08/10/2025
የኢነርጂ አጠቃቀም፣ ቆጣሪና ተያያዥ ዕቃዎች አጠቃቀም መመሪያ ምን ይላል?
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጥራት ያለው እና ያልተቆራረጠ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር አዳዲስ የአሠራር ሥርዓቶችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
ይሁን እንጂ የአገልግሎት አሰጣጡን የሚያስተጓጉሉ እኩይ ተግባራት በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ትልቅ ተግዳሮት ሆኖበታል፡፡ ተቋሙ እነዚህን እኩይ ተግባራት ለመከላከል የተለያዩ የሕግ ማዕቀፎች ያሉት የኢነርጂ አጠቃቀም፣ ቆጣሪና ተያያዥ ዕቃዎች ምርመራ መመርያ በሥራ ላይ አውሏል፡፡
#በመመሪያው መሰረት:- ➡️ የኃይል ሥርቆት መፈጸሙ የተረጋገጠ አንድ ደንበኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦቱ በጊዜያዊነት ከምሰሶ ወይም ከአቅርቦት መነሻ ላይ እንዲቋረጥበት ይደረጋል፣
➡️የተቋሙ የሕግ አገልግሎት ክስ ይመሰርታል፣ ፖሊስ/አቃቤ ህግ የምርመራ ሂደቱን ማጠናቀቁን በጹሁፍ እስኪያሳዉቅ እንዲሁም ደንበኛዉ የሚጠበቅበትን ክፍያ እስኪፈፅም እና መተማመኛ የዉል ሰነድ ላይ እስኪፈርም ድረስ በስርቆት ምክንያት የተቋረጠው ኃይል ተቋርጦ የሚቆይ ይሆናል፡፡
➡️የኃይል ስርቆት የፈፀመ ደንበኛ ከሌሎች ክፍያ በተጨማሪ ዉል በመተላለፉ አስተዳደራዊ ቅጣት እንደሚጣልበት በመመሪያው ተደንግጓል፡፡
➡️ የመኖሪያ ቤት ደንበኛ ለመጀመሪያ ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት ፈፅሞ ሲገኝ 20 ሺህ ብር ቅጣት ይጣልበታል፤ የጠቅላላ ታሪፍ ተጠቃሚ 500 ሺህ ብር፣ የዝቀተኛ ኢንደስትሪ ታሪፍ ተጠቃሚ 750 ሺህ ብር፣ የመካከለኛ ኢንደስትሪ ታሪፍ ተጠቃሚ 1 ሚሊየን ብር ይቀጣል፡፡
➡️በተያያዘም ከኃይል ስርቆት ድርጊታቸው ያልታረሙና ለሁለተኛ ጊዜ የኃይል ስርቆት ሲፈፅሙ የተገኙ ደንበኞች መጀመሪያ የከፈሉትን ቅጣት እጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡
➡️ በተጨማሪ በኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት ለሁለተኛ ጊዜ ተሳትፎ የነበራቸው የዝቅተኛና መካከለኛ ኢንዱስትሪ ታሪፍ ደንበኞች 2 ሚሊየን ብር፣ የጠቅላላ ታሪፍ ደንበኞች 1 ሚሊየን ብር ተቀማጭ (Security Deposit) ለተቋሙ ማስያዝ እንዳለባቸው መመሪያው ይገልፃል፡፡
➡️ተቀማጭ ያስያዙ ደንበኞች ለተከታታይ ሁለት ዓመታት የተቋሙን ደንብና መመሪያ አክብረው በትክክለኛ መንገድ ኃይል መጠቀማቸው ሲረጋገጥ ያስያዙት ገንዘብ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
➡️ ከተቋሙ ሠራተኞች ውጪ ማንኛውም ግለሰብ የኃይል ስርቆት በሚፈፅም አካል ላይ ጥቆማ ካቀረበ የቅጣቱ 25 በመቶ ክፍያ የሚከፈለው ይሆናል፡፡
የኃይል ስርቆት መፈፀሙን የጠቆመ አካል ማንነት ሚስጥራዊነት የተጠበቀ ሲሆን ስማርት ቆጣሪዎችን በተመለከተ ከሲስተም በቂ መረጃ ማግኘት ስለሚቻል የጥቆማ ማበረታቻ አይከፈልበትም፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት