South West Ethiopian Peoples Regional State Trade & Investments Office

  • Home
  • Ethiopia
  • Bonga
  • South West Ethiopian Peoples Regional State Trade & Investments Office

South West Ethiopian Peoples Regional State Trade & Investments Office To deliver information concerning trade and investment of the region.

በተጠናቀቀው  በጀት ዓመት 3.8 ቢሊዮን  ዶላር  የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት  መሳብ መቻሉን የኢትዮጵያ  ኢንቨስትመንት  ኮምሽን ምክትል ኮምሽነር ዳገቶ ኩምቢ ገለፁ።የፌደራል ፣ የክልል እና...
01/09/2024

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 3.8 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መሳብ መቻሉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮምሽን ምክትል ኮምሽነር ዳገቶ ኩምቢ ገለፁ።

የፌደራል ፣ የክልል እና የከተማ አስተዳደሮች የኢንቨስትመንት አስፈፃሚዎች የጋራ ምክክር በሚዛን አማን ከተማ ሲካሄድ የነበረው መድረክ ተጠናቀቀ።

የኢፌዴሪ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ዳገቶ ኩምቢ እንደገለፁት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት እና የሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት እንዲነቃቃ መንግስት የፋይናሽያል ሪፎርም፣ የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጠና ፣ የማይክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እንዲሁም የውጭና የገቢ ሥራዎች ሪፎርም ተጠቃሾች መሆናቸውን ተናግረዋል ።

በሀገሪቱ 10 ሺህ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ላይ ከተሰማሩ 3.8 ቢሊዮን ዶላር መሳብ መቻሉን አቶ ዳገቶ ጠቁመው የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ ኢንቨስተሮች ፍቃድ ካወጡ በኃላ በፕላናቸው መሰረት ወደስራ እንዲገቡ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመፍታት ኢንቨስትመንቱ የማይተካ ድርሻ አለው ብለዋል።

ያለውን የኢንቨስትመንት ፖቴንሽያል በውል ለይቶ በማስተዋወቅ ረገድና መሰረተ ልማት በማሟላት ያሉ ክፍተቶችን መቅረፍ እንደሚገባም ምክትል ኮሚሽነሩ ጨምረው ገልፀዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተመስገን ከበደ የክልሉን አጠቃላይ ገጽታ፣ የኢንቨስትመንት አማራጮች፣ ካለው የተፈጥሮ ሀብትና ምቹ ሁኔታ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ መሆኑን በሰነድ አመላክተዋል።

ከፖቴንሽያል አንፃር የማዕድን ሀብት፣ መልማት የሚችል መሬት፣ ምቹ የሆነ የአየር ፀባይ ፣ የቡና ፣ የቅመማ ቅመም ፣ የፍራፍሬ ፣ የሰብል የመሳሰሉት የሚመረቱበት እንደሆነም በሰነዳቸው አቶ ተመስገን ጠቁመው ክልሉ የበርካታ ሀብት ባለቤት መሆኑን ጠቁመዋል።

የምክክሩ ተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተው በሚመለከታቸው መልስና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል ።

የምክክሩ ተሳታፊዎች በመጨረሻም በቤንች ሸኮ ዞን በቡናና ቅመማቅመም ልማት ኢንቨስትመንት ላይ ያለውን የበበቃ ኮፋ ስቴትስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የቡና ፣ የቁንዶ በርበሬ፣ የጎማ ዛፍ ልማትና ዘመናዊ የቡና መፈልፈያን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

ሌላው የጉብኝት አካል ያደረጉት በቤንች ሸኮ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ አሮጌ ብርሃን ቀበሌ ከ1000ሄ/ር በላይ እየለማ ያለውን የሞገስ ይመር የቡናና ቅመማቅመም ልማት ድርጅትንም በመዘዋወር ተመልክተዋል።

ኢንቨስትመንት ለመሳብ  የተለያዩ ለውጦችን በማድረግ አሳሪ የነበሩትን ጉዳዮች እንዲሻሻሉ መደረጉ ተገለፀ።የኢፌዴሪ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ዓመታዊ የምክክር መድረክ በቤንች ሸኮ ዞን  በሚዛን አ...
31/08/2024

