North Shoa Zone Land Department

North Shoa Zone Land Department Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from North Shoa Zone Land Department, Government Organization, Debre birehan, Debre Birhan.

የ8 ወራት የመሬት መምሪያ እቅድ አፈጻጸም  እና የቀጣይ  አቅጣጫ በዙም ተካሂዷል1. የተቋም ግንባታ ስራችን ከወረዳ እስከ ቀበሌያለው ሠራተኛ ሥራ ላይ ነወይ ከሆነ በአደረጃጀት  እየተመራ ሥ...
19/03/2026

የ8 ወራት የመሬት መምሪያ እቅድ አፈጻጸም እና የቀጣይ አቅጣጫ በዙም ተካሂዷል
1. የተቋም ግንባታ ስራችን ከወረዳ እስከ ቀበሌያለው ሠራተኛ ሥራ ላይ ነወይ ከሆነ በአደረጃጀት እየተመራ ሥለመሆኑና የመጣ ለውጥ በተመለከተ ሥራን መሠረት ያደረገ ንግግር እንዲደረግ ተቀምጧል 2. KPI መሠረት ያደረገ የተግባራት አፈጻጸም መገምገም/ የመሬት አስተዳደር ቡድን /የአጠቃቀም የካሣትክ እና ቀበሌ ማእከል እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን የተመለከተ ግምገማና አቅጣጫ ተሠጥቷል
3.ልዩ ልዩ የኢንሼቲቭ ሥራዎች አፈፃፀም
ዲጅታል መታወቂያ
የገጠር ኮሪደር ትግበራ
የኢትዮ ኮደርስ አፈፃፀም
4.የሁለተኛ ይዞታ ማረጋገጫ ሠርተፊኬት አስይዞ ብድር ማሠጠት የተመለመለ የተበደረ የገንዘብ መጠን አበዳሪ ተቋም ወዘተ
5.የማሣ ማሻገር እና የመረጃ ማጥራት አፈፃፀም
5. የመሬት ግብይት አፈጻጸም
6.አጠቃላይ የ የ3ኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀም ሪፖርት ዝግጅት ምን እንደሚመስል /ሁሉም ወረዳና ከተማ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ጥንቃቄ የተሞላበት መረጃ እንዲሠሩ አቅጣጫ ተሠጥቷል። 7.የበጀት አጠቃቀም እና የከተማ መሬት ልማት ቡድን ሥራ ማስገባት ተገምግሞ አቅጣጫ ተሠጥቷል

የሰ/ሸዋ ዞን መሬት መምሪያ ከመጋቢት 2/2018 ዓ/ም እስከ መጋቢት 4/2018 ዓ/ም ድረስ ከደ/ብርሃንዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በሰሜን ሸዋ ዞን እና በሁሉም ወረዳዎች ለሚገኙ 50 የመሬት...
15/03/2026

የሰ/ሸዋ ዞን መሬት መምሪያ ከመጋቢት 2/2018 ዓ/ም እስከ መጋቢት 4/2018 ዓ/ም ድረስ ከደ/ብርሃን
ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በሰሜን ሸዋ ዞን እና በሁሉም ወረዳዎች ለሚገኙ 50 የመሬት አጠቃቀም ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል።

በዚህ ስልጠና መክፈቻ ላይ የደ/ብርሃን ዩኒቨርስቲ የማህበረሰብ ህብረት ዳሪክቶሬት ዳሬክተር የሆኑት ወ/ሮ መቅደስ ጌራወርቅ እንደተናገሩት መሬትን በውጤታማነት ጥቅም ላይ ለማዋል የመሬት
አጠቃቀም እቅድ ማዘጋጀት ያስፈልጋል። ይህን የመሬት አጠቃቀም እቅድ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ለማዘጋጀት
ደግሞ አሁን ለስልጣኞች የሚሰጠው የ GIS ስልጠና በጣም አስፈላጊ በመሆኑ የዚህ ስልጠና ተሳታፊ
ባለሙያዎች ስልጠናውን በትኩረት መከታተል እንዳለባቸው በማሳሰብ ስለጠናውን ከፍተዋል።

