Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital

Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital Found in Amhara Region North Shoa Zone Debre Birhan Town Kebele 02

የደብረብረሃን አጠ/ስፔ/ሆስፒታል የእውቅናና ሽልማት ፕሮግራም አካሔደ። የደብረብረሃን አጠ/ስፔ/ሆስፒታል በአገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው በ4ኛው ዙር የሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት/መረጃን መሰረ...
13/03/2026

የደብረብረሃን አጠ/ስፔ/ሆስፒታል የእውቅናና ሽልማት ፕሮግራም አካሔደ።
የደብረብረሃን አጠ/ስፔ/ሆስፒታል በአገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው በ4ኛው ዙር የሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት/መረጃን መሰረት ያደረገ የህክምና አገ/ሎት ተወዳድሮ የ5ሚሊየን ብር, የወርቅ ዋንጫ እና የሰርተፍኬት ተሸላሚ በመሆኑ የተነሳ የክልል አመራሮች, የዞን አመራሮች ,የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በዛሬው ዕለት ማለትም በ04/07/2018ዓ.ም ለሆስፒታሉ ጠቅላላ ሰራተኞች,ለባለድርሻ አካላት እና ለተገልጋዩ ማህበረሰብ የእንኳን ደስ ያላችሁ እና የሽልማት ፕሮግራም አካሒዷል ።
በመግቢያው ላይ የሆስፒታሉ ሜ/ዳሬክተር ዶ/ር ንጉሴ ተፈራ የዕለቱን ፕሮግራም በማስተዋወቅ የሆስፒታሉን ስራ-አስኪያጅ የፕሮግራሙን ተሳታ እንኳን ደህና መጣችሁ እንዲሉ ጋብዘዋል።
የሆስፒታሉም ሥራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ሙሉጌታ የፕሮግራሙን ተሳታፊዎች እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት በ4ኛው ዙር ሀገር አቀፍ "የሆስፒታሎች ጥምረት ለጥራት" ውድድር በአገር ደረጃ በአንደኝነት ከተቀመጡት አሥር ሆስፒታሎች መካከል የደብረብረሃን አጠ/ስፔ/ሆስፒታል አንዱ ሆኖ የወርቅ ዋንጫ፣ሰርተፍኬት እና የ5 ሚሊዮን ብር እንዲሸለም የሆስፒታሉ ማኔጅመንት እና አጠቃላይ ሠራተኞች ላደረጉት ያላሰለሰ ጥረት አመስግነዋል።
አያይዘውም ለዚህ ውጤት መምጣት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸውን ክልል ጤና ቢሮ፣ደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር፣የሰሜን ሸዋ ዞን አመራሮች እና ሌሎች ባለድርሻ እና አጋር አካላት ላደረጉት ድጋፍ አመስግነዋል።

በመቀጠልም የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ የተከበሩ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ የዕለቱን ፕሮግራም በመክፈት ሆስፒታሉ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተደጋጋሚ ተወዳድሮ ተሸላሚ የሆነ አንጋፋ ሆስፒታል መሆኑን አስታውሰዋል።

በዚህ ዓመትም ከአሥር ምርጥ ሆስፒታሎች አንዱ ሆኖ በማጠናቀቁ እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ለውጤቱ መገኘት ማኔጅመንቱ እና መላው ሠራተኛ ላደረጉት ከፍተኛ ትጋት በከተማ አስተዳደሩ ስም አመስግነዋል።

ከአሥር ምርጥ ሆስፒታሎች ውስጥ ደረጃ ይዞ ማጠናቀቅ መቻል ትልቅ ስኬት ነው ያሉት፣የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ሰለሞን ጌታቸው ውጤቱ የማናጅመንት አባላትና የጠቅላላ የሆስፒታሉ ሠራተኞች ልፋት ውጤት ነውና እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
በጥረታችሁ አኩሪ ድል በማስመዝገባች እንኳን ደስ አላችሁ ያሉት የደብረ ብርሃን ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በቀለ ገብሬ፣ይህ ስኬት የሁሉም ሠራተኛ የልፋትና የድካም ፍሬ ነው ብለዋል።

