Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital

Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital Found in Amhara Region North Shoa Zone Debre Birhan Town Kebele 02

አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አምስት ልጆችን በሰላም ተገላገለች!በትግራይ ክልል አበርገለ የጭላ ወረዳ በሚገኘው የጭላ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከስምረት ጤና ጣቢያ የመጣች አንዲት እናት አምስ...
08/09/2026

አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አምስት ልጆችን በሰላም ተገላገለች!

በትግራይ ክልል አበርገለ የጭላ ወረዳ በሚገኘው የጭላ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከስምረት ጤና ጣቢያ የመጣች አንዲት እናት አምስት ህፃናትን በሰላም መገላገሏን የሆስፒታሉ የጤና ባለሙያዎች አስታወቁ።

በወቅቱ እናቲቱን ያወለዱት አዋልድ ነርስ ገብረዮሐንስ ደስታ እንደገለጹት፡ እናቲቱ በማህፀኗ አምስት ህፃናትን የያዘች የነበረች ሲሆን፣ አራቱ ህፃናት ሙሉ እድገታቸውን ጨርሰው በጤና ተወልደዋል።

አምስተኛው ህፃን በሁለተኛው የእድገት ደረጃ (በአምስተኛው ወር አካባቢ) እድገቱ የቆመ ቢሆንም፣ እናቲቱ አራቱን ሙሉ ጤነኛ ህፃናት እና አንዱን እድገቱን ያላጠናቀቀውን ህፃን ጨምሮ በድምሩ አምስት ህፃናትን በሰላም ተገላግላለች።

ስለ እናቲቱ የተገለጹ አስደናቂ እውነታዎች፡እናቲቱ በቤተሰቧ የመንታ ዘር ያላት ከመሆኑም በላይ፣ እሷ ራሷ የመንታ ልጅ ነች! ይህ የመጀመሪያ ልጅ መውለዷ (በኩር) እንደሆነ ተገልጿል።

በአሁኑ ወቅት እናቲቱ ከባድ የኢኮኖሚ ችግር እንዳለባት የሆስፒታሉ ባለሙያዎች አክለው ገልጸዋል።

በአሁኑ ሰዓት የቅርብ ክትትል እየተደረገላቸው የሚገኙት እናትና ህፃናት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ተረጋግጧል።
ለበለጠ መረጃ:-
Telegram:- https://t.me/DBCSH2
page:- https://www.facebook.com/DBCSH
Tiktok:- https://tiktok.com/

(መረጃው፡- የአበርገለ የጭላ ወረዳ የመረጃና ህዝብ ግንኙነት ጽህፈት ቤት ነው)

የደብረብርሃን አጠ/ስፔ ሆስፒታል በከተማች እና በሰሜን ሸዋ የመጀመሪያ የሆነውን AI supported 4D Ultrasound ባለቤት ሆነ!የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከሚሰጣ...
08/09/2026

