ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት አክሱም ጽዮን፣ ተድባበ ማሪያም፣ መርጦ ለማሪያምና ጣና ቂርቆስ መካከል አንዷ ናት፡፡ በአመሰራረት ቅደም ተከል ከአክሱም ጽዮን ቀጥላ ሁለተኛዋ ጥንታዊና ብቸኛ ባለታሪክ ደብር ናት፡፡

ደብሯ ከክርስቶስ ልደት በፊት የተመሰረተች በመሆኗ ከ3 ሺህ ዓመታት በላይ ዕድሜ አስቆጥራለች፡፡ የተሰራችውም በቀዳማዊ ዳዊት የወንድም ልጅ አሚናዳብ አማካኝነት በ982ዓ.ዓ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ቤተ-ክርስቲያኗ 9 ጊዜ ፈርሶ ተሰርቷል፡፡ ብዙ ጊዜም ተጠግኗል፡፡

የአፄ ገላውዲዮስ አጽም ያረፈው በዚህ ደብር እንቁላል ግንብ በሚባለው ነው፡፡ በደብሯ በርካታ ቅርሶች ያሉ ሲሆን ንዋየ ቅድሳት፣ የብራና መጽሃፍት ገድሎች፣ ስዕሎች፣ የነገስታት ዘውዶች፣ ወንበርና አልባሳት፣ የነገስታት አጽም፣ የጥንት ነገስታት የጦር መሳሪያ ወዘተ ይገኛሉ፡፡ በድንጋይ ግድግዳና በቆርቆሮ ክዳን የተሰራ ነው፡፡

ዓመታዊ ክብረ በዓሏ አጼ ገላውዲዮስ ታቦተ ልደቷን ከእየሩሳሌም አስመጥተው ወደ ቤተ-ክርስቲያኑ ያስገቡበትን ቀን መነሻ በማድረግ ግንቦት 1 ቀን በልደታ እንዲሁም ግንቦት 2 ቀን ይከበራል፡፡

ዘገባው፦ የደቡብ ወሎ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ነው።

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ኮማንድ ፖስት የከተማዉን ፀጥታ ለማስጠበቅ ጥሎት የነበረውን ገደብ በከፊል ማንሳቱን አስታወቀ፡፡ሚያዚያ 16/2015 ዓ.ም (ደብኮ) የደብረ ብረሀን ከ...
24/04/2023

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ኮማንድ ፖስት የከተማዉን ፀጥታ ለማስጠበቅ ጥሎት የነበረውን ገደብ በከፊል ማንሳቱን አስታወቀ፡፡

ሚያዚያ 16/2015 ዓ.ም (ደብኮ) የደብረ ብረሀን ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ኮማንድ ፖስት የከተማ አስተዳደሩን ሰላም ለማረጋገጥና የህግ የበላይነት ለማስከበር አስቀምጧቸው የነበሩ ክልከላዎች በከፊል ማንሳቱን አስታውቋል፡፡

ኮማንድ ፖስቱ ከሚያዚያ 2 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን የታወጁ ክልከላዎችን በማስፈፀም ከተማዋ ወደቀድሞ ሰላሟ እንድትመለስ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የሃይማኖት አባቶች፣የሀገር ሽማግሌዎች፣ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ለሁሉም የከተማው የፀጥታ መዋቅር አባላት እና ለከተማው ነዋሪዎች በሙሉ ምስጋና በማቅረብ የተጣሉ ክልከላዎችን በከፊል ከዛሬ ጀምሮ መነሳታቸውን አስታውቋል፡፡

የቀጠሉ ክልከላዎች

1. በከተማ አስተዳደሩ ከተፈቀደለት የፀጥታ አካል ውጪ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ክልክል ነው፡፡
2. የሰራዊቱን ሚሊተሪ አልባሳት ከሰራዊቱ አባላት ውጪ ለብሶ መንቀሳቀስ ክልክል ነው
3. ያለ ከተማ አስተዳደሩ ፈቃድ በተለያዩ አካባዎች በቡድን መሰባሰብ ለከተማው የሠላም ችግር መንስኤ ስለሚሆን ፍፁም ተከለከለ ነው፡፡

