ደብረብርሃን ከተማ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Debre Birhan
  • ደብረብርሃን ከተማ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት

ደብረብርሃን ከተማ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን  ጽ/ቤት የደ/ብርሃን ከተማ በአፄ ዘርያእቆብ ዘመነ መንግስት በ1446 ዓ.ም የተቆረቆረች ጥንታዊ ከተማ ነች፡፡

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ የወጣቶች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ስራ አስፈፃሚ አቶ ድርሻዬ ደበበ ተገኝ...
12/07/2023

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ"

በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ የወጣቶች የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ስራ አስፈፃሚ አቶ ድርሻዬ ደበበ ተገኝተው የደም ልገሳ ፕሮግራም አስጀምረዋል ።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ድርሻዬ በፕሮግራሙ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በበጎ ፍቃድ አገልግሎት አንዱ የሆነው የደም ልገሳ ተግባር ቀደም ብሎ በክፍለ ከተማችን ቀበሌዎች የተጀመረ ሲሆን በዛሬው እለትም በክፍለ ከተማ ደረጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልፀዋል።

ደም እጦት ምክንያት ህይወታቸውን የሚያጡ ዜጎች እንደሚገኙ ገልፀው ነገር ግን የብዙዎችን ህይወት መታደግ ምንችለው ደግሞ ደም በመለገስ ነው ሲሉ ዋና ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል።

ደም መለገስ በገንዘብ የማይተመን የሰውን ልጅ ህይወት የማትረፍ ትልቅ ስራ ነው ብለዋል።

በዛሬው እለትም ደም ለመለገስ የተሰባሰቡትን ደም ለጋሾች በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ስም አመስግነዋል፡፡

አያይዘው በዛሬው እለት ከስጦታዎች ሁሉ የላቀ ስጦታ ደም በመሆኑና በዚህም ተገኝቼ ደም መለገስ በመቻሌ ደስተኛ ነኝ ሲሉ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ድርሻዬ ገልፀዋል ።

አስተያየታቸውን የሰጡ ደም ለጋሾች በገንዘብ የማይተመነውን የሰውን ልጅ ህይወት ለማትረፍ የሚያስችለውን ደም በተደጋጋሚ እየሰጡ እንደሆነና የደስታ ስሜት ከመፍጠር ውጪ የሚፈጥርባቸው የጤና ችግር እንደሌለና ሁሉም ደም መስጠት የሚችል ደም በመስጠት በደም እጦት ምክንያት የሚሰቃዩና ህይወታቸው አደጋ ላይ የወደቀ ወገኖችን ህይወት በመታደግ ረገድ ተሳትፎ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት - ደብረ ብርሃን

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ 2"! በደብረ ብርሃን ከተማ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ የ2015 በጀት ዓመት የበጋ በጎ ፍቃድ አገልግሎት መዝጊያና የ2015/16 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ  አገል...
12/07/2023

"በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ 2"!

በደብረ ብርሃን ከተማ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ የ2015 በጀት ዓመት የበጋ በጎ ፍቃድ አገልግሎት መዝጊያና የ2015/16 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ማካሄድ ጀመረ።

ሐምሌ 5/2015 ዓ.ም [ደብረ ብርሃን ] በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር " በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ"!በሚል መሪ ቃል የ2015/16 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መድረክ መካሄድ ጀመረ ።

በመድረኩ ላይ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ድርሻዬ ደበበ ፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ በለጡ ደገፉ ፣ የክ/ከተማና የቀበሌ አመራሮች ፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ሴቶች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

