Central Ethiopia Industrial Parks Development Corporation

Central Ethiopia Industrial  Parks Development Corporation Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Central Ethiopia Industrial Parks Development Corporation, Central Ethiopia Region, Butajira town, next to Serana Meeting Hall, Butajira.

የክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በክልል የሚቋቋም ሲሆን በሁለተኛዉ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ በተቀመጠዉ አቅጣጫ መሠረት በአገራችን የኢንዱስትሪ ልማት እንዲፋጠንና የገጠር ኢንዱስትራላይዘሽን እንዲስፋፋ አስፈላጊና ወሳኝ መሣሪያ የሆኑትን ኢንዱስትሪ ፓርኮችን፣ የገጠር ትራንስፎርሜሽን ማዕከላትንና የምርት መሰብሰቢያ ማዕከላትን እና እንዲሁም በክልሉ በሚገኙ ከተሞች የአነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ማምረቻ ማዕከላትንና የሚያለማና የሚያስተዳድር፣ የግብርና ትራንስፎርሜሽንን የሚያፋጥን፣ ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግ፤ ግብርናን- ከኢንዱስትሪ ጋር የሚያስተሳስር አካል ነው፡፡

የ315 KVA የኃይል አቅርቦትና የማምረቻ ሼድ በኮርፖሬሽኑ ድጋፍ የተደረገለት World Manufacturing PlC ከብዙ እልህ አስጨራሽ ክትትል በኋላ ማሽኖቹ ተጓጉዘው ኮርፖሬሽኑ አልምቶ ...
21/05/2026

የ315 KVA የኃይል አቅርቦትና የማምረቻ ሼድ በኮርፖሬሽኑ ድጋፍ የተደረገለት World Manufacturing PlC ከብዙ እልህ አስጨራሽ ክትትል በኋላ ማሽኖቹ ተጓጉዘው ኮርፖሬሽኑ አልምቶ በሚያስተዳድረው የወልቂጤ ማምረቻ ኢንዱሰትሪ ማዕከል ደርሰዋል።
ማሽኖቹም ተገጣጥመው ዱቄት የማምረት ስራ ሲጀምሩ ሰፊ የስራ እድል ፣በአርሶአደሩና በፋብሪካው መካከል የግብዓት ትስስር እንደሚፈጥር ይጠበቃል
(ፎቶ ክሬዲት - ሙራድ ያሲን)

በከምባታ ዞን በተለያዩ አከባቢዎች ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነቡ  ማምረቻ ሼዶች ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ተመረቁ።(ቡታጅራ፦ ግንቦት 12/2018) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮ...
20/05/2026

በከምባታ ዞን በተለያዩ አከባቢዎች ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነቡ ማምረቻ ሼዶች ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ተመረቁ።

(ቡታጅራ፦ ግንቦት 12/2018) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በከምባታ ዞን በዱራሜ እና ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ያስገነባቸውን የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ማምረቻ ሼዶች ማስፋፊያ ፕሮጀክቶች በይፋ ተመርቀዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወ/ሚካኤል እንደገለጹት ክልሉን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ በቅንጅት እየተሰራ ነው።

ኢንዱስትሪ ማለት የስራ ዕድል ፈጠራ፣ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ፣የቴክኖሎጂ ሽግግር፣በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል የሚሰጥና ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር እንደሆነም ገልፀዋል።

ከዚህ ቀደም በግብርና ዘርፍ ብቻ ተንጠልጥሎ የነበረውን ኢኮኖሚ የለወጡ መንግስት ወደ ብዝሃ ዘርፍ በማሳደግ የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በማሳደግ ላይ ይገኛል ነው ያሉት።

በአሁኑ ወቅት ግብርናን ለማሸጋገር በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን በመግለጽ ኢንዱስትሪው በአከባቢ ባሉት ፀጋዎች እሴት ተጨምሮ ጥራት ያለውን ምርት ለህብረተሰቡ ከማቅረብ ረገድ ያለው ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።

በክልሉ የኢንዱስትሪ ዞኖች እንዲከለሉ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የገለፁት አቶ ስንታየሁ ባለሀብቶች በዘርፉ በመሰማራት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ አሳስበዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ናትናኤል ሚሊዮን በበኩላቸው ይህ ፕሮጀክት በክልሉ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለስራ እድል ፈጠራ እና ለአካባቢያዊ ኢኮኖሚ ማነቃቂያ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው ብለዋል።

