በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት

በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ዘላቂ ሰላምና ልማትን በማስፈን ሁለንተናዊ ብልፅግናን እናረጋግጣለን!

" የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን እንግታ " በሚል መሪ ቃል የሰሜን ሸዋ  ዞንና የባሶና ወረና ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ፅ/ቤት ዓመታዊ የአካባቢ ጥበቃ በዓልን በጋራ አከበሩበዓለም ለ55ኛ፣ በኢ...
05/06/2026

" የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን እንግታ " በሚል መሪ ቃል የሰሜን ሸዋ ዞንና የባሶና ወረና ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ፅ/ቤት ዓመታዊ የአካባቢ ጥበቃ በዓልን በጋራ አከበሩ

በዓለም ለ55ኛ፣ በኢትዮጵያ ለ33ኛ ፣ በክልል ደረጃ ለ29ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአካባቢ ጥበቃ ቀንን የሰሜን ሸዋ ዞንና የባሶና ወራና ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ፅ/ቤት በዛሬው ዕለት በጋራ አከበሩ።

በክብረ በዓሉ ላይ የሰሜን ሸዋ ዞንና የባሶና ወራና ወረዳ አመራሮች፣ የቡድን መሪዎች እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

በበዓሉ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙ የባሶና ወራና ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘሪሁን ኃይለጊዮርጊስ እንዳሉት የሰው ልጅ ለተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ የሚሰጠው ተኩረት በማነሱና የህዝብ ቁጥር በመጨመሩ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የገጠመንን ችግር ልናስተካክል ይገባል ያሉ ሲሆን ለተፈጥሮ ምቹ ነገርን ስንፈጥር ህይወት ላለው ፍጥረት ሁሉ ምቹ ነገር እናስገኛለን ብለዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞንን በመወከል የተገኙት የዞኑ አደረጃጀት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ሽፈራ ግርማ በበዓሉ የመክፈቻ ንግግራቸው እንዳሉትም በዓሉ ሀገራዊ ምርጫውን በሠላም ባጠናቀቅንበት ማግስት የተከበረ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል ያሉ ሲሆን፤ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በአረንጓዴ ልማት አሻራ ተግባር ላይ ያለንን ስራ ልናጠናክር ይገባል፤ የአካባቢ ጥበቃ ስራ የአንድ ተቋም ስራ ብቻ አይደለም ሁላችንም ኃላፊነት አለብን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ከደብረብርሃን ዩንቨርስቲ በመምጣት በበዓሉ ላይ ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት ገብሬ ተፈራ (ዶ.ር) እንዳሉት 1972 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) የመጀመሪያው አለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ ስብሰባ በማካሔድ የአካባቢ ጥበቃ ስራ አለም አቀፍ አጀንዳ እንዲሆን መሠረት ተጥሏል፣ የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይም ከሰው ልጆች ጋር ቀጥታ የሚገናኝ ተገቢውን ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ነው ብለዋል።

ሌላኛው ጥናት አቅራቢ አለምነው ብርሃን (ዶ.ር) እንደገለፁትም ተፈጥሮ ሁሉን ነገር ታቀርብልናለች እኛ ግን የምንወስደው አላግባብ ነው፤ ስለሆነም ዘላቂ ልማት እናምጣ ሲባል ኢኮኖሚ ልማት፣ ማህበራዊ ልማትና የከባቢ ስነ ምህዳር ልማትን የሚያጠቃልል ስለሆነ ለአካባቢ ጥበቃ ስራ ሁሉም አካል በያገባኛልና ይመለከተኛል ስሜት ተግባሩን ሊደግፍ ይገባል ብለዋል።

በመጨረሻም የሰሜን ሸዋ ዞን አካባቢ ጥበቃ ፅ/ቤት የኃላፊው ተወካይ የሆኑት አቶ በሱፈቃድ ነበሩ ገድሌ እንዳሉት እንደ ሰሜን ሸዋ ዞን የአካባቢ ጥበቃ ስራውን ከአጋር አካላት ጋር ተባብረን እየሰራን ነው፤ በተለይ በካይ የሆኑ ማቴሪያል አጠቃቀም ላይ ህጎች እየተሻሻሉና መተግበር እየጀመሩ ነው ብለዋል። ተወካይ ኃላፊው ለፕሮግራሙ መሣካት ሚና የነበራቸውን አመስግነው የዕለቱ ፕሮግራምም ተጠናቋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የ11 ወር  አፈፃፀም ገመገመ ።ግምገማው አጠቃላይ ከመምሪያው ሰራተኞች ጋር ነው የተካሄደው ። የመምሪያ ኃላፊዋ ወ/ሮ የሮምነሽ ጋሻው...
05/06/2026