ከአሥር የወርቅ ዋንጫ ተሸላሚ ሆስፒታሎች ውስጥ 7ቱ ከአማራ ክልል መሆናቸው የክልሉ መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት ከፍተኛ መሆኑን የሚያስረዳ እንደሆነ በማንሳት ጤና ቢሮው ላደረገው ድጋፍ አመስግነው፣በቀጣይም የሆስፒታሉ ማኅበረሰብ እንደ አንድ ሰው ተባብሮ በመሥራት ውጤቱን ማስቀጠል ይገባል በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በውጤቱ ተደስተናል፣ኮርተናልም ያሉት የሰሜን ሸዋ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ፀዳለ ሰሙንጉስ፣ደብረ ብርሃን ሆስፒታል ለከተማው፣ለሰሜን ሸዋ ሕዝብ እና ለአጎራባች ክልሎች እየሰጠ ላለው አገልግሎት አመስግነዋል ይህም ውጤት በሰራተኛው ዘንድ የበለጠ መነሳሳት ይፈጥራል ብለዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአብክመ ጤና ቢሮ ም/ሃላፊ አቶ መልካሙ ጌትነት የደብረብረሃን አጠ/ስፔ/ሆስፒታል ላስመዘገበው አመርቂ ውጤት አመስግነው ለዚህ ውጤት መምጣት አስተዋፅኦ ያደረጉ አካላትን ሁሉ አመሥግነው በቀጣይም የሆስፒታሉ ሠራተኞች ህዝባቸውን በቅንነት ማገልገል እንዳለባቸው ጥብቅ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም ተግባሩን ላስተባበሩ, ለፈፀሙ, ድጋፍ ላደረጉ ባለሙያዎች, ሠራተኞች, ግለሠቦች እና ተቋማት የዕውቅና እና የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸው መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።

መጋቢት/2018 ዓ.ም
ደብረብሃን

06/03/2026
እንኳን ደስ አላችሁ!!!የደብረ ብርሃን ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መረጃን መሰረት ያደረገ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ(Evidence Based Health care) 4th cycle እ...
06/03/2026

እንኳን ደስ አላችሁ!!!

የደብረ ብርሃን ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መረጃን መሰረት ያደረገ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ(Evidence Based Health care) 4th cycle እንደ ሀገር ካሉ ሁሉም ሆስፒታሎች ተወዳድሮ በአንደኝነት ተርታ ከተመደቡት 10 ሆስፒታሎች አንዱ ሆኖ የ5 ሚልየን ብር ሽልማት ተሸላሚ ሆናል። በክልል ደረጃም ከተሸለሙ 10 ሆስፒታሎች 7ቱን በማሸለም የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ቀዳሚ ሆኗል።

የካቲት 27/2018

በደብረ ብርሃን ሆስፒታል የዲጂታል ጤና ክፍያ  አገልግሎት መጀመሩ ተገለጸ፡፡ደብረ ብርሃን፤ጥቅምት 20/2018(ደብመኮ)፡- ፀደይ ባንክ እና ጤና ሚንስቴር በደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻ...
31/10/2025

በደብረ ብርሃን ሆስፒታል የዲጂታል ጤና ክፍያ አገልግሎት መጀመሩ ተገለጸ፡፡

ደብረ ብርሃን፤ጥቅምት 20/2018(ደብመኮ)፡- ፀደይ ባንክ እና ጤና ሚንስቴር በደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዲጂታል ጤና ክፍያ አገልግሎት አስጀመሩ፡፡

የሆስፒታሉ ሥራ አስኪጅ አቶ ጥላሁን ሙሉጌታ እንደተናገሩት ሆስፒታሉ ዲጂታል ክፍያ አገልግሎት በመጀመሩ ለሆስፒታሉ እና ለተገልጋዮች ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንደሚሰጥ አንስተዋል።

ዲጂታል የክፍያ ሥርዓቱ ከሁሉም የሥራ ክፍሎች በጥራትና በፍጥነት የአገልግሎት ገቢ ለመሰብሰብም ኾነ ለክትትልና ለቁጥር ምቹ ከመኾኑም ባሻገር የሙያተኞችን የሥራ ጫና የሚቀንስ እና ለደንበኞች ሰፊ የክፍ አማራጭ ይዞ የመጣ ነው ብለዋል።

ለተገልጋዮች ጊዜን የሚቆጥብ፣እንግልትን የሚያስቀር ሲኾን ለሆስፒታሉ ደግሞ ለገቢ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ህትመት ይወጣ የነበረውን በሚሊዮን የሚቀጠር ሀብት የሚያስቀር ስለመኾኑም አመልክተዋል።