መድረኩን በመክፈቻ ንግግር ያስጀመሩት የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ድርሻዬ ደበበ በባለፈው 2015 በጀት ዓመት በበጋ መርሀ ግብር በርካታ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተግባራት ማከናወን እንደተቻለ ተናግረው የነበሩ በጎ ፍቃድ ተግባራት የበለጠ በማጠናከር በክረምት መርሀ ግብር ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በ2015/16 የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይም ወጣቱ በአቅመ ደካሞች በቤት እድሳት ፤ በአረንጓዴ አሻራ፤ በደም ልገሳ፤ በክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ፣ ለወላጅ አልባ ተማሪዎች የት/ት ቁሳቁስና አልባሳት የማሰባሰብ ስራና በሌሎች ተግባራት እንዲሳተፍ እና የማህበረሰባችን የኢኮኖሚና የልማት ክፍተቶችን በመሙላት የመልካምና በጎ ተግባራት ተካፋይ ትሆናላችሁ ብለዋል።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ም/አማካሪ ወ/ሮ አገረድ ወንዳፈረው እንደተናገሩት የክረምት በጎ ፍቃድ ወጣቶች ማህበረሰቡን የማገልገል ባህልና እሴቶችን የእርስ በእርስ ግንኙነትን የሚያጠናክር መሆኑን ገልፀው ተግባሩም ቀደም በሎ በክ/ፍለከተማው የተጀመረ ሲሆን የአቅመ ደካሞችን ቤት በመጠገን በደም ልገሳ በማጠናከሪያ ትምህርት የክረምት በጎ ፍቃድ የተለመደና ሁሉም መልካም ተግባራትን በመፈፀም ማህበረሰቡን ማገልገል እንደሚገባ በመልክታቸው ገልፀዋል ።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት - ደብረ ብርሃን

በሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በይፋ ተጀመረ ! በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ በሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ  የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በዛሬው እለት ለአቅመ ደካሞች የ...
01/07/2023

በሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በይፋ ተጀመረ !

በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ በሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በዛሬው እለት ለአቅመ ደካሞች የሚውል ቤት ግንባታ ስራ በመስራት በይፋ ተጀመረ ።

የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ያስጀመሩት የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ በለጡ ደገፉ ሲሆኑ ኃላፊዋ እንደተናገሩት በክረምት ወራት የአቅመ ደካሞች ቤት ማደስ ፣ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ፣ የደም ልገሳ፣ የከተማ ጽዳት፣ የጤና ሥራዎች እና ሌሎችም ተግባራት በሁሉም ቀበሌዎች ተጠናክሮ እንደሚሰራ ገልፀዋል ፡፡

በዛሬው እለትም የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራ በሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ መጀመሩን ገልፀዋል ። በተለይም በዘንድሮው የክረምት ወራት በርካታ ተግባራትን ለማከናወን መታቀዱን ገልፀው ለእቅዳችን መሳካት የሁሉንም አካል ድጋፍና እርብርብ የሚጠይቅ መሆኑ ኃላፊዋ ተናግረዋል።

ተግባሩ ህብረተሰቡንና ወጣቶችን በማነሳሳት የተሻለ ዉጤት ለማምጣትና ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን በክፍለ ከተማ ደረጃ በሰፊዉ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

የሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ እና አቶ ቢኒያም በላይ በበኩላቸው የ2015/16 በጀት አመት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በቀበሌው በይፋ መጀመሩን ገልፀው በዛሬው እለትም ቀበሌ አስተዳደሩ ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመሆን የጀመረውን የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ ስራን በፍጥነት አጠናቆ ለአቅመ ደካሞችን ቤቱን ለማስተላለፍ የመጀመሪያ የትኩረት ስራ በማድረግ ወጣቶቹንና ሴቶችን በማሳተፍ የበጎ ፍቃድ ስራውን ማስጀመራቸውን ተናግረዋል።

የመኖሪያ ቤቱ ግንባታም በአጭር ጊዜ ተጠናቆቆ ለሚመለከታቸው አካላትም እንደሚተላለፍ ተናግረዋል።

በተጨማሪም በቀበሌው በክረምት ወራት በርካታ ስራዎችን ለማከናወን በእቅድ መያዛቸውንና ለዚህም በርካታ ወጣቶችና ሴቶች በበጎ ፍቃድ የሚሳተፉ መሆናቸው የቀበሌው አስተዳዳሪ አቶ ቢኒያም ተናግረዋል።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ነው ።

