ደብረ ማርቆስ ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ

ደብረ ማርቆስ ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ይህ የደ/ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የከተማና መሠረተ ልማት ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ነው።

የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነዉ! በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው አዲሱ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በቀንና...
14/03/2026

የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነዉ!

በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው አዲሱ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በቀንና በሌሊት ፈረቃ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

ፕሮጀክቱ በ153 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን ግንባታውን በሚመጣው ሚያዝያ ወር ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው።

ፕሮጀክቱ የህዝቡን የቆየ ጥያቄ ከመመለሱ ባለፈ፣ ለአካባቢው ከፍተኛ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ይኖረዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እያከናወናቸው ካሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው ይህ ማረፊያ፣ የከተማዋን የንግድና የቱሪዝም እንቅስቃሴ ያነቃቃል ተብሎ ይጠበቃል።

የክልልና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በግንባታ ላይ ያሉ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ።በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የክልልና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በከተማዋ ው...
11/03/2026

የክልልና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በግንባታ ላይ ያሉ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ።

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የክልልና የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በከተማዋ ውስጥ በግንባታ ላይ የሚገኙ ልዩ ልዩ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን የመስክ ምልከታ አደረጉ።

ጉብኝቱ በዋናነት የፕሮጀክቶቹን አፈጻጸም ለመገምገም እና በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ መጠናቀቃቸውን ለማረጋገጥ ያለመ ስለመሆኑ ተገልጿል።
​ተግዳሮቶችን መለየት፦ በግንባታ ሂደቱ ላይ እያጋጠሙ ያሉ የግብዓትና የቴክኒክ እንቅፋቶች በውይይት ተለይተው፣ አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጣቸው አቅጣጫ ተቀምጧል።

​በጉብኝቱ ወቅት ከፍተኛ አመራሮቹ እንደገለጹት፣ እነዚህ መሠረተ ልማቶች የከተማዋን የንግድና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከማሳለጥ ባለፈ ለነዋሪዎች ምቹ የሆነ አካባቢን የመፍጠር ግብ አላቸው። "ልማቱ የሕዝብ ነው፤ በመሆኑም በተቀመጠው ጥራትና ፍጥነት ተጠናቆ ለነዋሪው አገልግሎት መስጠት አለበት" ሲሉ አሳስበዋል።

​በመጨረሻም፣ የፕሮጀክቶቹ ተቋራጮችና ባለሙያዎች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡና የክትትል ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ የመስክ ምልከታው ተጠናቋል።

በመስክ ምልከታው የአማራ ክልል ምክር ቤት የግብርና አካባቢ ጥበቃና ውሃ ሃብት ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ከፋለ ሙላቴ፣ የአማራ ክልል ገጠር መንገድ ኮንስትራክሽን ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አስራቴ አለኸኝ፣የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ፣የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኀላፊ አቶ መልካሙ ሽባባው እና ሌሎች አመራሮች ተሳትፈዋል።
​ ጉብኝት የተደረገባቸው ፕሮጀክቶች፦የሞሰብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ግንባታ ህንፃ፣የአማራ ልማት ማህበር ሁለገብ ህንፃ፣በፌደራል መንግስት በጀት እየተገነባ ያለው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ከሀዲስ አለማየሁ አደባባይ ዩኒቨርሲቲው መስመር እየተገነባ ያለው የመንገድ ዳር ልማት ፕሮጀክት ይገኙበታል።

25/02/2026

‼️
ይህ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ የክቡር Teshome Walle Gessesse ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ነው። ገጹን Like & Follow በማድረግ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃዎችን ያግኙ።
በዚህ ሊንክ ይወዳጁ 👇
https://www.facebook.com/share/17sDiXAHTW/?mibextid=wwXIfr

ማህበረሰቡ የኮሪደር ልማቱን ጥቅም በመገንዘብ እገዛ እያደረገ ነው።በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የኮሪደር ልማት ስራን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቅ ስራ መጀመሩን የደብረ...
21/02/2026

ማህበረሰቡ የኮሪደር ልማቱን ጥቅም በመገንዘብ እገዛ እያደረገ ነው።

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የ2018 በጀት ዓመት የኮሪደር ልማት ስራን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቅ ስራ መጀመሩን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳድር ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ገለፀ።

የመምሪያው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አስምሮም ሞስነህ እንደገለፁት በበጀት አመቱ 2.5ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ ለመስራት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

እየተሰራ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቱ የእግረኛ እና የብስክሌት መንገድ፣ የአረንጓዴ ቦታዎች እና የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካተተ ነው ብለዋል።

የኮሪደር ልማቱን ባጠረ ጊዜ ለመጨረስ በፍጥነት እየተሰራ ስለመሆኑም ገልፀዋል።

በበጀት ዓመቱ ከ472 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ በጀት የተለያዩ የመሰረተ ልማት ስራዎች እየተገነቡ መሆኑን አቶ አስምሮም ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ ከተሞችን ውብ፣ ጽዱ እና ለነዋሪዎች ምቾትን ከመፍጠር ባሻገር ኢኮኖሚውን በማነቃቃት ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር የላቀ አበርክቶ አለው ሲሉ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳድር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ ገልፀዋል።

በልማቱ የከተማዋ ማህብረተሰብ እያደረገ ላለው አገዛ ምስጋናቸውን ያቀረቡት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው በቀጣይም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ለልማቱ አጋዥነቱን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።

መልካም ዜናየኢትዮጵያ አየር መንገድ የደብረ ማርቆስን ጨምሮ አዳዲስ መዳረሻዎችን በሚያዚያ ወር ሥራ እንደሚያስጀምር አስታወቀ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው ሚያዝያ ወር ሦስት አዳዲስ የሀ...
18/02/2026

መልካም ዜና

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደብረ ማርቆስን ጨምሮ አዳዲስ መዳረሻዎችን በሚያዚያ ወር ሥራ እንደሚያስጀምር አስታወቀ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው ሚያዝያ ወር ሦስት አዳዲስ የሀገር ውስጥ አየር ማረፍያዎችን በማስመረቅ በረራ ለመጀመር ማቀዱን አሳውቋል።

እነዚህ አዳዲስ መዳረሻዎች ደብረ ማርቆስ፣ ነገሌ ቦረና እና ጎሬ መቱ ናቸው።

Ethiopian Airlines

በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተገነባ ያለው አዲሱ ጠቅላላ ሆስፒታል አሁናዊ ገጽታ
16/02/2026

በደብረ ማርቆስ ከተማ እየተገነባ ያለው አዲሱ ጠቅላላ ሆስፒታል አሁናዊ ገጽታ

15/02/2026
የደብረ ማርቆስ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራዎች አጀማመር!!
13/02/2026

የደብረ ማርቆስ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራዎች አጀማመር!!

Address

Debre Markos
Debra Markos

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ደብረ ማርቆስ ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share