የሰሜን ሸዋ ዞን ሴቶች ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የ11 ወር አፈፃፀም ገመገመ ።

ግምገማው አጠቃላይ ከመምሪያው ሰራተኞች ጋር ነው የተካሄደው ።

የመምሪያ ኃላፊዋ ወ/ሮ የሮምነሽ ጋሻውጠና እንደገለፁት ተቋሙ በርካታ የህ/ሰብ ክፍሎችን አገ/ሎት የሚሰጥ ተቋም ስለሆነ የደንበኞቻችንን አካታችና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተሰሩ ተግባራት አበረታች መሆኑን አመላክተዋል
የተሻለ አፈፃፀሙን የበለጠ ማጎልበት እንደሚጠበቅባቸው ገልፀዋል።

በዚህ አመት ከ25 አሻጋሪ እቅዱ የወረዱ ግቦችን የታችኛው መዋቅር እንዲተገበር በማድረግ ርብርብ የተደረገበት አመት መሆኑን ገልፀው በቀሪ ቀናት በየቡድኑ በትኩረት ሊተገበሩ የሚገባቸውን ተግባራት በመለየት የበለጠ ለማሳካት መተግበር እንዳለባቸው አስቀምጠዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎችም ሀሳብና አስተያየት ሰጥተዋል።
በትኩረት መተግበር ያለባቸው ተግባራት የበጋ በጎ ፈቃድ አተገባበርን በመገምገም የክረምት በጎፈቃድ ስራ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን ማከናዎን
የመንግስት ሰራተኞች ህፃናት ማቆያ ከዞን እስከ ወረዳ ማስጀመር
የተቋማት አካታችነትና የስርአተፆታ አተገባበር Keveling tool ምዘና ማጠናቀቅ ግብረመልስ መስጠት
የተለዩ የኢንሸቲቭ ተግባራት ቢከናወኑም ቀሪ ስራዎችን ማጠናቀቅ የወጣቶችና የሴቶች የስራ እድል ፈጠራን ማጠናቀቅ የፋይናንስ አቅርቦት ማመቻቸት የብድር ቁጠባ አገ/ሎቱን ምቹ ማድረግ ጎጂልማዳዊ ድርጊትን በመከላከል
ነፃ ቀበሌና ወረዳ መፍጠር እንደሚገባ አሳስበዋል ።

የሴቶችና የወጣቶችን የሰላም ግንባታ በማጠናከር በየአካባቢው ለዘላቂ ሰላም አስተዋፅኦ እንዳደርጉ ተልእኮ መስጠት
የሴቶች የልማት ህብረት አደረጃጀትን ማጠናከር ሁለንተናዊ ተልእኮ እንዲፈፅሙ በማድረግ ሞዴሎችን መመዘን መፈረጂ
የተጀመሩ ሰው ተኮር ተግባራትን ማጠናቀቅ መሆኑን በትኩረት እንዲጠናቀቁ ኃላፊዋ ጠቁመው ዝርዝር ማጠቃለያ ሰጥተው ውይይቱ ተጠናቆአል።

ሰሜን ሸዋ ዞን በቱሪዝም ሀብቱ የታደለ ነው። ይሔ በምስሉ የሚታየው በመንዝጌራ ምድር ወረዳ የሚገኘው  የመንዝ ጓሳ የማህበረሰብ ጥብቅ ስፍራ ፀጋ ነው። ከመንግስት የትኩረት አቅጣጫ አንዱ የሆ...
05/06/2026

ሰሜን ሸዋ ዞን በቱሪዝም ሀብቱ የታደለ ነው።
ይሔ በምስሉ የሚታየው በመንዝጌራ ምድር ወረዳ የሚገኘው የመንዝ ጓሳ የማህበረሰብ ጥብቅ ስፍራ ፀጋ ነው።

ከመንግስት የትኩረት አቅጣጫ አንዱ የሆነው የቱሪዝም ዘርፉ አሁን ላይ መነቃቃትን እያሳየ የተደበቁ ፀጋዎች እየወጡ ነው። የመንዝ ጓሳ የማህበረሰብ ጥብቅ ስፍራም ቢሰራበት ትልቅ ፀጋ ነው።

“ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር በሰሜን ሸዋ ዞን ከ64 ሚሊዮን በላይ የሀገር በቀል ዝርያ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተዋል” - ግብርና መምሪያበሰሜን ሸዋ ዞን ለዘንድሮው የችግኝ ተከላ...
04/06/2026

“ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር በሰሜን ሸዋ ዞን ከ64 ሚሊዮን በላይ የሀገር በቀል ዝርያ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተዋል” - ግብርና መምሪያ

በሰሜን ሸዋ ዞን ለዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር ከ64 ሚሊዮን በላይ የሀገር በቀል ዝርያ ያላቸው ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የዞኑ ግብርና መምሪያ የተፈጥሮ ሀብት ልማት ቡድን መሪ አቶ ጌታነህ ተክለማርያም እንደገለጹት፤ ለዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የሚሆኑ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች በተገቢው ሁኔታ እየተከናወኑ ይገኛሉ። ለዚሁ መርሐ-ግብር ከ36 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት የተዘጋጀ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ የ16 ሺህ 903 ሄክታር መሬት ካርታ የማዘጋጀት ሥራ ተጠናቋል።

የደን ልማት ሥራውን ጥራት ለማረጋገጥና አካባቢውን መልሶ ለማልማት ትኩረት ከተሰጣቸው ችግኞች መካከል 64 ነጥብ 6 ሚሊዮኑ የሀገር በቀል ዛፎች ዝርያ መሆናቸውን አብራርተዋል።

የችግኞችን የጽድቀት ምጣኔ ከሚያሳድጉ ዋና ዋና ተግባራት መካከል የጉድጓድ ዝግጅት አንዱ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ጌታነህ፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ213 ሚሊዮን በላይ ለተከላ የሚሆኑ ጉድጓዶች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።አሚኮ

በግሼ ወረዳ የራቤል የንጹህ መጠጥ ውሃ ግንባታ 82 በመቶ ደረሰደብረ ብርሃን፦ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር የራቤል ከተማ ነዋሪዎች የረጅም ጊዜ ጥያ...
04/06/2026

በግሼ ወረዳ የራቤል የንጹህ መጠጥ ውሃ ግንባታ 82 በመቶ ደረሰ

ደብረ ብርሃን፦ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም (አሚኮ) የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር የራቤል ከተማ ነዋሪዎች የረጅም ጊዜ ጥያቄና የግሼ ወረዳ የመልካም አስተዳደር እክል ሆኖ ቆይቷል። ይህንን ችግር ይፈታል ተብሎ የታመነበት የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በ208 ሚሊዮን ብር በጀት በክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ እየተከናወነ ይገኛል።

የፕሮጀክቱን አፈጻጸም በተመለከተ የጠየቅናቸው የወረዳው ውሃና ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዘውዴ ገለታው፤ ግንባታው በመስከረም ወር መጨረሻ መጠናቀቅ የነበረበት ቢሆንም በአካባቢው በነበረ የጸጥታ ችግር ሊዘገይ መቻሉን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት ባለው አንጻራዊ ሰላም ግንባታው በጥሩ ሁኔታ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ አፈጻጸሙም 82.5 በመቶ ደርሷል።

ፕሮጀክቱ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ፣ የታንከርና የቢሮ ግንባታ፣ የቧንቧ መስመር ዝርጋታ እንዲሁም ሙሉ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችን ያጠቃልላል። ግንባታው ሲጠናቀቅ የከተማዋን የውሃ ችግር ሙሉ በሙሉ ከመፍታቱም በላይ የውሃ ሽፋኑን ከ90 በመቶ በላይ እንደሚያደርሰው አቶ ዘውዴ አክለዋል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ክፍሌ አበራ በበኩላቸው፣ ፕሮጀክቱ እስከ ሰኔ መጨረሻ ተጠናቆ አገልግሎት እንዲጀምር የክልሉ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ፣ የወረዳው አስተዳደርና ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።(አሚኮ)

04/06/2026
በዞኑ የሚደረገው የግብአት ስርጭት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።በሰሜን ሸዋ ዞን ለ2018/19 የመኸር ምርት እድገት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ግብአቶች ወደ አርሶአደሩ መሰራጨታቸው እንደቀጠለ ነው...
04/06/2026