ኢንቨስትመንት ለመሳብ የተለያዩ ለውጦችን በማድረግ አሳሪ የነበሩትን ጉዳዮች እንዲሻሻሉ መደረጉ ተገለፀ።

የኢፌዴሪ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ዓመታዊ የምክክር መድረክ በቤንች ሸኮ ዞን በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደገለፁት በሀገሪቱ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ስትራቴጂዎች በመቀየስ ሀገራዊ ጠቀሜታው እንዳጎላ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

ከመንግስት ባሻገር የግሉ ሴክተር በኢንቨስትመንት በሚሰማራበት በቴክኖሎጂ ሽግግር ፣ በልምድ ልውውጥ የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል።

በቅርቡ የተደረገው የማይክል ኢኮኖሚ ለኢንቨስትመንት ከውጭ ባለሀብቶችን መሳብ የሚያስችል ለሀገር ውስጥ ኢንቨስተሮች ምቹ የሆነ መደላድል የሚፈጥር የሚፈጥር መሆኑን ጠቁመዋል ።

ለኢንቨስትመንት እየተደረገ ያለውን ድጋፍና የመደገፍ ስራ እንደሚጠበቅም ገልፀዋል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በኢንቨስትመንት ዘርፍ ያሉ ብሮክራሲዎችን በማሳጠር በ2 ዓመታት ተኩል 180 ኢንቨስትመንቶችን መስጠት መቻሉን ገልፀዋል።

የኢፌዴሪ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር እና የዋናው ኮምሽነር ተወካይ አቶ ዳገቶ ኩምቢ እንደገለፁት በሀገሪቱ ተወዳዳሪ ና ተመራጭ የኢንቨስትመንት አማራጭ እንዲኖር መንግስት በርካታ ለውጦችን በማድረግ አሳሪ የሆኑ ጉዳዮች እንዲሻሻሉ መደረጉን ገልፀዋል።

የሀገሪቱን ፀጋ ለዓለም በማስተዋወቅ የሀገር ውስጥና የውጭ ኢንቨስተሮችን እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ምክትል ኮምሽነሩ ተናግረዋል።

ከኢንዱስትሪ ፓርኮችና ከኢንዱስትሪው የሚጠበቀውን ያህል የውጭ ምንዛሬ እንዲገኝ መንግስት እየሰራ ያለውን ስራ በሚገባ መደገፍ ይገባል ብለዋል።

አንዱ አካባቢ ያለውን ምርጥ ተሞክሮ ልምድ የሚቀሰምበት በክፍተቶች ዙሪያ መፍትሄ የሚቀመጥበት የምክክር መድረክ መሆኑን አቶ ዳግቶ ተናግረዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በበኩላቸው የቤንች ሸኮ ዞን በርካታ የኢንቨስትመንት አማራጭ ያለው ዞን መሆኑን ጠቁመው በ2016 ዓ.ም ከ27ሺህ ቶን በላይ ቡናን ለማዕከላዊ ገበያ የላከ መሆኑን ተናግረዋል።

የውጭ ምንዛሬ ሊያስገኙ የሚችሉ የተለያዩ ምርቶች የሚመረቱበት ፣ ምቹ የሆነ አካባቢ በመሆኑ በከተማም ሆነ በገጠር በኢንቨስትመንት መሰማራት ለሚፈልጉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ዞኑ ለመቀበል ዝግጁ መሆኑን አቶ ሀብታሙ ገልፀዋል።

ከ 7 ሺ በላይ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ*************የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ እና ምርት በመደበቅ ተግባር ላይ የተገኙ ከ7 ሺ በላይ ነጋ...
07/08/2024

ከ 7 ሺ በላይ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ
*************

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ እና ምርት በመደበቅ ተግባር ላይ የተገኙ ከ7 ሺ በላይ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡

በውጪ ምንዛሪ አስተዳደር ላይ የተደረገውን ለውጥ ምክንያት በማድረግ የተስተዋለውን የምርቶች ዋጋ መጨመር ለመግታት ከላይ እስከ ታች በተደራጀ አግባብ ክትትልና ቍጥጥር መደረጉን የገለጹት ሚኒስትሩ ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ መሰራቱንም ጠቅሰዋል፡፡