አመራሩ  ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መፍታት ቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ ።ደብረ ብረሀን :-ሰኔ 19/2015ዓ.ም (ደብኮ)አመ...
26/06/2023

አመራሩ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መፍታት ቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን እንደሚገባ ተገለጸ ።
ደብረ ብረሀን :-ሰኔ 19/2015ዓ.ም (ደብኮ)አመራሩ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መፍታት ተቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን እንደሚገባ ተገለፀ ።

በደብረብርሃን ከተማ መፍጠንና መፍጠር የወል እውነቶችን የማፅናት ቀጣይ የትግል ምዕራፍ በሚል መሪ ሃሳብ ከከተማ እስከ ቀበሌ ላሉ የፓርቲ አመራሮች ሲሰጥ የሰነበተው ስልጠና ተጠናቀቀ።

የደብረብርሃን ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ጌታቸው እንደገለጹት አመራሩ በመልካም ስነምግባር ህብረተሰቡን በቅንነት ማገልገል እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።

የከተማው ሠላም በዘላቂነት ተጠብቆ እንዲዘልቅ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን ሆኖ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

የማዳበሪያ አቅርቦት፣የኑሮ ውድነት፣የሥራ አጥነት ችግር እንዲፈታ በየደረጃው እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል።

የደብረብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ካሳሁን እምቢአለ መድረኩን ሲያጠቃልሉ እንደተናገሩት ስርቆትን በጽናት ታግሎ በማስተካከል እና የአመራር አንድነት በማጠናከር ለህዝብና ለመንግስት የሚጠቅም ተጨባጭ ስራ መፈጸም እንደሚጠበቅ አሳውቀዋል፡፡
በተለይም አመራሩ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መፍታት ቀዳሚ ተግባሩ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡አመራር በተግባር ሰርቶ ውጤት ማምጣት እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
አሁን እንደ ሀገር ያለውን ዘርፈ ብዙ ችግሮች በመፍታት ለሀገረ መንግስት ግንባታ የምክክር ኮሚሽኑ ስራ ፋይዳው የጎላ መሆኑን አንስተው ለተግባራዊነቱ ሁሉም ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት አመልክተዋል፡፡

በደብረ ብርሃን ከተማ ከ57 ሺህ በላይ ወጣቶችን በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማሳተፍ መታቀዱ ተገለጸበጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ -2 በሚል መሪ መልዕክት የደብረ ብርሃን ከተማ ወጣትና ስፖር...
23/06/2023

በደብረ ብርሃን ከተማ ከ57 ሺህ በላይ ወጣቶችን በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማሳተፍ መታቀዱ ተገለጸ

በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ -2 በሚል መሪ መልዕክት የደብረ ብርሃን ከተማ ወጣትና ስፖርት መምሪያ የ2015ዓ.ም የክረምት በጎፈቃድ አገልግሎት የንቅናቄ መድረክ ከባለድርሻ አካላት ጋር እያካሄደ ይገኛል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ወጣትና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ኢንጂነር ቶማስ መኮንን የእንኳን ደህና መጣችሁ የመከፈቻ ንግግር አድርገዋል።

በ2014ዓ.ም በክረምት በጎፈቃድ አገልግሎት በክልሉ ከሚገኙ ከተሞች 1ኛ መውጣቱን አንስተዋል።በዚህ ዓመትም በተመሳሳይ የላቀ አፈፃጸም ለማስመዝገብ ተቀናጅቶ መስራት እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
በመጪው ክረምት በደብረብርሃን ከተማ 57 ሺህ 540 ወጣቶችን በማሳተፍ 57 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ግምት ያለው ሃብት ከወጪ ማዳን እንደሚቻል ተገልጿል።

በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳዳር ትጥቅ ይዘው ህውከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ የተደረሰባቸው ግለሰቦች በተኩስ ልውውጥ ከነ ጦርመሳሪያቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ። በከተማ አስተዳደሩ በእቴጌ ...
23/06/2023

በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳዳር ትጥቅ ይዘው ህውከትና ብጥብጥ ለመፍጠር ሲንቀሳቀሱ የተደረሰባቸው ግለሰቦች በተኩስ ልውውጥ ከነ ጦርመሳሪያቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ።

በከተማ አስተዳደሩ በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ሳሪያ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቦሰና ምንጭ በሚባል አካባቢ ቁጥራቸዉ በርከት ያሉ ሰዎች በጦር መሳሪያ የተደገፈ ህውከትና ብጥብጥ ለመፍጠር እየተዘጋጁ መሆኑ መረጃው ለጸጥታ ሀይሉ ይደርሳል።
ጉዳዩን በመረጃ ያጠናከረው የጸጥታ ሀይሉ ሰኔ 14 ለ15/2015 ዓ/ም ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት ድንገተኛ የተቀናጀ ስምሪት ተደርጎ ከሰዓታት ከባድ የተኩስ ምልልስ በኋላ የጥፋት ግለሰቦች ከነ መሳሪያቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በአካባቢው የከፋ ጉዳት እንዳይፈጠር የፀጥታ ሀይሉ እጅግ በከፍተኛ ጥንቃቄ በወታደራዊ ጥበብ ያለምንም ኪሳራ ያለ መስዕዋትነት ድል ማድረግ ችሏል።

በኦፕሬሽኑ 26 ግለሰቦች ከነ ትጥቃቸው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን አራት እስናይፐር ከ1261 ጥይት ጋር፣አንድ ድሽቃ ከ490 ጥይት ጋር፣5 ክላሽ ከሰባት ካርታና 530 ጥይት ጋር፣ 2 ብሬን፣ 3 የእጅ ቦንብ፣ ሁለት የቱርክ ሽጉጥ ከመሰል ስምንት ጥይት ጋር በቁጥጥር ስር ውሏል።

መረጃው የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ነዉ

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ጣይቱ ክፍለከተማ በሴፍትኔት ፕሮግራም የታቀፉ የማህበረሰብ ክፍሎች ለአረንጓዴ ልማት ከ1 ሺህ ካሬ ባለይ ቦታ ማዘጋጀታቸው ተገለፀ፡፡የደብረ ብርሃን ከተማ አስ...
22/06/2023

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ጣይቱ ክፍለከተማ በሴፍትኔት ፕሮግራም የታቀፉ የማህበረሰብ ክፍሎች ለአረንጓዴ ልማት ከ1 ሺህ ካሬ ባለይ ቦታ ማዘጋጀታቸው ተገለፀ፡፡

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ጣይቱ ክፍለከተማ አየር ጤና ቀበሌን አርንጓዴ ለማድረግ የሴፍትኔት ፕሮግራም ተጠቃሚዎች 1 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታን ለማልማት ዝግጅት ማጠናቀቃቸውም ተገልጿል፡፡

በጣይቱ ክፍለከተማ የአየር ጤና ቀበሌ አስታዳሪ አቶ ሱራፌል አስፋው እንደገለፁት በቀበሌው ለአርንጓዴ ልማት የተዘጋጀው ቦታ ስርቶ ማሳያ እንዲሆን ሲሆን በቦታውም የውባት ዛፎችን ከመትክል ጀምሮ በሴፍትኔት ፕሮግራም የታቀፉ የማህበረሰብ ክፍሎች የጓሮ አትክልቶችን በመትከል ተጠቃሚ የሚሆኑበት ነውም ብለዋል፡፡

