07/09/2026
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በተገኙበት በምስራቅ ጉራጌ ዞን በምስራቅ መስቃን ወረዳ፣ በእንሴኖ ከተማ አስተዳደር እና በማረቆ ልዩ ወረዳ ሲካሄድ የቆየውን የሰላም እና ልማት ውይይቶች ግምገማ፣ቀጣይ አቅጣጫ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ነው
ቡታጅራ፣ ጳጉሜ 2/2018
መድረኩ በሁለቱ ህዝቦች መካከል ዘላቂ ሰላም በማረጋገጥ የወንድማማችነት እና የእህታማማችነት እሴቶች ይበልጥ እንዲጎለብት በማድረግ ረገድ የጎላ አበርክቶ እንዳለውም ተመላክቷል።
በመድረኩ የክልል፣የምስራቅ ጉራጌ ዞን፣የማረቆ ልዩ ወረዳ፣የሀገር ሸማግሌዎች ፣የሀይማኖት አባቶች እና ከየመዋቅሩ ጥሪ የተደረገላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል ሲል የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።