የደብረብርሃን አጠ/ስፔ ሆስፒታል በከተማች እና በሰሜን ሸዋ የመጀመሪያ የሆነውን AI supported 4D Ultrasound ባለቤት ሆነ!
የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች ውስጥ የራጅ እና የአልትራሳውንድ ምርመራ አንዱ ሲሆን ይህን ምርመራ ለማሳለጥ ይረዳ ዘንድ ከTzu chi Foundation በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በ6,000,000 ብር ወጪ አዲስና ዘመናዊ የአልትራሳውንድ (4D Doppler Ultrasound) ማሽን ተገዝቶ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ሙሉጌታ አስታውቀዋል።
ስራ አስኪያጁ እንደገለፁት ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ የታካሚዎችን የምርመራ ጥራት ከፍ ለማድረግ፣ በሽታዎችን አስቀድሞ ለመለየት እና የተሻለ የሕክምና ክትትል ለማድረግ እንዲሁም ወደሌሎች የጤና ተቋማት የሚደረገውን እንግልት በመቀነስ ደረጃ ትልቅ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። ዶ/ር ንጉሴ ተፈራ የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር በበኩላቸው የspeciality and sub-specialty ፕሮግራም ማስፋፋትና ማስጀመር ፕሮግራም አካል የሆነው እና ተቋሙን በዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎች ከማደራጀት አንፃር ከTZU CHI FOUNDATION በተገኘ fund የተገዛ መሆኑን ገልፀው፣ የአልትራሳውንድ ማሽኑ በሰሜን ሸዋ ዞን እና በደብረብርሃን ከተማ ብቸኛው ማሽን እንደሆነና AI (Arteficial intteligence Supported መሆኑን ገልፀዋል።
የሚያከናውናቸው ዋና ዋና ምርመራዎች፡-
-የልብና የደምስር ምርመራ
-የማህፀን ምርመራ
-የነርቭ ምርመራ
-የአጥንት ምርመራ
-አጠቃላይ የሆድ ምርመራ (የኩላሊት፣ የጉበት፣ የአንጀት የመሳሰሉት) አገልግሎቶች ይሰጣል ሲሉ የሆስፒታሉ የራዲዮሎጂ ክፍል ሃላፊ አቶ ሃብታሙ ገላነው ገልፀዋሎ።
በመጨረሻም የተገዛው ማሽን የገጠማ ስራ የተሰራ ሲሆን የህክምና መሳሪያ ጥገና ክፍል ባለሙያዎች ባሉበት ለራዲዮሎጂ ክፍል ባለሙያዎች የስራ ላይ ስልጠና በመስጠት በሙሉ አቅሙ ስራ እንዲጀምር ተደርጓል።
ለበለጠ መረጃ:-
Telegram:- https://t.me/DBCSH2
page:- https://www.facebook.com/DBCSH
Tiktok:- https://tiktok.com/

ደብረብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል!
ጳጉሜ/2018 ዓ.ም

የደብረ ብርሃን ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላቦራቶሪ በኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት (EAS) በ ISO 15189:2022 መስፈርት መሠረት የተደረገለትን የክትትል ምዘና በስኬት አ...
04/09/2026

የደብረ ብርሃን ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላቦራቶሪ በኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት (EAS) በ ISO 15189:2022 መስፈርት መሠረት የተደረገለትን የክትትል ምዘና በስኬት አጠናቀቀ
ደብረ ብርሃን፣ ኢትዮጵያ

የሆስፒታላችን ላቦራቶሪ ከነሐሴ 27 እስከ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት (EAS) የተደረገበትን የክትትል ምዘና በአዲሱና በተሻሻለው የዓለም አቀፍ ISO 15189:2022 መስፈርት መሠረት በስኬት አጠናቋል።
ይህ ስኬት ላቦራቶሪያችን የሞለኪውላር ምርመራ ዘርፍ ከፍተኛ የጥራት ደረጃና አስተማማኝ አሰራር ያለው መሆኑን ያረጋገጠ ሲሆን፣
🔹 የጂን ኤክስፐርት (GeneXpert MTB/RIF) ምርመራ
🔹 የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ መጠን (HIV Viral Load) ምርመራ
🔹 የሕፃናት የቅድመ ኤች.አይ.ቪ (EID) ምርመራ
ላቦራቶሪያችን ላለፉት ተከታታይ ዓመታት ዓለም አቀፍ የጥራት ዕውቅናውን (Accreditation) አስጠብቆ የቆየ ሲሆን፣ ዋና ራዕያችንም ለማኅበረሰባችን ጥራት ያለው የላቦራቶሪ አገልግሎት መስጠት ነው።

"ይህ የክትትል ምዘና ስኬት ላቦራቶሪያችን ለጥራትና ለታካሚዎች ደህንነት የሚሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት የሚያሳይ ሲሆን፣ በቀጣይም የዕውቅና ዘርፎቻችንን ወደ ሌሎች የምርመራ ዓይነቶች በማስፋፋት አጠቃላይ የአገልግሎት ጥራታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።"
(የላቦራቶሪ አስተባባሪው ጌታው አለማየሁ)

የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ንጉሴ ተፈራ የባለሙያዎችን ተነሳሽነትና ትጋት አድንቀው በቀጣይ ሌሎች ምርመራዎችንም አለም አቀፍ መስፈርቶች መሠረት እንዲሠሩ ጥረት ማድረግ ይገባል ብለዋል ::
👏
ለዚህ ታላቅ ስኬት አስተዋጽኦ ላደረጋችሁ ሙሉ የላቦራቶሪ ባለሙያዎች ና አባላት እንዲሁም የሆስፒታሉ ማኔጅመንት እንኳን ደስ አለችሁ!