በዞኑ የሚደረገው የግብአት ስርጭት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

በሰሜን ሸዋ ዞን ለ2018/19 የመኸር ምርት እድገት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ግብአቶች ወደ አርሶአደሩ መሰራጨታቸው እንደቀጠለ ነው ።

ተግባሩን የዞኑ ግብርና መምሪያና ህብረት ስራ ማህበራት ፅ/ቤት ሃላፊዎች በበላይነት እያስተባበሩት ሲሆን በዛሬው እለት የተቋማቱ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የወደራ ዩኒየን አመራሮች በተገኙበት ለሃገረማርያም ወረዳ ዘጠኝ መኪናዎች ሽኝት ተደርጎላቸዋል።

ያለ ግብርና የለም ልዕልና!

በስፋት እናመርታለን የሃገራችንን ልዕልና እናረጋግጣለን!

በሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ የደም ልገሳ መርኃ ግብር አካሄደ ::የቀወት ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ከደብረብረሀን ደምባንክ ጋር በመተባበር የደም ልገሳ ንቅናቄ መርሀግብር አካሄደ ።በመርኃ ግብሩ የ...
04/06/2026

በሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ የደም ልገሳ መርኃ ግብር አካሄደ ::

የቀወት ወረዳ ጤና ፅ/ቤት ከደብረብረሀን ደምባንክ ጋር በመተባበር የደም ልገሳ ንቅናቄ መርሀግብር አካሄደ ።

በመርኃ ግብሩ የወረዳው አመራሮች ፣የሸዋሮቢት ሆስፒታል ሰራተኞች ፣ወጣቶች ፣ የመንግስት ሰራተኞች እና ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች የተሳተፉ ሲሆን በልገሳውም 75 ዩኒት ደም ማሰባሰብ መቻሉ ተገልጿል ።

በሚተካ ደም የማይተካን የሰው ልጅ ህይወት መታደግ የህሊና ሰላምን የሚሰጥ በጎ ተግባር ሲሆን በየጊዜው ለቀና ትብብራችሁ ከልብ እያመሰገን በቀጣይም ይህ ተግባር ባህል በማድረግ ድጋፋችሁ አይለዬን በማለት ሀሳባቸውን የገለፁት የቀወት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አድስ ሽፈራ ናቸው።

በሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ማማ ምድር ወረዳ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት የበጀት አመቱን እቅድ በስኬታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጠ።​የ...
03/06/2026

በሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ማማ ምድር ወረዳ የሰላም፣ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት የበጀት አመቱን እቅድ በስኬታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባ አቅጣጫ ተሰጠ።

​የሰሜን ሸዋ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ተማለደ በላይሁን እና የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ መርሻ ሀይሉ ከወረዳው ጠቅላላ አመራር ጋር በጋራ የውይይት መድረክ አካሂደዋል።

​በመድረኩ የተጀመሩ የልማትና የህዝብ ተጠቃሚነት ስራዎችን ዳር ለማድረስ የሁሉም ዘርፍ አመራር የተቀናጀ ርብርብ ይጠይቃል። በተለይም የአካባቢውን ሰላምና ጸጥታ በዘላቂነት በማረጋገጥ፣ ህዝባዊ አገልግሎቶችን በብቃት በመስጠት እና መልካም አስተዳደርን በማስፈን የተያዘውን የበጀት ዓመት እቅድ በስኬት ማጠናቀቅ እንደሚገባ አስተባባሪ አመራሮች አሳስበዋል።

​የወረዳው አመራሮችም በበኩላቸው የተሰጡ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ የተጀመሩ የልማት ስራዎችን በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅና የህዝቡን ጥያቄዎች ለመመለስ በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

03/06/2026

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ እንኳን ደስ አለን - የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ሆኖ በመጠናቀቁ የተሰማውን ደስታ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ገልጿል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የፀጥታ ኃይል አካላት እንዲሁም ሕዝቡ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሙሉ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ለተወጡት ሀገራዊ ኃላፊነት እና ላሳዩት ፅናትም ምክር ቤቱ ያለውን ምስጋና እና አድናቆት ገልጿል።

ምክር ቤቱ በመግለጫው፣ “ልዩነቶቻችንን እና ችግሮቻችንን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመፈታት በምርጫው የታየውን ሰላም በማስቀጠል የበኩላችንን ሚና እንወጣ፤ ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም በጋራ እንቁም” ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

Address

Debre Birhan Shewa
DEBERBRHAN

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በአማራ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share