በተጓዳኝም የአካባባው ማህበረሰብ ከዚህ ሰርቶ ማሳያ ልምድ በመውሰድ አካባቢያቸውን እና ግቢቸውን በውበት ዛፎችና በጓሮ አትክልቶች በማልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻልን ታሳቢ ያደርገ ስራ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚዛናዊና ፈጣን  መረጃ ለህብረተሰቡ በማድረስ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ ።ደብረ ብረሀን :- ሰኔ 13/2015ዓ.ም (ደብኮ)የኮሙንኬሽን ባለሙያዎች ሚዛናዊ...
20/06/2023

የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ሚዛናዊና ፈጣን መረጃ ለህብረተሰቡ በማድረስ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ ።
ደብረ ብረሀን :- ሰኔ 13/2015ዓ.ም (ደብኮ)የኮሙንኬሽን ባለሙያዎች ሚዛናዊና ፈጣን መረጃ ለህብረተሰቡ በማድረስ ሀላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተገለፀ ።
የደብረ ብርሃን ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ለኮሙኒኬሽን እና የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች በዜና አዘገጃጀት እና አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ሰጠ ።
ስልጠናው የዜና ዕቅድ፣ይዘት አመራረጥ፣አጭር ዜና አዘገጃጀት እና አጠቃቀም ዙሪያ ትኩረት ያደረገ ሲሆን በንድፈ ሀሳብ ተተንትኖ፤ በተግባር ልምምድ ተደግፎ ተሰጥቷል፡፡
ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ከስልጠናው መጠቀማቸውንና ደስተኛ መሆናቸውን ጠቅሰው ክፍተታቸውን የሞላ፣ለቀጣይ ስራ አቅም የሚገነባ መሆኑን አንስተዋል፡፡ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት አስቦ ስላዘጋጀው አመስግነው ቀጣይነት እንዲኖረውም ጠይቀዋል፡፡
የደብረብርሃን ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ መቅደስ ብዙነህ ስልጠናውን ሲያጠቃልሉ እንደተናገሩት እስካሁን የነበሩ ክፍተቶችን አርሞ ጥንካሬዎችን አጎልብቶ ተቀናጅቶ መስራት ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
በቀጣይ የኮሙኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ትክክለኛ፣ሚዛናዊና ፈጣን መረጃ ለህብረተሰቡ በማድረስ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ በሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ በ 2016 ዓ.ም በሚሰሩ የመሠረተ ልማት ስራዎች  ላይ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ውይይትና ፕሮጀክት መረጣ ተደረገ።          በእቴጌ ጣይቱ ...
04/06/2023

በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ በሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ በ 2016 ዓ.ም በሚሰሩ የመሠረተ ልማት ስራዎች ላይ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ውይይትና ፕሮጀክት መረጣ ተደረገ።

በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በቀጣይ 2016 በጀት ዓመት ለሚሰሩ የመሠረተ ልማት ስራዎች በሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ የሚሰሩ ፕሮክቶች በቀበሌው ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት ተካሂዷል።

በውይይቱ ላይ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ድርሻዬ ደበበ ፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ከተማና መሰረተ ልማት ሥራ አሥኪያጂ አቶ ዳግም እሸቴ ፣ የሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቢኒያም በላይ እንዲሁም የቀበሌው አመራሮችን የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

የሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ እንደገለፁት በቀበሌያችን በ2015 ዓ.ም 6 ፕሮጀክቶች ለመስራት ታቅዶ ሁሉም ፕሮጀክቶች በጥራትና በፍጥነት በተቀመጠላቸው ጊዜ ሰሌዳ ማጠናቀቅ ችለናል ብለዋል።

በተለይም ለዚህ ተግባር መሳካት የተለያዩ አጋር አካላት በቅንጅት መስራት መቻላቸው መሆኑን ጠቁመዋል።

በቀጣይ አመትም የቀበሌያችን ህዝብ የመሰረተ ልማት ፍላጎት ለመመለስ የፕሮጀክት መረጣ አድርገን ወደስራ እንገባለን ብለዋል።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የከተማና መሰረተ ልማት ፅ/ቤት ሥራ አሥኪያጅ አቶ ዳግም እሸቴ እንደገለፁት የክፍለ ከተማችን የ2015 ዓ.ም የመሰረተ ልማት ስራዎች ጥሩ በሚባል ደረጃ መሰራታቸውን ጠቅሰው ለዚህም ህብረተሰቡ ላደረገው አስተዋጽኦ አመስግነዋል።