እንደ ሚኒስትሩ ገለፃ የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት መሰረታዊ ሸቀጦችን የጫኑ 1649 ተሽከርካሪዎች ወደ ገበያ እየገቡ ሲሆን ከ115 ሺ ሊትር በላይ የምግብ ዘይት በስርጭት ሂደት ውስጥ ይገኛል፡፡

በአሁኑ ወቅት ምንም አይነት የምርት እጥረት አለመኖሩን የገለጹት ዶ/ር ካሳሁን ከህገ ወጥ ተግባራቸው በማይቆጠቡ ነጋዴዎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስገንዝበዋል፡፡

ነሀሴ 1 ቀን 2016

በዞኑ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 36 የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ ሐምሌ 30/2016 ፡ በቤንች ሸኮ ዞን ከሰሞኑ ይፋ የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ተከትሎ ያልተገባ ...
06/08/2024

በዞኑ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 36 የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወሰደ

ሐምሌ 30/2016 ፡ በቤንች ሸኮ ዞን ከሰሞኑ ይፋ የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ተከትሎ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ 36 የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱን የቤንች ሸኮ ዞን ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ፡፡

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ኮጁ በደካች እንደተናገሩት ማሻሻያውን ትከትሎ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪን ለመከላከል የቁጥጥር እና ክትትል ስራ እያከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

ሸማቹ ህብረተሰብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ እና ምርት በሚያሸሱ ነጋዴዎች ላይ ጥቆማ በመስጠት ከመንግስት ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል፡

መንግስት የማይክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ ማደረጉን ተከትሎ በዞናችን የሚገኙ ነጋዴዎች ማንኛዉም የዋጋ ጭማሪ እንዳያደርጉ መግለጫ መሰጠቱንም አስታውሰዋል፡፡

በዚህም የኢኒስፔክሸን ሥራዎች ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዉ በዞን ደረጃ በተጨባጭ የዋጋ ጭማሪ መደረጉን ማረጋገጥ መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡

በመሆኑም የጅምላና አከፋፋይ ነጋዴዎች በግንባታ ቁሳቁሶችና የምግብ ዘይት ላይ የዋጋ ጭማሪ ማድርጋቸዉን ተናግረዉ በተደጋጋሚ ከእኩይ ተግባራቸዉ እንዲቆጠቡ ቢደረግም ለመታረም ባለመቻላቸዉ እርምጃ መወሰዱን አስረድተዋል፡፡

አክለዉም በዞን ደረጃ 36 ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወስደዋል ብለዉ እርምጃዉም ቀጥታ ሱቆችን በማሸግ መሆኑንም ጨምረዉ ገልጸዋል፡፡

አምስት የሚሆኑ ጅምላ ነጋዴዎች በዚህ ዉስጥ መሳተፋቸዉን ያብራሩት አቶ ኮጁ በምርት ላይ ዋጋ ጭማሪ ያደረጉት ነጋዴዎች ምንም ዓይነት ምክንያታዊ የሆነ ነገር ሳይኖር ሆን ተብሎ የመንግስት ፖሊስን ለመቀልበስ ታስቦ የተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አቶ ኮጁ አያይዘዉም ሌሎች ነጋዴዎች ከመሰል እኩይ ተግባር እንዲታቀቡ አሳስበዉ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎች ከህጋዊ እርምጃ ዉጪ በንግዱ ስርዓት አዋጅ መሠረት አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድባቸዉም ጭምር አስጠንቅቃል፡፡

ሸማቹ ህብረተሰብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ እና ምርት በሚያሸሱ ነጋዴዎች ላይ ጥቆማ በመስጠት ከመንግስት ጎን እንዲቆም ጥሪ ያቀረቡት አቶ ኮጁ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎችን ሁለትና ሶስት በመሆን በህግ ሊያስጠይቁ የሚችሉበት ስርዓት እንደተዘረጋም ገልጸዋ፡፡

በስተመጨረሻም የታችኛዉ መዋቅር የመንግስት ፖሊሲን ከማስፈጻም ረገድ በቁርጠኝነት በመስራት በህዝቡ ላይ የተጋረጠዉን የዋጋ ጭማሪ በህግና በስርዓት እንዲፈታ አሳስበዋል፡፡