በዚህም ሆስፒታሉ አሁን እንደ ሀገርም ኾነ እንደ ከተማ ከተደረሰበት የዲጂታላይዜሽን ዕድገት ጋር አብሮ እንዲሄድ የድርሻውን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አንስተዋል።

በፀደይ ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ታደሰ በበኩላቸው ከጤና ሚንስቴር ጋር በመተባበር በደብረ ብርሃን ሆስፒታል እና በደብረ ብርሃን 04 ጤና ጣቢያ የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት ማስጀመራቸውን አስረድተዋል።

ከጤና የዲጂታል ክፍያ ባሻገር የጤና መድህን አገልግሎት ከወረቀት ወደ ዲጂታል ስርዓት ቀይሮ ሆስፒታሎችንና ጤና ጣቢያዎችን አስተሳስሮ የሚሰራ ትልቅ ፓኬጅ ነው ብለዋል።

እንኳን ደስ አለን ደስ አላችሁ!!!የአብክመ ጤና ቢሮ  ጥቅምት 17/2018 ዓም በክልል ደረጃ በተካሄደው  4ኛው ዙር ክልላዊ የጤና ላብራቶሪ ፊስቲባል ላቦራቶሪያችን የሠርተፊኬት ተሸላሚ በመ...
27/10/2025

እንኳን ደስ አለን ደስ አላችሁ!!!

የአብክመ ጤና ቢሮ ጥቅምት 17/2018 ዓም በክልል ደረጃ በተካሄደው 4ኛው ዙር ክልላዊ የጤና ላብራቶሪ ፊስቲባል
ላቦራቶሪያችን የሠርተፊኬት ተሸላሚ በመሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት እንወዳለን ።
በክልል ካሉት 91 የመንግስት ሆስፒታል ውስጥ 16 ቱ በአክሪዲቴሽን በተለያየ ግዜ እውቅና የተሠጣቸው ሲሆን
Step wise process towards accreditation (SLIPTA) በመተግበር ሌሎችም በከተማ አስተዳደሩ ካሉ 10 የመንግስት የጤና ተቋማት 4ቱ star/ኮኮብ 3 እና በላይ ደረጃ በማስመዝገብ እውቅና እና የማበረታቻ የምስክር ወረቀት ተበረከተላቸው።

ፊስቲባሉ ጠንካራ የላብራቶሪ ስርዓት ጥራት ላለው የጤና አገልግሎት በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን እየተወሳሰበ የመጣውን የጤና ችግር ወይንም በሽታ ለመቋቋም አለማቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የላብራቶሪ ስርአት መገንባት ወሳኝ እና አስፈላጊ የሚልበት ወቅት ላይ እንገኛለን ።

በዚህም መሰረት በላብራቶሪ ጥራት አስተዳደር (SLIPTA ) መስፈርት ከክልል እስከ ፊደራሉ ባሉ ተቋማት ተለክተው የኮኮብ ደረጃ ያገኙ፦
1ኛ. ሀኪም ግዛው ጠቅላላ ሆስፒታል star 4(ኮኮብ 4)
2ኛ. ደብረብርሃን 04 ጤና ጣቢያ star 3(ኮኮብ 3)
3ኛ. ጫጫ ጤና ጣቢያ star 3 (ኮኮብ 3)እና
4ኛ. በISO 15189 አለማቀፍ የህክምና ላብራቶሪ ጥራት ማረጋገጫ መስፈርት መሰረት በGen expert የደብረብርሃን ኮምፕሬሄንሲቪ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እውቅናን አግኝተዋል።

ለጥራት ልዩ ትኩረት በመስጠት በቀጣይ አጠናክረን እንሠራለን ።

ደብረ ብርሃን ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
ጥቅምት 17/2018

ደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄንሲቪ ስፔሻይዝድ ሆስፒታል  ከኪዩር ብላይንድነስ ጋር በመተባበር ከኅዳር 15 እስከ 21/2018 ዓ.ም  ድረስ ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ህክምና እንደሚሰጥ አስታወቀ፤ደብ...
20/10/2025

ደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄንሲቪ ስፔሻይዝድ ሆስፒታል ከኪዩር ብላይንድነስ ጋር በመተባበር ከኅዳር 15 እስከ 21/2018 ዓ.ም ድረስ ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ህክምና እንደሚሰጥ አስታወቀ፤