በቀጣይ አመት ለሚሰሩ ፕሮጀክቶች በየደረጃው ህዝብን የማወያየት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው በዛሬው እለት በሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ ጀምረናል ብለዋል።

በዚህም ቀበሌዎች የሚሰሩ የመሠረተ ልማት ስራዎች ላይ የፕሮጀክት መረጣ ለማድረግና የሚሠሩ የልማት ስራዎችን ለህብረተሰቡ ከሚያመጡት የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት አንፃር ታይቶ መረጣ መደረግ እንዳለበት ገልፀዋል።

በቀጣይ ለሚጀመሩ ስራዎች ማህበረሰቡን ያሳተፈና ያመኑበትን ለመስራት ያለመ ለማድረግ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑን ተናግረዋል ።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ድርሻዬ ደበበ በበኩላቸው በ2015 ዓ.ም በክፍለ ከተማ አስተዳደሩ በርካታ ፕሮጀክቶችን ስለማከናወናቸው በመጠቆም በቀጣይ አመት በርካታ የመሠረተ ልማት ስራዎች እንደሚሰሩና አሁን ላይ የአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሰራለት የመረጣቸው ፕሮጀክቶችን መሠረት በማድረግ የፕሮጀክት መረጣ እየተካሄደ ስለመሆኑ ተናግረዋል።

በዚህም መሰረት በሸዋረገድ ገድሌ ቀበሌ በ2016 በጀት አመት በአለም ባንክ እንዲሰሩ በቀበሌው ነዋሪዎች የተመረጡ ፕሮጀክቶች :-
1ኛ. ከሳህሌ እሸቴ እስከ ዋና ገበያው ጌሾ ተራ ድረስ የሚደርስ 320 ሜ ጠጠር መንገድና ተፋሰስ ግንባታ
2ኛ. ከቂርቆስ ቤ/ክ እስከ ስንታየሁ ቤት/አዲሱ ኮብል 390ሜ የጠጠር መንገድና ተፋሰስ ግንባታ
3ኛ. እታፈራሁ መኮንን እስከ አባተ ተፈራ 370 ሜ የጠጠርና ተፋሰስ ግንባታ
4ኛ. ከአዋሽ ባንክ እስከ ከሮያል የገበያ አዳራሽ እስከ በግ ተራው የመንገድ መብራት ዝርጋታ
5ኛ. ከቤዛ ፎቅ እስከ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን እስከ ጥሩነሽ ወፍጮ ቤት ድረስ 410ሜ የጠጠር መንገድና ተፋሰስ ግንባታ
► በተጨማሪም በ2015 በጀት አመት በቀበሌው የተሰሩ ሁለት የጠጠር መንገድና ተፋሰስ ግንባታ ስራ በ2016 በጀት አመት የኮብልስቶን ንጣፍ ስራ የሚሰራ ይሆናል።
በአጠቃላይ በመድረኩ በ2016 በጀት አመት በአለም ባንክ በጀት የሚሰሩ ፕሮጀክቶች መረጣ ተደርጎ መድረኩ ተጠናቋል።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ

በተለምዶ 633ቱ የቤት ማህበር በመባል የሚታወቁትና እጣ ወጥቶላቸው ቦታ ለተረከቡ የቤት ማህበራት የግንባታ ፍቃድ መሰጠት ተጀመረ።የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ህንፃ ሹም ጽ/ቤት በተ...
01/06/2023