መሰረታዊ ሸቀጦችን ጭነው በጉምሩክ ጣቢያ ቆመው የነበሩ  273 ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው የጉምሩክ ስነ-ስርዓት ጨርሰው ወደ መዳረሻቸው ምርቶችን ማጎጎዝ መጀመራቸው ተገለጸ።==========...
05/08/2024

መሰረታዊ ሸቀጦችን ጭነው በጉምሩክ ጣቢያ ቆመው የነበሩ 273 ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው የጉምሩክ ስነ-ስርዓት ጨርሰው ወደ መዳረሻቸው ምርቶችን ማጎጎዝ መጀመራቸው ተገለጸ።
==========================
29/11/2016 መሰረታዊ ሸቀጦችን ጭነው በጉምሩክ ጣቢያ ቆመው የነበሩ በርካታ ተሽከርካሪዎች ዙሪያ ከጉምሩክ ጋር በተደረገ ውይይት ተሽከርካሪዎቹ መሰረታዊ ሸቀጦቹን ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ይዘው እንዲንቀሳቀሱ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።

በዛሬው ቀን ብቻ 101 ከባድ ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው 4,444,000 ሌትር ዘይት የያዙ፣
80 ከባድ ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው 32,000 ኩንታል ስኳር የጫኑ፣ 23 ከባድ ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው 9,200 ኩንታል ሩዝ የጫኑ፣ 69 ከባድ ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው 27,600 ኩንታል የስንዴ ዱቄት የጫኑ፣ በጥቅሉ 273 ተሽከርካሪዎች ከነተሳቢያቸው የጉምሩክ ስነስርዓት ጨርሰው ወደ መዳረሻቸው መንቀሳቀሳቸውን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በነገው እለት ከፍተኛ ቁጥር ያለው መሰረታዊ ሸቀጥ ከጉምሩክ ጣቢያዎች ወደ መላው የሀገራቱ አከባቢዎች የሚጎጎዝ መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቁመዋል::

ከ14 ሚሊዮን ሌትር በላይ የምግብ ዘይት በሚቀጥለው ሳምንት በመላው ሀገሪቱ  ይሰራጫል ******************በአዳማ ጉምሩክ ጣቢያ መሰረታዊ ሸቀጦችን ጭነው የቆሙ ከ700 በላይ ተሽከር...
04/08/2024

ከ14 ሚሊዮን ሌትር በላይ የምግብ ዘይት በሚቀጥለው ሳምንት በመላው ሀገሪቱ ይሰራጫል
******************

በአዳማ ጉምሩክ ጣቢያ መሰረታዊ ሸቀጦችን ጭነው የቆሙ ከ700 በላይ ተሽከርካሪዎች ለገበያ ምርት በሚቀርብበት አግባብ ላይ ውይይት መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።

በአዳማ ጉምሩክ ጣቢያ የተለያዩ መሰረታዊ ሸቀጦችን ጭነው የቆሙ ከ700 በላይ ተሽከርካሪዎች የጉምሩክ ስነ ስርዓት ጨርሰው ለገበያው ምርት በሚቀርብበት አግባብ ላይ በጋራ በመወያየት የመፍትሄ አቅጣጫ መቀመጡን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።

በተለይ ገንዘብ ሚኒስቴር አዲስ ካወጣው የቫት ክፊያ ጋር ተያይዞ አስራር ላይ ያጋጠመው የግልፀኝነት መጓደል ሙሉ በሙሉ ተቀርፎ አብዛኛው ተሽከርካሪ ወደ ገበያ የሚያቀርቡ መሆናቸውን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

የገበያ ሁኔታን በዘላቂነት ለማረጋጋጥ በመንግስት ግዢው የተፈፀመው ከ14 ሚሊየን ሌትር በላይ የምግብ ዘይት በሚቀጥለው ሳምንት በመላው ሀገሪቱ የሚስራጭ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንግድ ማህበረሰብ አባላት እና ከከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ጋር የፋይናንስ ሚኒስትር ዲኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በተገኙበት መንግስት በቅርቡ ተግባራዊ ባደረ...
04/08/2024

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንግድ ማህበረሰብ አባላት እና ከከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ጋር የፋይናንስ ሚኒስትር ዲኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በተገኙበት መንግስት በቅርቡ ተግባራዊ ባደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ማሻሻያ ዙሪያ ውይይት አደረጉ።

ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው እንደገለፁት ሪፎርሙ ለሀገራችን በርካታ ጥቅም የሚያስገኝ ሲሆን በዋነኛነት ዘላቂ ልማትንና አካታችነትን ለማረጋገጥ፣ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሚያደርግ የኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት፣ የመንግስትን የእዳ ጫና ለመቀነስ፣ የተረጋጋ ተወዳዳሪ እና የዋጋ ግሽበትን መቀነስ የሚያስችል የገበያ ሁኔታን ለመፍጠር፣ ተኪ ምርቶችን በማምረትና ለውጪ ገበያ የምንልከውን ምርት በማሳድግ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ እንዲሁም ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ በመፍጠር የውጪ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ እድል የሚፈጥር ይሆናል ብለዋል።

ወቅታዊ ተግዳሮቶችን ለመቆጣጠር ደሃው እና ዝቅተኛ ገቢ ያለው ማህበረሰብ እንዳይጎዳ የመንግስት ሰራተኞችን ደሞዝ መጨመር፣ ደሃውን መደጎም ፣ በተለይም በሴፍቲኔት የታቀፉ የማህበረሰብ ክፍሎችን ገቢ በሚያስገኝና ተረጂነትን በሚቀንስ መንገድ መደገፍ እንዲሁም የስራ እድልን በስፋት መፍጠርን ታሳቢ ባደረገ መልኩ የሚተገበር ሲሆን በቀጣይም ከአምራቾች እና አስመጪዎች ጋር በቅርበት በመስራት እንዲሁም ገበያውን የሚያዛቡ፣ በተለይም ምንም ከውጪ ምንዛሪ ጋር ግንኙነት የሌላቸው ምርቶች ላይ አላግባብ ዋጋ በሚጨምሩ እና ምርት በሚሰውሩ አካላት ላይ ጠንካራ የሆነ ቁጥጥር እና ህግ የማስከበር ስራ እንደሚሰራ አሳውቀዋል።

የኢኮኖሚ ማሻሻያዉን ተከትሎ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል--------------------------------- የኢኮኖሚ ማሻሻያዉን ተከትሎ የዋጋ ጭማሪ በሚ...
03/08/2024

የኢኮኖሚ ማሻሻያዉን ተከትሎ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል
---------------------------------

የኢኮኖሚ ማሻሻያዉን ተከትሎ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን የዳዉሮ ዞን ታርጫ ከተማ አስተዳደር ሥራ ክህሎት ንግድና ኢንተረፍራዝ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ መንግስቱ ይመኑ ገልጿል።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፓሊስ መግለጫን ተከትሎ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ ስድስት የንግድ ድርጅቶች መታሸጋቸው ተገልፀዋል።

አቶ መንግስቱ ይመኑ እንደገለጹት የታሸጉ ስድስት የንግድ ድርጅቶች በተለዩ ሸቀጣሸቀጦች ላይ ምክንያታዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ መሆናቸውን የገለፁ ስሆን በዚህም ባለ 5 ሌትር ዘይት ከ1000ብር ወደ 1200 ብር፣ ባለ 3 ሌትር ዘይት ከ530 ወደ 750 ብርና የ20 ሌትር ዘይት ከ4000ብር ወደ 5600ብር በማሳደግ የዋጋ ጭማሬ ማድረጋጌ ተረጋግጦ የንግድ ቤቶቹ መታሸጋቸውን አሳውቀዋል።

በተመሳሳይ መልኩ ፓስታ ከ70 ብር ወደ 80 ብር በማሳደግ የሸጡና፣ እንዲሁም የመሽጫ ዋጋ ( የምግብና መጠጥ ) ያልለጠፉ ሶስት ሆተሎችና አስር ሱቆችን እንድታሸጉ ማድረግ የተቻለ ስሆን የክትትል ቡድኑ በቀጣይነት ክትትሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አቶ መንግስቱ ይመኑ ገልፀዋል።

