01/01/2024
የጠባሴ ክፍለ ከተማ አስተዳደር አዲስ አበባ የሚኖሩ ተወላጆችን በማስተባበር ግምቱ 124,900 ብር በላይ የሚገመት የበዓል መዋያ ድጋፍ አደረገ።
በጠባሴ ክፍለ ከተማ በዝቅተኛ የንሮ ደረጃ ለሚገኙ 70 ለሚሆኑ ወገኖቻችን ግምቱ ከ124,900 ብር የሚገመት ለምግብነት የሚውል የአይነት ድጋፍ ተደርጓል።
በድጋፉ ወቅት የጠባሴ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መርሻ ማሞ የድጋፉ አስተባባሪ አቶ ውብሸት መንግስቴ የጎል ኢትዮጵያ አስተባባሪዎች እንዲሁም የክፍለ ለተማ እና የቀበሌ አመራሮች ተገኝተውበታል።
ድጋፉን ከተለያዩ መልካም አሳቢ ወገኖች ማሰባሰብ እንደቻሉ የገለጹት አቶ ውብሸት መንግስቴ ድጋፉ በቂ ነው ባይባልም በዓሉን ምክንያት በማድረግ ወገኖቻችንን ለማሰብ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
ስለተደረገው ድጋፍ ልባዊ ምስጋናቸውን ያቀረቡት የጠባሴ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መርሻ ማሞ ድጋፉ ዝቅተኛ የንሮ ደረጃ ያላቸውን ወገኖች ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ ከመንፈስ እርካታ ባሻገር ወንድማማችነትን እና እህትማማችነትን የሚያጎለብት አንድነትን የሚያጠናክር ድጋፍ እንደሆነ ገልጸዋል።