የለውጡ መንግስት የኢንዱስትሪ ልማት ፖሊሲ ዋና ትኩረት ሀገራችንን ከፍጆታ ተኮር ኢኮኖሚ ወደ ምርት ተኮር ኢኮኖሚ መሸጋገር ነው ብለው በተለይም አግሮ ፕሮሰሲንግ፣ ጨርቃጨርቅ፣ ቆዳ፣ የግንባታ እቃዎች እና አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፎችን በማጠናከር የሀገር ውስጥ ምርትን ማሳደግ ነው።

ፕሮጀክቱ የአከባቢውን ግብአት በመጠቀም እና የገበያ ትስስር በመፍጠር የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድግ ነው ብለው በዱራሜ 4 እንዲሁም በሺንሽቾ 8 በአጠቃላይ 12 ኢንዱስሪ ሼዶችን ያካተተ ፕሮጀክት እንደሆነም ጠቁመዋል።

ፕሮጀክቱ የሃይል አቅርቦትን ጨምሮ ከ90 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ መሆኑን ጠቁመው ለተግባሩ ውጤታማነት አወንታዊ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አካላትን አመስግነዋል።

የከምባታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አረጋ እሸቱ በፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት ማሳያ ነው።

አካባቢው የተለያዩ ምርቶች በስፋት የሚመረት እንደመሆኑ መጠን ማህረሰቡ ለኢንዱስትሪ የሚውሉ ምርቶችን በስፋትና በጥራት በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በእለቱም አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተካሄደ ሲሆን የክልል፣ የዞን እና የከተማ አስተዳደሮች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

(ምንጭ- የማኢክ መኮቢ)

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በስሩ ለሚያስተዳድራቸው ለአምራች ኢንተርፕራይዞች የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄደ(ሚያዝያ 29/2018 ዓ.ም — ቡታጅ...
08/05/2026

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በስሩ ለሚያስተዳድራቸው ለአምራች ኢንተርፕራይዞች የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አካሄደ

(ሚያዝያ 29/2018 ዓ.ም — ቡታጅራ)- የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በስሩ ለሚያስተዳድራቸው ከክልሉ ከተለያዩ ማምረቻ ኢንዱሰትሪ ማዕከላት የተውጣጡ አምራች ኢንተርፕራይዞች፣ ለኮርፖሬሽኑ የማኔጅመንት አካላትና የዘርፉ ባለሞያዎች በሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከሚገኙት ከሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ እና ከይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ የልምድ ልውውጥና ምርጥ ተሞክሮ የመቅሰም ጉብኝት አካሂደዋል።

በጉብኝቱ ወቅት ተሳታፊዎቹ በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የአቮካዶ ዘይት፣ የቡና እና ሌሎች የሀገር ውስጥና የውጭ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ካምፓኒዎችን ጎብኝተዋል። በተለይም በምርት አመራረት ፣ በጥራት አስተዳደር፣ በፊትዮሽና የኋልዮሽ የእሴት ሰንሰለት ትስስር፣ በገበያ ትስስር እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ተግባራዊ ልምዶችን ወስደዋል።

በተመሳሳይ በሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ በነበረ ቆይታ በጨርቃ ጨርቅ ዘርፍ የተሰማሩ ካምፓኒዎችን በመጎብኘት በዘርፉ እየተተገበሩ ያሉ ዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎችን፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን እና ዘርፉ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል የመፍጠር አቅም እንዳለው ተመልክተዋል።

ተሳታፊ ኢንተርፕራይዞቹም ከጉብኝቱ ያገኙት ልምድ ወደ ሥራቸው በመመለስ ይበልጥ ተግባራዊ ለማድረግ እና በቁርጠኝነት ለመስራት ከፍተኛ ተነሳሽነት እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።
በመጨረሻም አምራች ኢንተርፕራይዞቹ ኮርፖሬሽኑ አቅማችውን ለመገንባት የማምረቻ ሼድ ከማቅረብ በዘለለ በርካታ መዋዕለ ነዋይ በማፍሰስ ውጤታማነትን ለመጨመር እና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ኮርፖሬሽኑ እያደረገ ያለው ጥረት ተጨባጭ ለውጥ እያመጣ መሆኑን ጠቁመው ይህ ጥረት እውቅና የሚሰጠውና እያደረገ ካለው ጥረት በተጨማሪ እንዲህ ዓይነት የልምድ ልውውጥ ፕሮግራሞች የአምራች ኢንተርፕራይዞችን አቅም የሚያጠናክር በመሆኑ በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል እንደሚገባ ጠይቀዋል።