ደብረ ብርሃን፤ጥቅምት 10/2018(ደብመኮ)፡-ሆስፒታሉ ከኪዩር ብላይንድነስ ጋር በመተባበር ከኅዳር 15 እስከ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በሚሰጠው የዓይን ሞራ ግርዶሽ እና የዓይን ቆብ ህክምና አስመልክቶ ከባለድረሽ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡

የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ሙሉጌታ እንደገለጹት ኪዩር ብላይንድነስ ከተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ከኅዳር 15 እስከ 21/2018 ዓ.ም ድረስ ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ እና የዓይን ቆብ ህክምና በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ እንደሚሰጥ አስታወቀዋል፡፡

በዚህ ዙር 2 ሺህ ወገኖችን ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ጠቅሰው ደብረ ብርሃን፣ሙሉ ሰሜን ሸዋ እና አጎራባች ወረዳዎች ውስጥ ያሉት የችግሩ ሰለባ የኾኑ ሁሉ የህክምና፣የምግብ፣የመኝታና የትራንስፖረት ሙሉ ወጫቸው ተሸፍኖ በነፃ አገልግሎቱ እንደሚሰጣቸው አመልክተዋል፡፡

የልየታ ስራው ከኅዳር 1 እስከ ኅዳር 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በየአቅራቢያቸው በሚገኙ በተመረጡት ጤና ተቋማት በአካል እየተገኙ መታየት እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪ የኾኑ ደግሞ በደብረ ብርሃን ሆስፒታል በተመሳሳይ ከኅዳር 1 እስከ ኅዳር 14 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በአካል ተገኝተው በመመዝገብ መታከም እንደሚችሉ አስታውቀዋል፡፡

ስራው እንዲሳካም በየደረጃው የሚመለከታቸው አመራሮች፣የጤና፣የትራንስፖርት፣የፀጥታ፣የሚዲያ ተቋማት በዋናነት ተግባሩን በባለቤትነት ወስደው የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የደብረ ብርሃን ሆስፒታል የዓይን ሰብ ስፔሻሊስት ዶክተር ሙሉቀን በዓይን ሞራ ግርዶሽ ምክንያት በዓለም፣በሀገራችንና በክልላችን በርካታ ሰዎች የዓይናቸውን ብርሃን እያጡ መኾኑን ጠቅሰው በአግባቡ ከታከሙት መዳን እንደሚቻል አስረድተዋል፡፡

ደብረ ብርሃን ሆስፒታል ከኪዩር ብላይንድነስ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ባለፈው ዓመት ከ1 ሺህ 5 መቶ ለሚበልጡ ሰዎች በነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ የዓይን ቆብ ህክምና መስጠቱትን አስታውሰዋል፡፡

አሁንም ከኅዳር 15 እስከ 21 ድረስ በሚሰጠው ህክምና በወጣው መርሐ ግብር መሰረት የአግልግሎቱ ተጠቃሚ መኾን እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡

የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በቀለ ገብሬ ውይይቱን ሲያጠቃልሉ እንደገለጹት ደብረ ብርሃን ሆስፒታል ከኪዩር ብላይንድነስ ጋር በመተባበ እስካሁን ከ2 ሺህ 5 መቶ ለሚበልጡ ወገኖች ህክምና ሰጥቶ የዓይናቸው ብርሃን እንዲመለስ በማድረጉ አመስግነዋል፡፡

በነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ይሰጣል የሚል ዜና መስማት እጅግ አስደሳች መኾኑንም ተናግረዋል፡፡

መረጃውን ለሚመለከታቸው በማድረስም ኾነ ለስራው መሳካት ባለድርሻ አካላት፣በየደረጃው ያሉ የስራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ኃላፊነታቸውን በተገቢው እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ከተማው የራሱን የቤት ስራ ወስዶ የችግሩ ተጠቂዎች ተጠቃሚ እንዲኾኑ የሚጠበቅበትን እንደሚሰራም ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡

ደብኮ

የደብረ ብርሃን  ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል  በአሜሪካ ሄልዝ አሊየንስ የበጀት ድጋፍ የተከታታይ ሙያ ስልጠና ማዕከል  አስመረቀደብረ ብርሃን፤መስከረም 15/2018 (ደብመኮ)፡- በአ...
25/09/2025

የደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአሜሪካ ሄልዝ አሊየንስ የበጀት ድጋፍ የተከታታይ ሙያ ስልጠና ማዕከል አስመረቀ

ደብረ ብርሃን፤መስከረም 15/2018 (ደብመኮ)፡- በአሜሪካ ኢንተርናሽል ሄልዝ አሊያንስ የገንዝብ ድጋፍ ደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ያስገነባው የተከታታይ ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከል ግንባታና እድሳት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ኾነ፡፡

የደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ንጉሴ ተፈራ እንደገለጹት አሜሪካን ኢንተርናሽናል አሊያንስ ከሆስፒታሉ ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የተከታታይ ሙያ ማሰልጠኛ ማዕከል መገንባቱንና የነበረው መታደሱን አስታውቀዋል፡፡

ማዕከሉ በአስፈላጊ ግብዓቶች የተደራጀ፣የነርሶች የክህሎት ማጎልበቻ ላብራቶሪ ዘመኑን በዋጀ የህክምና መሰሪያዎች እና መርጃ ግብዓቶች የተደራጀ በመኾኑ ለስራቸው አቅም እንደሚጨምር ጠቅሰው ድርጅቱን አመስግነዋል፡፡

የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸት ማዕከሉን መርቀው ስራ ያስጀመሩ ሲኾን፤ የስልጠና ማዕከሉ ሙሉ እድሳት ተደርጎለት እና አስፈላጊ ልዩ ልዩ የህክምና መሳሪያዎች ተሟልተውለት ለስራ ዝግጁ እንዲኾ ጊዜያቸውን፣ዕውቀታቸውንና ገንዘባቸውን ለሰጡ ሁሉ ከንቲባ በድሉ አመስግነዋል፡፡

በተለይም የተግባር ስልልጠና መስጫ ማዕከሎችን በመገንባት ህክምናና የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን በማሟላት ለምረቃ እንዲበቃ የዶክተር ጆሴፍ ማሲ ቤተሰቦች ላደረጉት ድጋፍ አመስግነው ዕውቅና ዕውቅና በመስጠት በቀጣይም ድጋፋቸው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡

ደብረ ብርሃን ሆስፒታል ከጊዜ ወደ ጊዜ አቅሙን እያሳደገ ለከተማውና ለአካባቢው ሕዝብ የተሟላ የህክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ አንስተዋል።

በቀጣይም ተወዳዳሪ ለመኾ ተመሳሳይ የትብብር አሰራሮችን በማመቻቸት የሆስፒታሉን አሰራር የበለጠ ማዘመን እንደሚያስፈልግም አመልክተዋል፡፡

የAIHA(የአሜሪካን ኢንተርናሽል አሊያንስ ካንትሪ ዳይሪክተር) ወይዘሮ ቅድስት ኃይሉ ድርጅታቸው ከደብረ ብርሃን ኮፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝ ሆስፒታል ጋር በመተባበር የስልጠና ማዕከል በመገንባት፣ግብዓት በማሟላት በኩል ጥሩ ስራ መስራቱን አንስተዋል፡፡

ለስራው ውጤታማነት የሆስፒታሉ የስራ ኃላፊዎች ቀና መኾን ክፍተኛውን ድርሻ የሚወስድ መኾኑንም ጠቅሰው አመስግነዋል፡፡

የአሜሪካን ኢንተርናሽል አሊያንስ ወደ ፊትም ከሆስፒታሉ ጋር ተባብሮ መስራቱን እንደሚቀጥል ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡

ደመኮ

ሆስፒታሉ ዘመናዊ የሲቲ ስካን ማሽን ከአማራ ክልል ጤና ቢሮ  ተበረከተለት ደብረ ብርሃን፤ሰኔ 29/2017 (ደብመኮ):- የደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄኔሲቭ  ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ78 ሚሊዮን ብ...
06/07/2025

ሆስፒታሉ ዘመናዊ የሲቲ ስካን ማሽን ከአማራ ክልል ጤና ቢሮ ተበረከተለት

ደብረ ብርሃን፤ሰኔ 29/2017 (ደብመኮ):- የደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄኔሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ78 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የኾነበት ዘመናዊ የሲቲ ስካን(CT SCAN) ማሽን ከክልሉ ጤና ቢሮ ድጋፍ ተደርጎለታል።