ስልጠናው በተግባር የተደገፈና ሰልጣኙ በቡድንና በግል ስራዎች እየተገመገመ የሰልጠናው ሂደት ቀጥሎ በመጨረሻም እያንዳንዱ ሰልጣኝ ባገኘው የ GIS ክህሎት የራሱን ወረዳና ቀበሌዎች የተለያዩ ካርታዎች ሰርቶ እዲያሳይ ተደርጎ ስልጠናው ተጠናቋል። በመጨረሻም የሰርተፊኬት ሽልማት ለሁሉም ሰልጣኞች ተሰጥቷል።
በዚህ የሰርተፊኬት ማጠቃላያ ፕሮግራም ላይ አሰልጣኝ የዩኒቨርስቲው ዶክተሮች፣ አጠቃላይ ሰልጣኞች እና የሰሜን ሸዋ ዞን መሬት መምሪያ ማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች የተገኙ ሲሆን የደ/ብርሃን ዩኒቨርስቲ የማህበረሰብ ህብረት አመራር
የሆኑት ዶክተር እስጢፋኖስ ለማ በስልጠናው መዝጊያ ንግግራቸው ይህ ሰልጣኝ ወደየወረዳው ከተመለሰ በኋላ በሰለጠነበት አግባብ ሳይሰለች ተግባራዊ ልምምድ በማድረግ የራሱን ክህሎት በማዳበር ለወረዳውም ሆነ ለዞኑ አቅም መሆን ይኖርበታል ካሉ በኋላ ለቀጣይም የደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ ከሰ/ሸዋ ዞን መሬት መምሪያ ጋር በመተባበር ተመሳሳይ ስልጠና ለመስጠት ዝግጁ እንደሆኑ ገልጸዋል። በመጨረሻም የመምሪያው የማኔጅመንት
አባላት ከሰልጣኞች ጋር በቀጣይ ወራት ስለሚፈጸሙ የመሬት አጠቃቀም እቅዶች ዙሪያና ስለሚገጥሙ ችግሮች በመወያየት እና አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ የ GIS ስልጠናው በተሳካ ሁኔታ ተቋጭቷል።

25/01/2026
25/01/2026

በአማራ ክልል የተሻሻለው የመሬት አዋጅ የትኞቹን መብቶች ያጎናጽፋል?
++++++++++++++++++++++++

12/01/2026
11/01/2026

፲፰. በገጠር መሬት ይዞታ ላይ የተፈራን ግንባታ በሽያጭ ስለማስተላለፍ

በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፯ ስር የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ፡-
፩/ በከተማ ወሰን ተጠቃለው ርክክብ ባልተደረገባቸው ይዞታዎች እና በከተማ ክልል በተጠቃለሉ የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ የሚገኙ ባለይዞታዎች እስከ 500 ካሬ ሜትር ባለ መሬት ላይ ከማሳቸው ላይ ያፈሯቸውን የተለያዩ ቤትና ተያያዥ ግንባታዎች መሸጥ ይችላሉ፡፡ ይሁን እንጂ የተሸጠው ንብረት አርፎበት ከነበረው መሬት ውጭ ከ500 ካሬ ሜትር በላይ ቀሪ መሬት ያለው ባለይዞታ መሬቱን ለሌሎች የግብርና ተግባራት ከማዋል በስተቀር ከፋፍሎም ይሁን ሳይከፍል ቤት ገንብቶ መሸጥ የተከለከለ ነው፤