በመጨረሻም ከሰሞኑ በተደረገዉ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ህብረተሰቡ ላይ መደናገጦች መታየታቸዉን ገልፀዉ በንግዱ ማህበረሰብ ላይ የሚታዩ አላግባብ ተግባራትን ለመቆጣጠር ግብረ ሀይል የተቋቋመ ስሆን ማንኛውም ነጋዴ በዚህ ምክንያት ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ ማድረግ እንደማይችል ገልፀዉ ከስርዓቱ ወጥተው በተገኙ ላይ እየተወሰደ ያለዉ እርምጃ ተጠናክሮ እንደምቀጥል ተናግረዋል።

በጀሙ ከተማ በህገ ወጥ ተግባር በፈጸሙ 23 የንግድ  ተቋማት ላይ የማሸግ እርምጃ ተወሰደ።ሐምሌ 27 ቀን 2016ዓምበምዕራብ ኦሞ ዞን በጀሙ ከተማ አስተዳደር  በሀገሪቱ የተደረገውን የማክሮ ...
03/08/2024

በጀሙ ከተማ በህገ ወጥ ተግባር በፈጸሙ 23 የንግድ ተቋማት ላይ የማሸግ እርምጃ ተወሰደ።
ሐምሌ 27 ቀን 2016ዓም
በምዕራብ ኦሞ ዞን በጀሙ ከተማ አስተዳደር በሀገሪቱ የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያን ተከትሎ ህገ ወጥ ስራን እየሰሩ በሚገኙ ነጋዴዎች ላይ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል።

በከተማው ግብረሀይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቅሶ የህገ ወጥ የሸቀጦች ዋጋ ጭማሪና ምርትን የማከማቸት ህገ ወጥ ተግባርት ዙሪያ የተሳተፉ ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ ተገልጿል።

በከተማው በዛሬው ቀን ያላግባብ ዋጋ በጨመሩ፤ ምርት በደበቁና ለህግ ተገዢ ባልሆኑ የንግድ ተቋማት የማሸግ እርምጃ ሲወሰድ መቆየቱ ተገልጿል።

በከተማዉ ፍትሃዊ የገበያ ውድድር ስርዓት በማህብረሰቡ መካከል እንዲኖር ትልቁ የመንግሥት ኃላፊነት ሆኖ ሳለ የነፃ ስርዓት እስከሚሆን ድረስ በገበያ ጉድለት ዉስጥ ከፍተኛ ሚና አላቸው ተብሎ በመረጃ በተለዩት የምግብ ነክ አቅራቢ፣ ሸቀጦችና የህንፃ መሣሪዎች ላይ ጥልቅ ወይይት ካደረጉ በኋላ የጋራ አቅጣጫዎች በማስቀመጥ ሥራ ዛሬ ጀምሯል።

በዛሬዉ ዕለት የጋራ ዉሣኔ ሰጪዉ ግብረኃይል ችግር ያለባቸው ከ 23 በላይ የንግድ ድርጅቶች ላይ አስተማሪ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።
እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

ህገ ወጥ ተግባር በፈጸሙ 2202 የንግድ  ተቋማት ላይ የማሸግ እርምጃ ተወሰደ።=================== የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከክልልና ከከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ጋር ...
03/08/2024

ህገ ወጥ ተግባር በፈጸሙ 2202 የንግድ ተቋማት ላይ የማሸግ እርምጃ ተወሰደ።
===================
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከክልልና ከከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን በሀገሪቱ የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያን ተከትሎ ህገ ወጥ ስራን እየሰሩ በሚገኙ ነጋዴዎች ላይ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል።

ከብሄራዊ የንግድ ተቋማት የፀረ ህገ ወጥ ንግድና ገበያ መቆጣጠርያ የጋራ ኮሚቴ አባላት ጋር የህገ ወጥ የሸቀጦች ዋጋ ጭማሪና ምርትን የማከማቸት ህገ ወጥ ተግባርት ዙሪያ በየክልሉ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች አፈፃፀምን መገምገማቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገልጸዋል።