በተለምዶ 633ቱ የቤት ማህበር በመባል የሚታወቁትና እጣ ወጥቶላቸው ቦታ ለተረከቡ የቤት ማህበራት የግንባታ ፍቃድ መሰጠት ተጀመረ።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ህንፃ ሹም ጽ/ቤት በተለምዶው 633ቱ የቤት ህ/ስ/ማህበር በመባል የሚታወቀው የቤት ማህበር እጣ ወጥቶላቸው ቦታ ለተረከቡ ማህበራት የግንባታ ፈቃድ መስጠት መጀመሩን ገለፀ ።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ህንፃ ሹም ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሪት ቃልኪዳን ገብሩ እንደገለፁት በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ በልቼ ቀበሌ አካባቢ ቦታ ለተረከቡ ማህበራት የግንባታ ፈቃድ መስጠት መጀመሩን የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወ/ሪት ቃልኪዳን ገብሩ ገልፀዋል ።

አያይዘውም ኃላፊዋ ማህበሩ አገልግሎቱን ለማግኘት ወደ ጽ/ቤቱ ሲመጣ አዲስ የማህበር ፕላን የግንባታ ፈቃድ ለማግኘት የኘላን ስምምነት የሚጠይቁ ማህበራት ከዚህ በታች ያሉትን መስፈርቶች በቅድሚያ አውቀው ማሟላት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል ።

በዚህም መሠረት :-

➛ የኘላን ስምምነት መረጃ ከከተማና መሰረተ ልማት የተሞላ ቅፅ እና የይዞታ ማረጋገጫ ኮፒ ሆኖ ማህተም ያለው፣

➛ የሊዝ ውለታ ኦርጅናል ለህንፃ ሹም ግልባጭ የተደረገውን፣
➛ የማህበር እውቅና የተሰጠበት ደብዳቤ ከእነ አባላት ዝርዝር የያዘ ኮፒ፣
➛ የማህበሩ ሊቀ መንበር/ፀሐፊ ወይም ህጋዊ ውክልና ያለው ሰው፣ መታወቂያ ይዞ መቅረብ አለበት።
➛ወፍራም ክላሴር አንድ እና የኘላን ስምምነት ቅፃቅፅ ኮፒ
➛የአገልግሎት ክፍያ 300 ብር ናቸው።

ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች አሟልተው የመጡ ማህበራት አገልግሎቱን በተቀላጠፈ መልኩ ማግኘት ይችላሉ ሲሉ ገልፀዋል ።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት - ደብረ ብርሃን

በደብረ ብርሃን ከተማ በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት የሳሪያ ቀበሌ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ማዕከል አመታዊ የሰላም ቀንን በደማቅ ሁኔታ በተለያዩ ዝግጅቶች ማ...
01/06/2023

በደብረ ብርሃን ከተማ በእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት የሳሪያ ቀበሌ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ማዕከል አመታዊ የሰላም ቀንን በደማቅ ሁኔታ በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር ጀመረ።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት የሳሪያ ቀበሌ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ማዕከል የሰላም ቀንን በደማቅ ሁኔታ በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበር ጀመረ ።

በፕሮግራሙ ላይ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ድርሻዬ ደበበ ፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ጋሻውበዛ ፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አዲስ ባዩ ፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ በለጡ ደገፉ እንዲሁም የክፍለ ከተማና የቀበሌ አመራሮች ፣ የፀጥታ አካላት ፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ የሀይማኖት አባቶች እና የቀበሌው የማህበረሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

መድረኩን በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የከፈቱት የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ የሳሪያ ቀበሌ ዋና አስተዳዳሪ አቶ የሺጥላ ተ/ፃዲቅ አያይዘውም ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ የሰላም ቀንን መላው ነዋሪዎቻችን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ እናከብራለን ብለዋል።