፪/ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ (፩) የተደነገገው ቢኖርም የቀሪው የማሳ ስፋት ከ200 ካሬ ሜትር በታች ከሆነ የመኖሪያ ቤቱ አካል እንደሆነ ተቆጥሮ አብሮ ይተላለፋል። ይሁን እንጂ ይህ አዋጅ ከመውጣቱ በፊት በዚህ ህግ ከተደነገገው አነስተኛ የማሳ መጠን በታች በሆነ ህጋዊ እውቅና አግኝቶ በተመዘገበ ማሳ ላይ የተገነባን ቤት ከመሸጥ አይከለክልም፤
፫/ ከከተማ ክልል ውጭ ባሉ የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ የሚገኙ ባለይዞታዎች እስከ 1000 ካሬ ሜትር ባለ መሬት ላይ ያፈሯቸውን ቤትና ተያያዥ ግንባታዎች መሸጥ ይችላሉ፡፡ ይሁን እንጂ የተሸጠው ንብረት አርፎበት ከነበረው መሬት ውጭ ከ1000 ካሬ ሜትር በላይ ቀሪ መሬት ያለው ባለይዞታ መሬቱን ለሌሎች የግብርና ተግባራት ከማዋል በስተቀር ከፋፍሎም ይሁን ሳይከፍል ቤት ገንብቶ መሸጥ የተከለከለ ነው፤

፬/ በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ (፫) የተደነገገው ቢኖርም የቀሪው ማሳ ስፋት ከ 200 ካሬ ሜትር በታች ከሆነ የመኖሪያ ቤቱ አካል እንደሆነ ተቆጥሮ አብሮ ይተላለፋል። ይሁን እንጂ ይህ አዋጅ ከመውጣቱ በፊት በዚህ ህግ ከተደነገገው አነስተኛ የማሳ መጠን በታች በሆነ ህጋዊ እውቅና አግኝቶ በተመዘገበ ማሳ ላይ የተገነባን ቤት ከመሸጥ አይከለክልም፡፡

በአዲሱ አዋጅ የተከተቱ ቁልፍ መረጃዎች በቀላሉ ለመከታተል ከዚህ በታች የተመላከቱትን ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
የሚፈልጉትን መረጃም በፈለጉት ጊዜ እንዲያገኙ ተግተን እንሰራለን።

1️⃣ 👉 ፌስቡክ ገፃችን:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100064799525991

2️⃣ 👉ዩቲዩብ ቻናል:_ https://youtube.com/?si=ULUpWE7z4t_zNcpt

3️⃣👉 ዋትሳፕ :-
https://chat.whatsapp.com/ESNMdUA0MiOCSKYmULRsJb
ወይም
https://chat.whatsapp.com/D68iL7eeh6IDLE4C4tNUXL?mode=wwt

4️⃣👉ቴሌግራም:- https://t.me/+_mcZddtJ3JpjYTFk

11/01/2026

፲፯. በገጠር መሬት ይዞታ ላይ የተፈራን ንብረት በሽያጭ ስለማስተላለፍ

፩/ ባለይዞታዎች በመሬት ይዞታቸው ላይ በጉልበታቸው፣ በእውቀታቸው ወይም በመፍጠር ችሎታቸው ያፈሯቸውን የማይንቀሳቀሱ ቋሚ ንብረቶች ባሉበት ሁኔታ የመሸጥ፣ የመለወጥ ወይም በሌላ በማንኛውም ህጋዊ መንገድ የማስተላለፍ መብት አላቸው፤
፪/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተደነገጉት የማይንቀሳቀሱ ቋሚ ንብረቶች ግንባታዎችን ወይም በመሬት ላይ ሙሉ በሙሉ የለሙ ቋሚ ተክሎችን የሚያጠቃልል ነው፤
፫/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተደነገገው መብት ተፈጻሚ ሲሆን አብሮ የሚተላለፈው መሬት ባለይዞታውን ከይዞታው በማያፈናቅል መልኩ በመሬቱ ላይ የተፈራውን ንብረት ለመጠቀም የሚያገለግል የመሬት ስፋት ብቻ መሆን አለበት፤