በርክክቡ መርሐ ግብር ላይ የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸትን ጨምሮ የክልልና የከተማው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣የሆስፒታሉ ማኅበረሰብ እንዲሁም የኅብረተሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በቀለ ገብሬ የሕዝባችን የዘመናት ጥያቄ የመለስ ዘመናዊ የሲቲ ስካን ማሽን የተረከተበት ዕለት በመኾኑ እንኳን ደስ አለን ብለዋል።

ከዚህም በፊት ይህ ማሽን ባለመኖሩ ህዝቡ ለተለያየ እንግልት ይዳረግ እንደነበር አስታውሰዋል።የክልሉ ጤና ቢሮ ከ78 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ችግሩ እንዲፈታ ስላደረገ አመስግነዋል።

የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሜዴካል ዳይሬክተር ዶክተር ንጉሴ ተፈራ በበኩላቸው የሆስፒታሉን እና የማኅበረሰቡ ጥያቄ የመለሰ፣ለረጂም ጊዜ የተጠበቀ ማሽን ስለኾነ በጣም ደስ ብልናል ብለዋል።

የሲቲ ስካን ማሽኑ እንደሀገር የህክምናውን አገልግሎት ማጠናከር የሚለውን ስትራቴጂ ለመተግበር ጥቅሙ ከፍተኛ እንደኾነ አንስተው የክልሉ ጤና ቢሮ ገዝቶ ስለሰጣቸው ከልብ እናመሰግናለን ብለዋል።

የእስካሁኑ የሆስፒታሉ አገልግሎት እንደተጠበቀ ኾኖ በዚህ ሲቲ ስካን ታግዘው ሲሰሩ የሚሰጡትን የህክምና ጥራት ከማስጠበቁም ባሻገር ወደ ሌላ ጤና ተቋም ለምርመራ የሚላኩ ታካሚዎች አይኖሩም በማለት አብራርተዋል።

ደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለከተማ ብቻ ሳይኾን ለሰሜን ሸዋና ለአጎራባች ወረዳዎች ደረጃውን የጠበቀ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ፣በህዝብ የተወደ ተቋም መኾኑን የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸት ምስክርነት ሰጥተዋል።

ይሁን እንጂ ከዚህ በፊት የሲቲ ስካን ማሽን ባለመኖሩ ተገልጋው ለከፍተኛ ወጪና እንግልት ይዳረግ እንደነበር አስታውሰው የክልሉ ጤና ቢሮ ያበረከተው ዘመናዊ የሲቲ ስካን ማሽን የህዝቡን ውጣ ውረድ ያስቀረና የረጂም ጊዜ የህዝቡን ጥያቄ የመለስ በመኾኑ እንኳን ደስ አለን ብለዋል።የክልሉ ጤና ቢሮ ስላደረገው ድጋፍም በከተማው ህዝብ ስም አመስግነዋል።

ማሽኑን ለሆስፒታሉ ተጨማሪ ትልቅ አቅም የፈጠረ መኾኑን ጠቅሰው በአግባቡ ሥራ ላይ በማዋል የመንግሥትን አክሞ የማዳን ስትራቴጂ ግብ እንዲያሳካ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የኅበረተሰብ ተወካዮች በሰጡት አስተያየት የዓመታት ጥያቄያቸው ምላሽ በማግስቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት ወደ አዲስ አበባ ሄደውና በግል ከፍለው መታከም ያልቻሉ ህመምተኞች ማሽኑ በዚህ ሆስፒታል ባለመኖሩ መሞታቸውን ስታውሰዋል።

በቀጣይ በተመጣጣኝ ክፍያ አገልግሎቱን ማግኘት የሚያስችል ስለኾነ ለህዝቡ ትልቅ ዕድል ነው ሲሉም አክለዋል።

ደብመኮ

ሆስፒታሉ ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ የህክምና ካርድ አገልግሎት (Fully Electronic Medical Record) በይፋ አስጀመረደብረብርሃን፤ሚያዚያ15/2017 ዓ.ም የደብረብርሃን ኮምፕሬ...
24/04/2025

ሆስፒታሉ ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ የህክምና ካርድ አገልግሎት (Fully Electronic Medical Record) በይፋ አስጀመረ