የቀበሌያችን የፀጥታ ሁኔታ ለማስጠበቅ ከህዝባችን ጋር ተቀናጅተን እንሰራለን ሲሉ ገልፀዋል።

በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ድርሻዬ ደበበ በበኩላቸው ሰላም የሁሉም ኢትዮጵያዊ የአብሮነትና አንድነት መሰረት በመሆኑ ሁላችንም ሰላማችንን በጋራ መጠበቅ አለብን ሲሉ ገልፀዋል ።

ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጎን ሆኖ የስርቆትና ሌሎች ተያያዥ የሰላም ጠንቅ የሆኑትን እንቅስቃሴዎች አሁንም ነቅቶ በመጠበቅ ለቀበሌዋና አካባቢው ሰላም መስፈን ዘብ መቆም እንዳለበትም አስገዝበዋል።
በቀበሌ ብሎም በክፍለ ከተማችን ደረጃ ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ በመግባት የልማት ስራውን ከመቼው ጊዜ በላይ ለማከናወን የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ያበረከተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ሲሉ ዋና ስራ አስፈፃሚው ገልፀዋል።

ሰላም ለሰው ልጆች አስፈላጊና መሠረታዊ ጉዳይ በመሆኑ የሁሉንም አካል ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል።

DBPP

‹‹የኢትዮጵያ መዳኛ ትርክት አብሮነት፣ወንድማማችነትና በጋራ ሀገርን የመገንባት ትርክት ነው፡፡ ››  አቶ ግዛቸው ሙሉነህ***የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ በክልሉ የሚገኙ የዞንና የከተማ አስ...
22/05/2023

‹‹የኢትዮጵያ መዳኛ ትርክት አብሮነት፣ወንድማማችነትና በጋራ ሀገርን የመገንባት ትርክት ነው፡፡ ›› አቶ ግዛቸው ሙሉነህ
***
የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ በክልሉ የሚገኙ የዞንና የከተማ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ወቅታዊ ክልላዊ ሁኔታዎችን መሰረት ያደረገ ውይይት በባህር ዳር ማካሄድ ጀምሯል፡፡

በውይይቱ የተገኙት የአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰት ቀውስ የአመራር መናጋትን ይፈጥራል፤ በዚህ ምክንያት የመልካም አስተዳር ችግሮችን የሚያባብስ እና የአካባቢን ሠላም የሚያደፈርስ በመሆኑ ለዚህ የሚመጥን የሚዲያና የተግባቦት ሥራ በሁሉም አካባቢዎች በአግባቡ መሰራት አለበት ብለዋል፡፡

አሁን ላይ በአገራችንም ሆነ በክልሉ ብዙ አይነት የትርክት መዛነፍ እንዳለ ያነሱት ቢሮ ኃላፊው ሀገርን ሊያድን የሚችለውን ትርክት ማጽናት ያስፈልጋል ብለዋል ፡፡

‹‹የኢትዮጵያ መዳኛ ትርክት አብሮነት፣ወንድማማችነትና በጋራ ሀገርን የመገንባት፣ኢኮኖሚን የማሳደግ ትርክት ነው›› ያሉት አቶ ግዛቸው ከዚህ ውጪ ያሉ ትርክቶች ሀገርን የሚያፈርሱና ለጠላት አጋልጠው የሚሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በዋና ዋና ጉዳዮች ትኩረት አድርጎ የተግባቦት ሥራ አለመስራት በኮሙኒኬሽን መዋቅሩ የሚታይ የተግባቦት ዝንፈት መሆኑን የገለጹት ቢሮ ኃፊው የአብሮነት እሳቤዎችን በሚያጎሉ ክልላዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በትኩረት መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል፡፡

ለህዝቡ መድረስ የሚገባውን ወቅታዊ መረጃ ተግባቦትን በሚያጠናክር መልኩ ሁሉንም የመገናኛ አማራጮች በመጠቀም የኮሙኒኬሽን መዋቅሩ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡


አማራ ክልል ኮሙኒኬሽን

Address

Debre Birhan
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ደብረብርሃን ከተማ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ደብረብርሃን ከተማ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት:

Share