፬/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተደነገገው መብት ተፈጻሚ የሚሆነው የመሬት አጠቃቀም ዕቅድን መሰረት በማድረግ ብቻ ይሆናል፡፡ ሆኖም ግን የመሬት አጠቃቀም እቅድ ባልተዘጋጀበት አካባቢ ከአሁን በፊት በህግ መሰረት በይዞታ ማረጋገጫ ደብተሩ ላይ ባስመዘገበው ይዞታ ውስጥ የተገነባ መኖሪያ ቤትን ከመሸጥ፣ ከመለወጥ ወይም በሌላ በማንኛውም ህጋዊ መንገድ ከማስተላለፍ አይከለክልም፤

፭/ አካለ መጠን ያላደረሰ ልጅ ሞግዚት ፍርድ ቤት ካልፈቀደ በስተቀር አካለ መጠን ያላደረሰውን ልጅ በገጠር መሬት ይዞታ የተፈሩ የማይንቀሳቀሱ ቋሚ ንብረቶችን ባሉበት ሁኔታ መሸጥ፣ መለወጥ ወይም በሌላ በማንኛውም መንገድ ማስተላለፍ አይችልም፤
፮/ በፍርድ የተከለከለ ሰው ሞግዚት በፍርድ በተከለከለው ሰው የገጠር መሬት ይዞታ ላይ የተፈሩ የማይንቀሳቀሱ ቋሚ ንብረቶችን ባሉበት ሁኔታ መሸጥ፣ መለወጥ ወይም በሌላ በማንኛውም መንገድ ማስተላለፍ አይችልም፡፡ ሆኖም ግን ፍርድ ቤቱ የመከልከል ውሳኔ በሚሰጥበት ወቅት ወይም ከሰጠ በኃላ በፍርድ የተከለከለው ሰው ራሱ ወይም ከሞግዚቱ ጋር በመሆን የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ሽያጭ ውልን እንዲዋዋል የፈቀደለት ከሆነ በይዞታው ላይ የተፈሩ የማይንቀሳቀሱ ቋሚ ንብረቶችን ባሉበት ሁኔታ መሸጥ፣ መለወጥ ወይም በሌላ በማንኛውም ህጋዊ መንገድ ማስተላለፍ ይችላል፤

፯/ በገጠር መሬት የተፈራን የማይንቀሳቀስ ቋሚ ንብረት የመሸጥ፣ የመለወጥ ወይም በሌላ በማንኛውም ህጋዊ መንገድ የማስተላለፍ ውል በፁህፍ ሆኖ በወረዳ ወይም በከተማ ፍትህ ጽህፈት ቤት ቀርቦ መረጋገጥ እና መመዝገብ አለበት፡፡ የተረገጋጠው እና የተመዘገበው ሰነድ ቅጅ ለስም ንብረት ዝውውር ለሚመለከተው ወረዳ ገጠር መሬት ጽህፈት ቤት፣ ከተማ መሬት ጽህፈት ቤት ወይም ከተማ መሬት መምሪያ መላክ አለበት፡፡ በጽሁፍ ያልተደረገ፣ ያልተረጋገጠ እና ያልተመዘገበ ውል እንዳልተደረገ ይቆጠራል፤

፰/ በገጠር መሬት ላይ የተፈራ ቋሚ ንብረት በሽያጭ ወይም በሌላ በማንኛውም ህጋዊ መንገድ ከማስተላለፍ ጋር ተያይዞ ሊኖር የሚችል ክፍያ በደንብ ይወሰናል፡፡
በአዲሱ አዋጅ የተከተቱ ቁልፍ መረጃዎች በቀላሉ ለመከታተል ከዚህ በታች የተመላከቱትን ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
የሚፈልጉትን መረጃም በፈለጉት ጊዜ እንዲያገኙ ተግተን እንሰራለን።