ደብረብርሃን፤ሚያዚያ15/2017 ዓ.ም የደብረብርሃን ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ የህክምና ካርድ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታውቋል፡፡

አገልግሎቱን የደብረብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸት ያስጀመሩት ሲሆን በመርሀ ግብሩ ላይ የክልል፣የከተማ፣የህብረተሰብ ተወካዮች፣የሆስፒታሉ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተግኝተዋል።

የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ሙሉጌታ እንደገለጹት ሆስፒታላቸው ከወረቀት ንክኪ ነፃ የሆነ የህክምና ካርድ አገልግሎት ለመስጠት ሰፊ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቶ ዛሬ በአውቶሜሽን ሙሉ በሙሉ ስራ ማስጀመሩን አንስተዋል፡፡

ስራው በቴክኖሎጂ መደገፉ ለታካሚዎች፣፣ለባለሙያዎችና ለሆስፒታሉ ጥቅሙ ከፍያለ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ረጂም የካርድ ሰልፍ የሚያስቀር፣የታካሚዎችን የቆይታ ጊዜ የሚያሳጥርና የካርድ ጠፋብኝ ቅሬታን የሚያስቀር እንዲሁም የተገልጋዮችን እርካታ የሚጨምር መሆኑን ለአብነት አብራርተዋል፡፡
ሲስተሙ ተቋማቸው በየዓመቱ ለህትመት የሚያወጣውን ወጪ ከመቀነሱም በላይ ተወዳዳሪ የጤና ተቋም ለመፍጠር እንደሚያስችለውም ጠቁመዋል፡

ሆስፒታሉ በ2016 ዓ.ም ብቻ ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ ለህትመት ማውጣቱን ጠቁመዋል።

ወደ ስራ የገባው አዲሱ ቴክኖሎጂ ከ23 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሆነበት መሆኑን ጠቅሰው በጤና ሚንስቴር፣በክልሉ ጤና ቢሮ፣በዶክተር ድረሴ እና በሆስፒታሉ መሸፈኑን አስታውቀዋል።

የደብረብርሃን ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በቀለ ገብሬ በበኩላቸው እንደገለጹት ሆስፒታሉ ከወረቀት ንክኪ ሙሉ በሙሉ ነፃ የሆነ የህክምና አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ለደብረብርሃን፣ለሰሜን ሸዋ ዞንና እና ለአጎራባች ክልል ህዝብ ትልቅ ብስራትና ጠቀሜታውም ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል።

ቴክኖሎጂው ካርድ ለማውጣት የሚወስደውን ጊዜ በመቀነስ፣እንግልትን በማስቀረት፣የሠራተኛውን የስራ ጫና በማቅለል ጥራት ያለው የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ፋይዳው ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ ሀኪም ግዛው ሆስፒታል የተጀመረው ከወረቀት ንክኪ የህክምና አገልግሎት ተሞክሮ በደብረብርሃን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል መደገሙ ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።

በከተማው በሚገኙ በሁሉም ጤና ተቋማት ለመተግበር እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

የደብረብርሃን ከተማ ስማርት ሲቲ ዕቅድ ይኽ ዓይነት የዲጂታላይዜሽን ትግበራ ስራውን እንደሚያፋጥነው አመልክተዋል።

ስራው እንዲሳካ በማስተባበር ተቋማቸውና በየደረጃው የሚመለከታቸው አካላት ላበረከቱት አስተዋጽኦ፣እንዲሁም የሙያና የግብዓት ድጋፍ ያደረጉ ተቋማትንና ግለሰቦች አመስግነዋል።

የደብረብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባና የሆስፒታሉ የቦርድ ሰብሳቢ የተከበሩ በድሉ ውብሸት እንደተናገሩት ዲጂታላይዜሽን አገልግሎት አሰጣጥ በማቀላጠፍ የመልካም አስተዳደር ችግር መፍቻ አንዱ መሳሪያ መሆኑን አንስተዋል።
ዘመኑ የሚጠይቀውን በቴክኖሎጂ ተደግፎ ፈጣንና ቀልጣፋ የህክምና አገልግሎት ለህብረተሰቡ መስጠት መቻል ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።

ጤና ጣቢያዎችና ሆስፒታሎች ወደ ዲጂታል ቴክኖሎጂ መግባታቸው ተገቢና አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው ስራው ወደፊትም ውጤታማ ሆኖ እንዲዘልቅ ሁሉም የየድርሻውን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ ከንቲባ በድሉ አሳስበዋል።