ኮርፖሬሽኑም በበኩሉ በበጀት ዓመቱ በስሩ ለሚያስተዳድራቸው አምራች ኢንዱስትሪዎች እቅም እንዲያሳድጉ የተለያዩ ማሽነሪዎች ድጋፍ ማድረጉን ፣አማካሪ ድርጅቶችንም በመቅጠር በበርካታ ርዕሶች የተግባርና የንድፈ ሀሳብ ስልጠናዎችን መስጠቱን፣ የኢንዱሰትሪ ደህንነት መጠበቂያ መሳሪያዎች በድጋፍ ከማበርከቱ በዘለለ ከትልልቅ የሀገር ውስጥና የውጭ ኢንቨስትመንቶች ልምድ በመውሰድ አቅም እንዲገነባ እያደረገ ያለው ጥረት የዕቅዱ አካል መሆኑን በመግለፅ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

በመጨረሻም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ አንዋር ሳቢር ይህ ጉብኝት የተሳካ እንዲሆን የተባበሩትን የኢንዱሰትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን፣ የሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽንንና እንዲሁም በበጀት የደገፈውን GIZ- invest for jobs አመስግነዋል።

መረጃው፡- በቢዝነስ ዲቪሎፕመንትና ኦፕሬሽን ዳይሬክቶሬት የማርኬቲንግና ኮሙኒኬሽን ክፍል ነው

(ሚያዚያ 21,2018:ቡታጅራ) ዛሬ ደግሞ የሀላባ ማምረቻ ማዕከልን የአጥር፣ የጥገና እና እድሳት ስራዎችን መስራት ጀምረናል። የማምረቻ ማዕከላቶቻችን ለአምራቾች ምቹ እና ለስራ ተስማሚ የማድ...
29/04/2026

(ሚያዚያ 21,2018:ቡታጅራ)
ዛሬ ደግሞ የሀላባ ማምረቻ ማዕከልን የአጥር፣ የጥገና እና እድሳት ስራዎችን መስራት ጀምረናል።
የማምረቻ ማዕከላቶቻችን ለአምራቾች ምቹ እና ለስራ ተስማሚ የማድረጉን ሂደት አጠናክረን እየቀጠልን ነው።

ሚያዚያ 19,2018: ቡታጅራ በኮርፖሬሽኑ በበጀት ዓመቱ ለመስራት ካቀድናቸው ስራዎች መካከል አንዱ የሳጃ የማምረቻ ኢንዱሰትሪ ማዕከልን እድሳት እና ጥገና ማከናወን ነው። ከዚህ አንፃር ሳይቱ...
27/04/2026

ሚያዚያ 19,2018: ቡታጅራ
በኮርፖሬሽኑ በበጀት ዓመቱ ለመስራት ካቀድናቸው ስራዎች መካከል አንዱ የሳጃ የማምረቻ ኢንዱሰትሪ ማዕከልን እድሳት እና ጥገና ማከናወን ነው።
ከዚህ አንፃር ሳይቱ ለጎርፍ ተጋላጭ የነበረ በመሆኑ ይህንን በመገንዘብ የአጥር፣ የዕድሳት እና የውሃ ፍሳሽ ማስወገጃ መስመሮችን ጨምሮ ሌሎችን ተጓዳኝ ስራዎችን መስራት ጀምረናል።
ተቋራጩም ቅድመ ክፍያ እንኳን ሳይወስድ በፍጥነት ወደ ሳይት በመግባት ክረምቱ በአምራቾች ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ለወሰደው ቁርጠኝነት ኮርፖሬሽኑ ከልብ ያመሰግናል።

(ሚያዚያ 10,2018:ቡታጅራ)በሰርኩላር ኢኮኖሚ ላይ ያተኮረው ስልጠና ኮርፖሬሽኑ ባለማውና በሚያስተዳድራቸው  በወልቂጤ ከተማ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱሰትሪ ማዕከላት ውስጥ ለሚገኙ አምራች ኢንዱስ...
18/04/2026

(ሚያዚያ 10,2018:ቡታጅራ)በሰርኩላር ኢኮኖሚ ላይ ያተኮረው ስልጠና ኮርፖሬሽኑ ባለማውና በሚያስተዳድራቸው በወልቂጤ ከተማ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱሰትሪ ማዕከላት ውስጥ ለሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች ዛሬ መስጠት ተጀምሯል።