1️⃣ 👉 ፌስቡክ ገፃችን:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100064799525991

2️⃣ 👉ዩቲዩብ ቻናል:_ https://youtube.com/?si=ULUpWE7z4t_zNcpt

3️⃣👉 ዋትሳፕ :-
https://chat.whatsapp.com/ESNMdUA0MiOCSKYmULRsJb
ወይም
https://chat.whatsapp.com/D68iL7eeh6IDLE4C4tNUXL?mode=wwt

4️⃣👉ቴሌግራም:- https://t.me/+_mcZddtJ3JpjYTFk

09/01/2026

አንቀጽ ፲፩. ስጦታ
(ከአዋጁ በቀጥታ የተወሰደ)
*****************
፩/ የገጠር መሬት ባለይዞታ ይዞታውን በቤተሰብ ሕጉ የስጋ ዘመዳሞች መካከል በስጦታ ወይም በውል በተደገፈ በይጦረኛል ስምምነት ሊያስተላልፍ ይችላል፤
፪/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ባለይዞታው በውል በተደገፈ የይጦረኛል ስምምነት ውል ለገባለት ለማንኛውም ሰው በስጦታ ማስተላለፍ ይችላል፤
፫/ በሞግዚት ጥበቃ ስር የሚተዳደሩ በፍርድ የተከለከሉ ሰዎችን በመወከል ሞግዚቱ ወደታች ለሚቆጠሩ የባለይዞታው ተዎላጆች በቤተዘመድ ምክር ጉባኤ ፈቃድ በስጦታ ማስተላለፍ ይችላሉ፤
፬/ በዚህ አንቀፅ ንኡስ አንቀፅ (፩)፣ (፪)፣ እና (፫) በተደነገገው መሰረት ስጦታ ሲደረግ አካል ጉዳተኞችን እና እድሜያቸው ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆችን የሚጎዳ ከሆነ በህግ ፊት ተፈፃሚነት አይኖረውም፤
፭/ አካለ መጠን ያላደረሰ ልጅ ሞግዚት አካላ መጠን ያልደረሰውን ልጅ የገጠር መሬት ይዞታ በልጁ ስም በስጦታ ማስተላለፍ አይችልም፤
፮/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) የተደነገገው በሁኔታዎች ላይ የተመሰረተ የስጦታ ውል የይፍረስልኝ ክስ በውሉ ላይ የተቀመጠው ቅድመ ሁኔታ ከተጣሰበት ወይም መጣሱን ስጦታ ሰጪው ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ በ2 ዓመት ጊዜ ውስጥ መቅረብ አለበት፤
፯/ ማንኛውም የገጠር መሬት ስጦታ ውል በጽሁፍ ሆኖ መሬቱ ለሚገኝበት ወረዳ መሬት ጽህፈት ቤት፣ ከተማ መሬት ጽህፈት ቤት ወይም ከተማ መሬት መምሪያ ፊት ቀርቦ መረጋገጥ እና መመዝገብ አለበት፡፡ በጽሁፍ ያልተደረገ፣ ያልተረጋገጠ እና ያልተመዘገበ ውል እንዳልተደረገ ይቆጠራል፤
፰/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ፯ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ የስጦታ ውል ማረጋገጥ እና ምዝገባ ስርዓት ዝርዝር በደንብ ይወሰናል፡፡
በአዲሱ አዋጅ የተከተቱ ቁልፍ መረጃዎች በቀላሉ ለመከታተል ከዚህ በታች የተመላከቱትን ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
የሚፈልጉትን መረጃም በፈለጉት ጊዜ እንዲያገኙ ተግተን እንሰራለን።

1️⃣ 👉 ፌስቡክ ገፃችን:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100064799525991