ከተማዋም በአሁኑ ሰዓት የቀደመ ሰላሟ ተመልሶ በፍፁም መረጋጋት ውስጥ ያለች እና ሁሉም የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መደበኛ ስራቸውን እያከናወኑ የሚገኙ በመሆኑ ሰላም ወዳዱ የደብረ ብርሃን ህዝብም አሁን ያለውን ሰላም እንዲያስቅጥል እና ማንኛውንም የተለየና አዲስ እንግዳ የሆነ ነገር ሲያጋጥም እንደተለመደው ለፀጥታ ተቋማት ጥቆማ እንዲሰጥ መልዕክት ተላልፏል፡፡

የተከሰተውን ሀገራዊና ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክተው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የተከሰተው ችግር በውይይትና በሠላም...
11/04/2023

የተከሰተውን ሀገራዊና ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክተው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የተከሰተው ችግር በውይይትና በሠላም እንዲፈታ ጥሪ አቀረቡ።

ሚያዚያ 03/2015 ዓ.ም (ደብኮ) ብፁዕነታቸው የሰላም ችግሩም በሃይማኖት አባቶችና በሀገር ሽማግሌዎች በውይይት እና በመካከር ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ እንደተናገሩት ይህ ወቅት በመላው ኢትዮጵያ በክርስትና እና በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ታላቅ የጾምና የጸሎት ወቅት ሲሆን በተለይም በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ሰሙነ ሕማማት በመሆኑ ሕዝበ ክርስቲያኑ ለጸሎት፣ ለጾምና ለስግደት ወደ ቤተ ክርስቲያን ከወትሮው በተለየ መልኩ የሚመጣበት እና የሕዝቡ ፍሰት የሚጨምርበት ወቅት ነው ብለዋል።

ይሁን እንጂ በዚህ ከፍተኛ የጾምና የጸሎት ወቅት እንደሀገርም ሆነ እንደ ደብረ ብርሃን ከተማ የሰላም ችግር ያጋጠመን በመሆኑ አዝነናል ብለዋል።

ዞኑም ሆነ ከተማችን ደብረ ብርሃን በፈጣን ልማትና እድገት ላይ የሚገኙ ቢሆንም በዚህ ሰዓት የሰላም እጦት ያጋጠመ በመሆኑ ይህን የተከሰተ ችግር በመፍታት በኩል በተለይም መንግስት በሚመራው ህዝብ ላይ ጉዳት እንዳይደርስ በሆደ ሰፊነት ችግሩን እንዲፈታ አሳስበዋል።

ብፁዕነታቸው አያይዘውም አሁን ያለነው ፆም፣ ጸሎትና ስግደት ላይ ቢሆንም የሰላም ቀውስ የገጠመን በመሆኑ በዞኑ አብያተ ክርስቲያናት ያላችሁ ሁሉ ከወትሮው በተለየ መልኩ እስከ ስቅለቱ ድረስ በልቅሶ፣ በዕንባና በመሪር ሀዘን ፀሎተ ምህላን እንድታከናውኑ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ብፁዕነታቸው የተከሰተውን የሰላም እጦት ችግር በሃይማኖት አባቶችና በሀገር ሽማግሌዎች በውይይት እና በመካከር ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ተጨማሪየ(ደብከ)የተለያዩ መረጃዎችን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ይጎብኙ
ፌስቡክhttps://www.facebook.com/DebreBirehancommunication
ዩቱዩብhttps://www.youtube.com/c/DebreBirhanCommunication
በቴሌግራምhttps://t.me/+0D4s3zCu-G4yM2Nk
ትዊተርhttps://twitter.com/birhan_debre
ዌብሳይትhttps://www.dbcity.gov.et/
እባክዎንshareእና invite ማድረግዎንእንዳይረሱት

Address

Debre Birhan
1000

Telephone

+251911776619

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ደብረብርሃን ከተማ አፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ደብረብርሃን ከተማ አፄ ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት:

Share