30/04/2026
በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር የሳይንስና የቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች ወድድርና ኤግዚብሽን ተካሄደ ።
ሚያዝያ 21/2018 ዓ.ም (ቡታጅራ)
በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዩኒትና ከከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ዩኒት ጋር በመተባበር በትምህርት ቤቶች ፣ በኢንተርፕራይዞች እና በግል የሳይንስና የቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች ኤግዚብሽንና ውድድር ተካሂዷል።
በውድድሩ ላይ የተገኙት የ ከተማ አስተዳደሩ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ሃላፊ አቶ ፈቱ አሕመድ መንግስት ለሳይንስ ቴክኖሎጂና ለፈጠራ ስራዎች ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የት/ት ዩኒት ሃላፊ አቶ ሹራላ ጀማል በዛሬው ዕለት በተካሄደው የሳይንስ ቴክኖሎጂ የፈጠራ ስራዎች ውድድሩ ላይ የተለያዩ ማህበራዊ ችግሮችን ሊፈቱ የሚችሉ የፈጠራ ስራዎች ማየት መቻላቸውን ተናግረዋል።
የታዩት የፈጠራ ስራዎች ወደ ማህበረሰቡ ጋር የሚደርሱበት ሁኔታ መፍጠር እንደሚገባ አስገንዝበዋል። የከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ዛሬ በተካሄደው የፈጠራ ስራ ውድድር በርካታ አዳዲስ ችግር ፈቺ የሆኑ የፈጠራ ስራዎች መቅረባቸውን ተናግረዋል።
የፈጠራ ስራዎች ከውድድር አልፈው የፈጠራ ባለቤቶችን ተጠቃሚ እንዲያደርጉ እና ማህበረሰቡን ችግር መፍታት እንዲችሉ ያለባቸውን ችግሮች ለመቅረፍ በሁሉም መልኩ እገዛ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በዛሬው ዕለት የተሻለ ስራዎች ያቀረቡ አካላት በቀጣይ ለሚደረገው ዞናል ውድድር ጥሩ ውጤት ለማምጣት ጥረት ማድረግ አለባቸው ብለዋል።
በመጨረሻም የተሻለ ስራ ያቀረቡ አካላት የእውቅና የምስክር ወረቀትና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በውድድሩ ላይ የፅ/ቤት ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች፣ የት/ቤት ርዕሳነ መምህራን፣ ተማሪዎች ተገኝተዋል።
ዘገባው የእንሴኖ ከተማ አስተዳደር ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዩኒት ነው።