ደባርቅ መሰናዶና ፪ኛ ደረጃ ት/ቤት ልቃዊ የመረጃ መስኮት

  • Home
  • Ethiopia
  • Debark'
  • ደባርቅ መሰናዶና ፪ኛ ደረጃ ት/ቤት ልቃዊ የመረጃ መስኮት

ደባርቅ መሰናዶና ፪ኛ ደረጃ ት/ቤት ልቃዊ የመረጃ መስኮት Debark pre and 2ndary school
(1)

የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅበት ካሪክለም ይፋ ሆኗልየፈተና ዝግጅቱ:1. ከ9ኛ ክፍል በነባሩ እና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተመሳሳይ ይዘቶች፣ 2. ከ10 - 12ኛ...
21/10/2025

የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚዘጋጅበት ካሪክለም ይፋ ሆኗል

የፈተና ዝግጅቱ:
1. ከ9ኛ ክፍል በነባሩ እና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ተመሳሳይ ይዘቶች፣

2. ከ10 - 12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል።

ለተማሪዎቻችን
19/10/2025

ለተማሪዎቻችን

ማስታወቂያ:-የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብን ስለማሳዎቅ*********************************************ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች...
07/10/2025

ማስታወቂያ:-የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብን ስለማሳዎቅ
*********************************************

ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የ Remedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን እናሳውቃለን።

1. በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33% ከመቶ እና ከዚያ የተቆረጠ መሆኑን።

2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ።

ትምህርት ሚኒስቴር ።

22/09/2025

በመምህርነትህ ክብር እና ኩራት የሚሰማህ ልፋትህን በአደባባይ የሚገልጥ ተማሪ ሲገኝ ነው

ተማሪ አብርሀም ገ/ሂወት አካል ጉዳትን እና ኢኮኖሚን ታግሎ ያሸነፈ ብርቱ ተማሪ ትምህርት ቤቱ በአንተ ኮርቷል።

ነገ ዩኒቨርስቲ ሲገባ ብዙ ነገር ያስፈልገዋልና ተማሪ አብርሀምን ለማገዝ የምትፈልጉ

። 0908008585
ኢንባ 1000506147698 abriham g/hiwot g/egziabhair

#ማስታወሻ
👉ሊማሊሞ ቻሪቲ
👉ደባርቅ ዩኒቨርስቲ
👉ሰው መሆን ክብር የህፃናትና አረጋውያን መረዳጃ ማህበር

ክበሩልን አብራችሁ እንደምትዘልቁ ትት ቤቱ ባለ ሙሉ ተስፋ ነው።

ካለፉት አመታት በትምህርት ቤት እና በዞን ደረጃ ከነበሩት አማካኝ ውጤት የተሻለ ውጤት በትምህርት ቤታችን ሲመዘገብ 1ኛ ተማሪ አብርሀም ገ/ሂወት 514 soc 2ኛ ተማሪ አቤል እያዩ 504 n...
22/09/2025

ካለፉት አመታት በትምህርት ቤት እና በዞን ደረጃ ከነበሩት አማካኝ ውጤት የተሻለ ውጤት በትምህርት ቤታችን ሲመዘገብ
1ኛ ተማሪ አብርሀም ገ/ሂወት 514 soc
2ኛ ተማሪ አቤል እያዩ 504 nat
3ኛ ተማሪ ሙሉቀን በሪሁን 486 nat
ሆኖ ያለፈ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን የዩኒቨርስቲ #ምርጫ ማስተካከል የምትፈልጉ በአካል ትት ቤት በመገኘት እንድታስተካክሉ።

አኩርታችሁልንና ክበሩልን

ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች
22/09/2025

ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች

የ2017ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ይፋ ሆኗል በትምህርት ቤታችንከተፈጥሮ ሳይንስና አቤል እያዩ 504ከማህበራዊ ሳይንስ አብርሀም ገ/ሂዎት 514 እስከ አሁን የተመዘገበ ውጤት ነው።ውጤት ለ...
15/09/2025

የ2017ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ይፋ ሆኗል በትምህርት ቤታችን

ከተፈጥሮ ሳይንስና አቤል እያዩ 504
ከማህበራዊ ሳይንስ አብርሀም ገ/ሂዎት 514 እስከ አሁን የተመዘገበ ውጤት ነው።

ውጤት ለማየት www.neaea.gov.et

የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎች ይፋ ሆኑ፡፡የ2017 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈተኑ ተፈታኞች በሚከ...
15/09/2025

የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎች ይፋ ሆኑ፡፡

የ2017 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈተኑ ተፈታኞች በሚከተሉት አድራሻዎች ዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ፡፡

ዌብ ሳይትና ቴሌግራም አድራሻ የሚጠቀሙ ተፈታኞች ጊዜያዊ ሰርቲፊኬታቸውን ወዲያውኑ አውርደው (download አድርገው) መውሰድና መጠቀም ይችላሉ፡፡

አድራሻዎቹ፡
1. ዌብ ሳይት፡ https://result.eaes.et
2. ቴሌገራም፡ https://t.me/EAESbot
3. አጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡ 6284

(የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት)

06/09/2025


MoE

ትምህርት ሚኒስቴር ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተማሪዎች ሞባይል ስልክ፣ ታብሌት እና መሰል ኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን ይዘው ወደ ትምህርት ቤት እንዳይሔዱ ከልክሏል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን አጀማመር ላይ ከክልል እና ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ጋር የበይነ-መረብ ምክክር አድርጓል።

የ2018 ትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ ሰኞ መስከረም 05/2018 ዓ.ም እንደሚጀመር ተገልጿል።

ተማሪዎች ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ታብሌት እና መሰል ኤሌክትሮኒክስ ቁሶችን ይዘው በትምህርት ቤት መገኘት ክልክል መሆኑን የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ገልፀዋል።

ባለፈው ዓመት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎችን ጨምሮ ሁሉም ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት እና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ ወላጆች፣ መምህራን እና የዘርፉ ባለድርሻዎች የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።

27/07/2025

የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ - አዋጅ ቁጥር 1368/2017
=================

➡የትምህርት አዋጁ 16 ክፍሎች 97 አንቀፆችና 420 ንኡሳን አንቀፆች ያሉት አዋጅ ነዉ፡፡
✍️የተፈፃሚነት ወሰን
1. ይህ አዋጅ አጠቃላይ ትምህርትን በተመለከተ በሁሉም #የፌዴራልና #የክልል የትምህርት ተቋማት፣ እንደዚሁም በትምህርት አቅርቦትና አቀባበል ረገድ በሀገሪቱ በተሰማሩ መንግስታዊ እንዲሁም መንግስታዊ ያልሆኑ አካላትና በውጭ ሀገር በተቋቋሙ የኢትዮጵያ ማኀበረሰብ ትምህርት ተቋማት ላይ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
2. በኢትዮጵያ ሠራዊት፣ አስተዳደር፣ በሌሎች መንግሥታዊ ተቋማት በሚካሄዱ ትምህርት ቤቶች ላይ ሁሉ ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
📝የአጠቃላይ ትምህርት መርሆች
==================
1. ትምህርትን በእኩልነትና በፍትሐዊነት ተደራሽ ማድረግ፣
2. የትምህርት ጥራት እና አግባብነት ማረጋገጥ፣
3. የአጠቃላይ ትምህርት የትምህርት አመራርና አስተዳደር ባልተማከለና በዴሞክራሲያዊ ውሳኔ አሰጣጥና በተጠያቂነት መርሕ ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ማድረግ፣
4. በትምህርት ተቋማት ከሚፈጸሙ ማናቸውም ዓይነት አድሏዊ አሠራሮች መጠበቅ፣
5. የተማሪዎችን በነጻነት የማሰብ፣ የመጠየቅና የመመራመር ጥረት ማበረታታት፣ እንደዚሁም ለቀጣይ ሁለንተናዊ ዕድገታቸው የሚያግዙ ክህሎቶችን፣ የሥነ ምግባር ደንቦችንና ችሎታዎችን እንዲያዳብሩ ማድረግ፣
6. በተማሪዎች መካከል ሰላምን መፍጠር፣ የአንድነት፣ የአብሮ መሥራትና የመቻቻል መንፈስን ማዳበር የሚያስችል አቅጣጫ ማስቀመጥ፣ ማኀበራዊና ብሔረሰባዊ ልዩነቶችን በሚገባ በመገንዘብ ከዚህ የሚነሱ አላስፈላጊ ችግሮችን ሊያስወግድ የሚችል የትምህርት አቅርቦት እንዲኖር ማድረግ፣
7. መልካም አስተዳደርን፣ ማኅበራዊ ተሳትፎ እና አብሮነትን መሠረት ባደረገ መልኩ ወላጆች፣ አሳዳሪዎች፣ የማኅበረሰብ ክፍሎች፣ የግሉ ዘርፍና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት የየበኩላቸውን አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ የሚችሉበት የትምህርት ልማትና አመራር ማመቻቸት፣
8. የትምህርት አቅርቦት ሀብትንና ቁሳቁስ አጠቃቀምን ወጭ ቆጣቢ ማድረግና ለሁሉም ፍትሐዊ በሆነ መልኩ የሚዳረስበትን ሁኔታ መፍጠር፣
9. ሀገራዊ የትምህርት ሥርዓትን ከሃይማኖት ትምህርትና ከፓርቲ ፖለቲካ ወገንተኝነት መለየት፣
10. ለሃገር በቀል እውቀቶች ልዩ ትኩረት መስጠት፤
✍️ነጻና የግዴታ ትምህርትን የሚመለከቱ አጠቃላይ ድንጋጌዎች
========+=====+==
1. ዕድሜው ለትምህርት የደረሰ ማንኛውም ሕጻን በመንግሥት ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ፤ የአንደኛ ደረጃና የመካከለኛ ደረጃ ትምህርትን በነጻ የመማር መብትና ትምህርቱንም የመከታተል ግዴታ አለበት፡፡
2. ማንኛውም ዜጋ በመንግሥት ትምህርት ቤቶች የሁለተኛ ደረጃ ትምህርትን በነጻ የመማር መብት አለው፡፡
3. አንድ ሕጻን በሚኖርበት አካባቢ ባሉ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ፤ የአንደኛ ደረጃና የመካከለኛ ደረጃ እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማግኘቱን ማረጋገጥ ነው፡፡
4. አንድ ተማሪ ከሚማርበት ትምህርት ቤት በተለያዩ ምከንያቶች የመኖሪያ አድራሻውን ሲቀይር ወደሌላ ትምህርት ቤት ተዛውሮ የመማር መብት አለው፡፡
➤ከክፍል ወደ ክፍል ዝውውር
እና ሌሎች የአዋጁ ዝርዝር ሰነድ
የአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ _አዋጅ ቁጥር ___ 1368/2017 የወጣውን መመልከት ይቻላል።