በሪፖርቱ እጅግ አበረታች የሆነ ጅምር የህገ ወጥ ንግድ ቁጥጥር ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ የገለጹት ሚኒስትሩ በሚቀጥሉት ቀናትም ቁጥጥሩ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።
ለአብነት በዛሬው ቀን ብቻ ያላግባብ ዋጋ በጨመሩ፤ ምርት በደበቁና ለህግ ተገዢ ባልሆኑ 967 የንግድ ተቋማት የማሸግ እርምጃ ሲወሰድ 9ኙ ደግሞ የንግድ ፈቃድ እገዳ ተጥሎባቸዋል፡፡ በተመሳሳይ የ2 ተቋማት ፈቃድ ተሰርዟል፡፡ ከህገ ወጥ ተግባራቸው እንዲታረሙና ማስተካያ እንዲያደርጉ ተነግሯቸው ለማስተካከል ፍቃደኛ ያልሆኑ 49 ነጋዴዎች በእስራት መቀጣታቸውን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ አስከዛሬው ድረስ ደግሞ 2202 የንግድ ተቋማት ላይ የማሸግ እርምጃ ሲወሰድ፤ በ18ቱ ላይ የንግድ ፍቃድ እገዳ እንዲሁም በ6 ተቋማት ላይ የንግድ ፍቃድ ስረዛ እርምጃዎች ሲወሰዱ ከህገ ወጥ ተግባራቸው ለመታረም ፍቃደኛ ባልሆኑ 87 ነጋዴዎች ላይ የእስራት ቅጣት ተጥሏል፡፡

ህገወጥ ዋጋ በጨመሩ ነጋዴዎች ላይ የተቀናጀ እርምጃ መውሰድ ተጀምሯል። ህገወጥ ዋጋ በመጨመር ኢፍትሐዊ  ንግድ አሠራር ውስጥ በገቡት አካላት ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት እርምጃ እየተወሰደ እ...
03/08/2024

ህገወጥ ዋጋ በጨመሩ ነጋዴዎች ላይ የተቀናጀ እርምጃ መውሰድ ተጀምሯል።

ህገወጥ ዋጋ በመጨመር ኢፍትሐዊ ንግድ አሠራር ውስጥ በገቡት አካላት ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት እርምጃ እየተወሰደ እንደምገኝ የዳውሮ ዞን ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ወራቦ ገልጸዋል።

በዳውሮ ዞን ውስጥ ባሉት 10 ወረዳዎች እና ሁለት ከተማ አስተዳደር ሀገራዊ ኢኮኖሚ ሪፎርምን በማሳበብ በመሠረታዊ ሸቀጦችና ምርቶች ላይ ህገወጥ ዋጋ የጨመሩ 41 ንግድ ተቋማት ታሽጓል።

የታሸጉ ንግድ ተቋማት በተለይም በስኳር፣ ዘይት፣ ፋብሪካ ምርቶች ላይ ዋጋ የጨመሩና የምግብና ሸቀጥ ዋጋ ዝርዝር ለማውጣት ፈቃደኛ ያልሆኑ ናቸው ብለዋል።

ስለዚህ አንዳንድ ነጋዴዎች በህገ ወጥ ዋጋ ጭማሪ ከመሳተፍና ምርት ከመደበቅ እንድታቀቡ እየገለፅን በዚህ ህገወጥ ተግባር የሚሳተፉ አካላትን በማጋለጥ ከክትትልና ቁጥጥር ግብረሃይል ጎን በመቆም ህብረተሰቡ የጀመረውን ትብብር እንድያጠናክር አቶ ወንድሙ አሳስበዋል።

በክልሉ ያለአግባብ ዋጋ በጨመሩና የፍጆታ ዕቃዎችን በደበቁ 56 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለፀየደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ በክልሉ በመሠረታ...
03/08/2024

በክልሉ ያለአግባብ ዋጋ በጨመሩና የፍጆታ ዕቃዎችን በደበቁ 56 የንግድ ድርጅቶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ በክልሉ በመሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎች ላይ ያለአግባብ ዋጋ የጨመሩና ምርትን/ዕቃን ያሸሹ 56 የንግድ ድርጅቶችን ማሸጉን የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አምደ ፉሪስ ገልጸዋል፡፡

አቶ አምደ ፋሪስ አክለውም በቀጣይም ያለአግባብ የዋጋ ጭማሪ በሚያደረጉና ምርትን ያለአግባብ በማከማቸትና በመደበቅ በገበያ ላይ ሰው ሠራሽ ዕጥረት እንዲፈጠር በሚያደርጉ የንግድ ድርጅቶች ላይ የሚወሰደዉ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳወቀዋል፡፡

Address

South West
Bonga

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when South West Ethiopian Peoples Regional State Trade & Investments Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share