13/12/2025
የአሳግርት ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ከአስተዳደር አይሲቲ የስራ ቡድን ጋር በመተባበር ለትምህርት አመራር ፣ ለባለሙያዎች መረጃ አስተዳደር ሲስተም ዲጂታላይዜሽን ዙሪያ በቂ ስልጠና በመስጠት በየተቋማቸው የተማሪ፣የመምህር ፣እንዲሁም የትምህርት ተቋማቸውን አጠቃላይ የትምህርት መረጃዎች ወደ emis.moe.gov.et ሲስተም በአግባቡ ማስገባት እንዲችሉ ስልጠና ተሰጥቷል። ስልጠናው ለመንግስት 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መንግስታዊ ላልሆኑ ት/ቤቶች ትላንትናና ዛሬን ጨምሮ በተግባር የተደገፈ ስልጠና መስጠቱን አስታወቀ።
(ታህሳስ 3/2017 ዓ.ም) ስልጠናው በዋናነት በአጠቃላይ ትምህርት መረጃ አስተዳደር ሲስተም ዲጂታላይዜሽን አተገባበር እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ስልጠና ወስደው በየትምህርት ቤቶቻቸው የተማሪ፣ የመምህር ፣ የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ አጠቃላይ የትምህርት መረጃዎችን ወደ emis.moe.gov.et ሲስተም እንዲያስገቡ ለማስቻል ለሁለት ቀን ተሠጥቷል በማጠቃለያ የአሳግርት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አላዩ ብሬ አስተዳደራቸው በየትምህርት ተቋማቱ በሚያደርገው ድጋፍ እና ክትትል የሚያረጋግጥ መሆኑን ጠቁመው ሰልጣኞቹ የወሰዱትን ስልጠና መሰረት በማድረግ መረጃዎቹን ወደሲስተሙ በማስገባት ጥራቱ የተጠበቀ እና በቴክኖሎጂ የተደገፈ የትምህርት መረጃ ለሚመለከተው አካል በአግባቡ ተደራሽ እንዲሆን ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲውጡ ጥሪ አስተላልፈዋል።