2️⃣ 👉ዩቲዩብ ቻናል:_ https://youtube.com/?si=ULUpWE7z4t_zNcpt

3️⃣👉 ዋትሳፕ :-
https://chat.whatsapp.com/ESNMdUA0MiOCSKYmULRsJb
ወይም
https://chat.whatsapp.com/D68iL7eeh6IDLE4C4tNUXL?mode=wwt

4️⃣👉ቴሌግራም:- https://t.me/+_mcZddtJ3JpjYTFk

05/01/2026
05/01/2026

ዝቅተኛው የአንድ አርሶ አደር የይዞታ ማሳ ስፋት 0.25 ሄክታር ስለመሆኑ የፌደራሉም ሆነ የአማራ ክልል ገጠር መሬት አስ/አጠ/አዋጅ ደንግጓል።
0.25 ሄክታር ማለት፣ በሳይንሳዊ የቅየሳ ልኬታ 2500 ካሬ ሜትር ነው።
ስጦታ ተቀባዩ ከስጦታ ሰጩ ሊቀበልና የይዞታ መብት ሊተላለፍለት የሚገባ የይዞታ መጠን ዝቅተኛውን የማሳ መጠን 0.25 ሄክታር ወይም 2500 ካሬ ሜትር ማሚላት ግዴታ ነው ::
በመሆኑም የሁለተኛ ደረጃ የይዞታ ማረጋገጫ አረንጓዴ ደብተር ወይም በካዳስተር ልኬታ በካርታ የተደገፈ ካርታ ሊሰጠው የሚገባም ይህንን የይዞታ ጣራያ ሊያሟላም የሚገባው ስለመሆኑ ስንቶቻችን ግንዛቤው አለን?
በልዩ ምክንያት አሳማኝ ተብለው በዝርዝር ከተቀመጡት ልዩ ምክንያቶች በስተቀር 0.25 ሄ/ር ያልሞላ የማሳ መጠን ለሚሰጥ የሁለተኛ ደረጃ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ወይም ካርታ የተሳሳተ ማስረጃም ተደርጎ ይወሰዳል።
የተሳሳተ ማስረጃ መስጠት ደግሞ ከበድ ያለ የወንጀልና የፍትሐብሄር ተጠያቂነት ያለው መሆኑን በአዲሱ የገጠ/መ/አስ/አጠ/ አዋጅ በዝርዝር መቀጮ ተደንግጓል!!
በመሆኑም በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያ የሚለቀቁ ምንጭ የሌላቸው አሉባልታዎችን በጥንቃቄ መመርመር የሚገባ መሆኑን የአበክመ መሬት ቢሮ ያሳስባል።
በቀጣይም ዝክረ ህጉ ታትሞ ለሰፊው ህዝብ እስኪደርስ፣ ደንብና መመሪያዎች እስኪደርሱ፣ በየ ደረጃው ላለው የመሬት ተቋምና ለአጋር ባለ ድርሻ አካላት ስልጠናና የግንዛቤ ፈጠራ እስከሚሰራ
የሚፈልጉትን መረጃም በፈለጉት ጊዜ እንዲያገኙ ተግተን አጫጭር መረጃዎችን በማጋራት በትጋት የመረጃ ምንጭ ሆነን የምናገለግላችሁ ይሆናል።

የቢሮው ህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት!
ታህሳስ26/2018
ባ/ዳር

1️⃣ 👉 ፌስቡክ ገፃችን:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100064799525991

2️⃣ 👉ዩቲዩብ ቻናል:_ https://youtube.com/?si=ULUpWE7z4t_zNcpt

3️⃣👉 ዋትሳፕ :-
https://chat.whatsapp.com/ESNMdUA0MiOCSKYmULRsJb
ወይም
https://chat.whatsapp.com/D68iL7eeh6IDLE4C4tNUXL?mode=wwt

4️⃣👉ቴሌግራም:- https://t.me/+_mcZddtJ3JpjYTFk

Address

Debre Birehan
Debre Birhan

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when North Shoa Zone Land Department posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share