ለመላው የሊማሊሞ አድራጎት ማህበር አባላትና አመታዊ መዋጮ የከፈላችሁ ገንዘባችሁ ስራውን አንድ እርምጃ ከፍ እያደረገ ይገኛል።በርቱ
25/07/2025

ለመላው የሊማሊሞ አድራጎት ማህበር አባላትና አመታዊ መዋጮ የከፈላችሁ ገንዘባችሁ ስራውን አንድ እርምጃ ከፍ እያደረገ ይገኛል።

በርቱ

የ2017ዓ.ም የትምህርት ዘመን  #ተቋጭቷልበትምህርት ዘመኑ👉ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በክፍልና ከአጠቃላይ 👉ጥሩ አፈፃፀም የነበራቸው ምስጉን መምህራን ፤ ዲፖርትመንት ፤ የክፍል ሀላ...
10/07/2025

የ2017ዓ.ም የትምህርት ዘመን #ተቋጭቷል

በትምህርት ዘመኑ
👉ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በክፍልና ከአጠቃላይ
👉ጥሩ አፈፃፀም የነበራቸው ምስጉን መምህራን ፤ ዲፖርትመንት ፤ የክፍል ሀላፊ መምህር ፤ ፈረቃ አስተባባሪ እና አደረጃጀቶች
👉ጥሩ የስራ አፈፃፀም ያለውን የአስተዳደር ሰራተኛ በማበረታቻ ያጀበ ሲሆን ከየትኛውም ግዜ በበለጠ ከክፍል ክፍል የተዘዋወረ ተማሪ ብዛት ከፍተኛ ሆኖ ተመዝግቧል።

መልካም የእረፍት ግዜ ውድ የትምህርት ቤታችን መምህራንና ተማሪዎች።

Address

Debark'

Telephone

0581170014

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ደባርቅ መሰናዶና ፪ኛ ደረጃ ት/ቤት ልቃዊ የመረጃ መስኮት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ደባርቅ መሰናዶና ፪ኛ ደረጃ ት/ቤት ልቃዊ የመረጃ መስኮት:

Share