ስልጠናው በGIZ-Invest for Jobs ድጋፍ በSMART Career Solutions አማካሪ ድርጅት በኩል በወልቂጤ ከተማ እየተሰጠ ይገኛል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ምርቶችን መልሶ ጥቅም ላይ ማዋል (Recycling) በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተካሄደ(ቀን፡ ሚያዝያ 07 ቀን 2018 ዓ.ም:ቡታጅራ)የማዕከላዊ...
16/04/2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ምርቶችን መልሶ ጥቅም ላይ ማዋል (Recycling) በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት ተካሄደ
(ቀን፡ ሚያዝያ 07 ቀን 2018 ዓ.ም:ቡታጅራ)
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በክልሉ የሚገኙ ከተሞችን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግና የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ በአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል። በዚህም መሠረት በሆሳዕና እና በወልቂጤ ከተሞች የኢንዱስትሪ ምርቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል (Resource Recycling ) ዘርፍ የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞችን አቅም ለመገንባት የሚያስችል ከፍተኛ የሥራ አመራር ውይይት በዛሬው ዕለት በዋናው መሥሪያ ቤት ተካሂዷል።
የአማካሪ ድርጅቱ ጥናትና ግኝቶች
"ስማርት ካሪየር ሶሉሽንስ" (Smart Career Solutions) የተሰኘው አማካሪ ድርጅት በሆሳዕና እና ወልቂጤ ከተሞች በሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ላይ ያደረገውን የክፍተት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት አቅርቧል። ሪፖርቱ በዋናነት ኢንተርፕራይዞቹ በምርት ሂደት ውስጥ ተረፈ-ምርቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል ረገድ ያሉባቸውን የዕውቀት፣ የቴክኖሎጂ እና የሥርዓት ክፍተቶች በዝርዝር አመልክቷል።

በተጨማሪም በጥናቱ የተለዩትን ክፍተቶች መሠረት በማድረግ፣ ምርትን መልሶ ጥቅም ላይ የሚያውሉ (Recycling Enterprises) ኢንተርፕራይዞችን በቴክኖሎጂ ለማገዝ ስምምነት ላይ ተደርሷል። በዚህም መሠረት፦
ለኢንተርፕራይዞቹ የሚሰጡ የማሽነሪ ድጋፎችን ዓይነትና ጥራት የሚወስን ዝርዝር የዕቃ መግለጫ (Technical Specification) እንዲዘጋጅ አቅጣጫ ተቀምጧል።ድጋፍ የሚደረገው ኢንተርፕራይዞቹ ጥሬ ዕቃን በቁጠባ እንዲጠቀሙና የአካባቢ ብክለትን እንዲቀንሱ ታስቦ የሚከናወን መሆኑ ተገልጿል።

በመጨረሻም ኢንተርፕራይዞቹ የአካባቢ ጥበቃ መርሆዎችን ተከትለው እንዲያመርቱ፣ ቆሻሻን ወደ ሀብት እንዲቀይሩና የስራ ዕድል እንዲፈጥሩ አልፎም የሚሰጣቸውን ማሽነሪዎች በአግባቡ እንዲያንቀሳቅሱና የምርት ጥራታቸውን እንዲያሳድጉ ተከታታይ የሙያና የቴክኒክ ሥልጠና ከነገ ጀምሮ በሚሰጥበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። ሥልጠናው በንድፈ-ሐሳብ ብቻ ሳይወሰን በተግባር የተደገፈ እንዲሆንና ውጤታማነቱም በኮርፖሬሽኑ በኩል ክትትል እንደሚደረግበት ታውቋል።

በውይይቱ ወቅት የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተወካይ #እና የማኔጅመንት አካላት በሰጡት መመሪያ መሠረት፣ ይህ የድጋፍ መርሃ-ግብር የሆሳዕና እና የወልቂጤ ከተሞችን የኢንዱስትሪ እንቅስቃሴ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግርና የክብ ኢኮኖሚ (Circular Economy) ሥርዓትን በክልሉ ለማስፈን ትልቅ ሚና የሚጫወት ነው ሲሉ ሀሳባቸውን ሰጥተዋል።

ለተጨማሪ መረጃ፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን
የማርኬቲንግ እና ቢዝነስ ዲቨሎፕመንት ዳይሬክቶሬት

Address

Central Ethiopia Region, Butajira Town, Next To Serana Meeting Hall
Butajira
169

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Ethiopia Industrial Parks Development Corporation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Central Ethiopia Industrial Parks Development Corporation:

Share