የደብረብረሃን ኮ/ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የተግባራት እቅድ አፈፃፀም እና የ2019 ዓ.ም እቅድ ትውውቅ ፕሮግራም አካሔደ።  የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ሙሉጌታ ተሳታፊ...
20/08/2026

የደብረብረሃን ኮ/ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የተግባራት እቅድ አፈፃፀም እና የ2019 ዓ.ም እቅድ ትውውቅ ፕሮግራም አካሔደ። የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ሙሉጌታ ተሳታፊዎችን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በማስተላለፍ ሆስፒታሉ በበጀት ዓመቱ በርካታ ተግባራትን ያከናወነ ሲሆን በተለይ በEBC 4th Cycle በሀገር አቀፍ ደረጃ ካሉ ምርጥ አስር ሆስፒታሎች መካከል በመካተት የ5,000,000 ብር እና የክርስቲያል ዋንጫ ሽልማት ተሸላሚ ሆኗል በማለት የመድረኩን ተሳታፊዎች እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል። በመቀጠል የደብረብረሃን ከተማ ጤና መምሪያ ምክትል ሀላፊ አቶ ሠይድ አሰን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በመክፈቻ ንግግራቸውም ደብረብረሃን ሆስፒታል በርካታ ስራዎችን በመስራታችሁ የበርካታ ታካሚዎችን ህይዎት መታደግ ተችሏል ይህ በበለጠ እንዲጠናከር በሚል ሀሳብ መድረኩን ከፍተዋል ።በመቀጠልም የሆስፒታሉ የፕላን ፕሮግራም አስተባባሪ ወ/ሮ ፅጌ ታዬ የሆስፒታሉን የ2018 ዓ.ም የተግባራት አፈፃፀም ሪፓርት እና የ2019 ዓ.ም እቅድ አቅርበዋል። በቀረበው ሪፓርት ላይ ሠፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ከተሳታፊዎችም በቀረበው ሪፓርት ላይ በርካታ ጥያቄዎች የተነሡ ሲሆን በተነሡትም ጥያቄዎች ላይ የሚመለከታቸው አካላት መልስ ሠጥተዋል።
በመቀጠልም የደብረብረሃን ከተማ ጤና መምሪያ ም/ሃላፊ አቶ ሠይድ አሰን እና የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ሙሉጌታ የዕለቱ ፕሮግራም ሲያጠቃልሉ በ2019 ዓ. ም ሆስፒታሉ በሚከተሉትን ተግባራት ላይ ትኩረት አደርጎ መስራት እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጠዋል
1. ጥራት ያለው, ወቅቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት በመስጠት በሆስፒታሉ ውስጥ የታካሚዎችን የቆይታ ጊዜ መቀነስ ብሎም ሞትን መቀነስ
2. የውስጥ ገቢን በአግባቡ መሰብሰብ
3. በሆስፒታሉ ውስጥ ያለውን የሰው ሀይል በአግባቡ መከታተል እና ስምሪት መስጠት
4. ከወረቀት ነፃ የሆነ አገልግሎትን ማጠናከር
5. በመጨረሻም የ2019 ዓ.ም እቅድን በአግባቡ መፈፀም። በመጨረሻም በተለያዩ ተግባራት በ2018 ዓ.ም የተሻለ አፈፃፀም ላላቸው ሀላፊዎች እና ክፍሎች የማበረታቻ ሽልማት በመስጠት የዕለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል።
ነሃሴ/2018 ዓ.ም
ደብረብረሃን ኮም/ስፔ/ሆስፒታል

አስደሳች ዜና!!! የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዓይን የጨረር ህክምና አገልግሎት መስጠት ጀመረ። የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከሚሰጣቸው የህክምና አገል...
15/08/2026

አስደሳች ዜና!!!

የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዓይን የጨረር ህክምና አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከሚሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች መካከል አንዱ የዓይን ህክምና ሲሆን በዚህም በተመላለሽ ህክምና፣ በተኝቶ ህክምና ፣ በቀዶ ህክምና እና በመነጸር ህክምና በየጊዜው አገልግሎቱን እያዘመነ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል።

በዛሬው ዕለት ደግሞ ህክምናውን የበለጠ ለማዘመን የሚያግዘውን በጨረር ቀዶ ህክምና ('Laser Eye surgery') ለመስራት የሚያግዘውን የህምና መሳሪያ ከኪዩር ብላይንድነስ ፕሮጀክት ከሚባል ግብረሰናይ ድርጅት በእርዳታ በመረከብ ህክምና መስጠት መጀመሩን ሆስፒታሉ በደስታ ያበስራል።

በዚህም አገልግሎቱን ለማግኘት አዲስ አበባ ድረስ ይላኩ የነበሩ ታካሚዎችን ከእንግልት ይታደጋል ተብሎ ይጠበቃል ።

በመጨረሻም አገልግሎቱ በመጀመሩ ተገልጋዮቻችን፣ የደብረ ብርሃንና አካባቢው ማህበረሰብ እና ሠራተኞቻችን እንኳን ደስ ያላችሁ እያልን የዘወትር አጋራችን ኪዩር ብላይንድነስ ፕሮጀክት እና አገልግሎቱን ለማስጀመር ከፍተኛ አስዋጽኦ ያደረጋችሁ የሆስፒታላችን አመራሮችና የዓይን ህክምና ክፍል ባለሙያዎቻችን ላቅ ያለ ምሥጋና ይገባችኋል።

የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
ነሀሴ 2018 ዓ.ም

የደብረብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፋርማሲ ክፍል በ2018 በጀት ዓመት በተመረጡ የአገልግሎት አሰጣጥና የጥራት  መለኪያዎች እቅድ አፈጻጸም አማራ ክልል ከሚገኙ ሆስፒታሎች ተወዳድ...
12/08/2026

የደብረብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፋርማሲ ክፍል በ2018 በጀት ዓመት በተመረጡ የአገልግሎት አሰጣጥና የጥራት መለኪያዎች እቅድ አፈጻጸም አማራ ክልል ከሚገኙ ሆስፒታሎች ተወዳድሮ 3ኛ ደረጃ በመውጣት የእውቅናና የምስክር ወረቀት ተበርክቶለታል።

09/05/2026
አስደሳች ዜና ለአካባቢው ነዋሪዎች!የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከአሜሪካው ኪውር ብላይንድነስ (Cure Blindness) ጋር በመተባበር ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 7/2018 ዓ....
08/05/2026

አስደሳች ዜና ለአካባቢው ነዋሪዎች!

የደብረ ብርሃን አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከአሜሪካው ኪውር ብላይንድነስ (Cure Blindness) ጋር በመተባበር ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 7/2018 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ነፃ የዓይን ቀዶ ህክምና ዘመቻ አዘጋጅቷል።

የሚሰጡ የህክምና አገልግሎቶች፦

🌾የዓይን ሞራ ግርዶሽ መግፈፍ

🌾የዓይን ቆብ ቅንደላ (Trichiasis)

🌾እና ሌሎች ተያያዥ የዓይን ቀዶ ህክምናዎች።

በመሆኑም በሰሜን ሸዋ ዞን እና በደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ጤና መምሪያ ስር በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎች የቅድመ ልየታ (Screening) መርሃ ግብር ወጥቷል።

ይህ ችግር ያለባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች በወጣው ፕሮግራም መሰረት ተገኝተው የነፃ ህክምናው ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣ መረጃውን ለሚመለከታቸው ወገኖች በማድረስ ሁላችሁም የበኩላችሁን እንድትወጡ ሆስፒታሉ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ጨዋታው  ለቀጣይ ሳምንት የተላለፈ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።
23/04/2026

ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ጨዋታው ለቀጣይ ሳምንት የተላለፈ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።

Address

Debre Birhan

Telephone

+251116811333

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Debre Birhan Comprehensive Specialized Hospital:

Shortcuts

Share