ስራው በውጤታማነት እንዲጠናቀቅ ያደረጉ አካላትን ሁሉ አመስግነዋል።

telegram link:
https://t.me/DBCSH1
Facebook link:
https://www.facebook.com/DBCSH

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችና ለሆስፒታላችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።መልካም ስግደት!https://t.me...
18/04/2025

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችና ለሆስፒታላችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

መልካም ስግደት!

https://t.me/DBCSH1
https://www.facebook.com/DBCSH

የአብክመ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ገስጥ ጥላሁን እና የደብረ ብርሃን ከተማ አስተደዳደር ጤና መምሪያ ሃላፊዎች አቶ በቀለ ገብሬ እና አቶ ሰይድ አሰን በደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ...
15/04/2025

የአብክመ ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ገስጥ ጥላሁን እና የደብረ ብርሃን ከተማ አስተደዳደር ጤና መምሪያ ሃላፊዎች አቶ በቀለ ገብሬ እና አቶ ሰይድ አሰን በደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለአዋቂዎች እና ለጨቅላ ህፃናት ፅኑ ህሙማን አገልግሎት የሚዉል ባለ አራት ወለል (G+4) የመጀመሪያ ዙር ግራወንድ ግንባታን ጎበኙ፡፡ በጉብኝቱ ወቅት የተጀመረውን የግንባታ ሂደት አድንቀው ያለውን የክፍል ጥበት ለመቅረፍ ከዚህ በላይ መፍጠን እንደሚገባዉ ለግንባታ ተቆጣጣሪው መሃንዲስ ኢንጂነር በሩክ ጋር የስራ መመሪያ ተሰጥቶታል፡፡ የጤና ቢሮ ሃላፊው እና የጤና መምሪያው ሃላፊዎች ለግንባታው እና ለአጠቃላይ ስራው በቅርበት እንደሚደግፉ አረጋግጠዋል፡፡
telegram link:
https://t.me/DBCSH1
Facebook link:
https://www.facebook.com/DBCSH

ሚያዚያ 7/2017 ዓ.ም

የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከክልል ጤና ቢሮና ዩኒሴፍ ባገኘዉ የበጀት ድጋፍ ለአዋቂዎች እና ለጨቅላ ህፃናት ፅኑ ህክምና አገልግሎት የሚውል ባለ 4 ወለል ህንፃ (G+4) ...
12/04/2025

የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከክልል ጤና ቢሮና ዩኒሴፍ ባገኘዉ የበጀት ድጋፍ ለአዋቂዎች እና ለጨቅላ ህፃናት ፅኑ ህክምና አገልግሎት የሚውል ባለ 4 ወለል ህንፃ (G+4) ግንባታ የመጀመሪያ ዙር ግንባታ የመሰረት ቁፋሮ ስራ ተጀምሯል፡፡ ይህ የመጀመሪያ ዙር ግንባታ የመሬት ወለሉ (ግራወንዱን) በአጭር ጊዜ በ3 ወር ውስጥ ይተናቀቃል ተብሎ እቅድ የተያዘ ሲሆን ግንባታው ሲጠናቀቅ የክፍል ጥበት እና የአልጋ እጥረት ላለባቸው ለአዋቂዎች ፅኑ ህክምና አገልግሎት ትልቅ እፎይታ እንደሚሰጥ ይታመናል፡፡ ለ88 ዓመት እድሜ ጠገብ ለሆነው ሆስፒታል ጥሩ ገፅታ ያላብሰዋል ተብሎ ይገመታል፡፡ በቀጣይም ደረጃ በደረጃ ግንባታዉን የማስቀጠል ስራ ተሰርቶ የህፃናት ፅኑ ህክምናንና የተጨናነቀ የተኝቶ ህክምናን በመፍታት ረገድ አስተዋፅኦ ይኖረዋል። ይህ ግንባታ እንዲጀመር ድጋፍ ላደረጋችሁ አንዲሁም ላስተባበራችሁ አካላት በሙሉ ምስጋናችን የላቀ ነው፡፡
telegram link:
https://t.me/DBCSH1
Facebook link:
https://www.facebook.com/DBCSH

ሚያዚያ 2017 ዓ.ም

Address

Debre Birhan

Telephone

+251116811333

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital:

Share