Southwest Culture Tourism & Sport Bureau

Southwest Culture Tourism & Sport Bureau It is the official Regional Government Office

ከኢፌዲሪ ባህልና ስፓርት ሚኒስቴር የተውጣጡ የክትትልና ድጋፍ ቡድን በጊምቦ ወረዳ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ምልከታ አደረጉ።‎‎የክትትልና ድጋፍ ቡድኑ በጊምቦ ወረዳ የስፖርት ጂም ቤት፣ዘመና...
13/06/2026

ከኢፌዲሪ ባህልና ስፓርት ሚኒስቴር የተውጣጡ የክትትልና ድጋፍ ቡድን በጊምቦ ወረዳ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ምልከታ አደረጉ።

‎የክትትልና ድጋፍ ቡድኑ በጊምቦ ወረዳ የስፖርት ጂም ቤት፣ዘመናዊ ኮፊ ሐውስ እና በጋሪ ያሆ ባህል መንደር ውስጥ የተለያዩ የቅርስ እቃዎችን ጨምሮ በፕሮጀክት ደረጃ ተይዘው እየተሰሩ ያሉ የወተት ላም፣የቦንጋ በግ እርባታ፣የእንቁላል ጣይ ዶሮ፣የንብ ማነብ እና ሌሎችም የልማት ስራዎች ናቸው የተጎበኙት።

‎የጊምቦ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተገኝ ማሞ እንዳሉት ጽህፈት ቤቱ በባህል አማካሪ ም/ቤት በኩል በወረዳ ደረጃ የሚሰሩ ሥራዎች በግንባር ቀደምትነት እየተስፋፋ መሆኑን ገልጸዋል።

‎አቶ ተገኝ አክለው በወረዳው መንግስት መልካም ፍቃድ ለህዝብ አገልግሎት ለሚውሉ ሥራዎች በጀት መድቦ የተለያዩ ተግባራትን ከባህል አማካሪ ም/ቤቱ ጋር በጋራ በመሆን እየሰራ እንደሆነ አብራርተዋል።

‎በባህል ማዕከል ውስጥ ያሉ የተለያዩ ታሪክ ያዘሉ ቅርሶችንና በጀግንነት ታሪክ የሰሩትን በተመለከተ በሙዝየሙ ሥራ አስኪያጅ በጊምቤራሻ መለሰ መሸሻ በኩል ለክትትልና ድጋፍ ቡድኑ ማብራሪያ ተሰጥተዋል።

‎የክትትልና ድጋፍ ቡድኑ በወረዳው በተመለከቱት የልማት እንቅስቃሴ መደሰታቸውንም አስታውቀዋል።

‎እስከ ስፍራው ተገኝተው ተግባራትን ለተመለከቱ የክትትልና ድጋፍ ቡድኑ የወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ተገኝ ማሞ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

‎በእለቱም የስፖርት ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ አበባ አማሬን ጨምሮ ሌሎች የፌደራል እንግዶች ከወረዳው ባለድርሻ አካላቶች ጋር በመሆን ነው ምልከታ ያደረጉት::

በክልሉ ለ5 ተከታታይ ቀናት የቆየው የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን የመጨረሻ የምልክታ ሥራዎችን በካፋ ዞን በግንቦ ወረዳ ማጠቃለያ በማድረግ የድጋፍና ክትትል ስራቸ...
12/06/2026

በክልሉ ለ5 ተከታታይ ቀናት የቆየው የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን የመጨረሻ የምልክታ ሥራዎችን በካፋ ዞን በግንቦ ወረዳ ማጠቃለያ በማድረግ የድጋፍና ክትትል ስራቸውን አጠናቀቁ


‎ //ሰኔ 05/2018 ዓ.ም፣ ቦንጋ//


‎በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የማጠቃለያ የድጋፍና ክትትል ሥራዎችን የሚያደርጉ የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን በክልሉ ለ5 ተከታታይ ቀናት በመቆየት በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራትን ከቢሮ እስከ ወረዳና ከተማ አስተዳደር በመገምገምና ምልከታ በማድረግ ዛሬ በግንቦ ወረዳ ማጠቃለያ በማድረግ የድጋፍና ክትትል ሥራቸውን አጠናቀዋል።


‎ቡድኑ በቢሮ በባህል፣ በቋንቋ፣ በዕደ ጥበብ፣ በኪነ ጥበብ፣ በቅርስ አሰባሰብና አደረጃጀት፣ በቤተ-መጽሐፈት፣ በባህል ማዕከላት አደረጃጀት፣ በታዳጊ ስፖርተኞች አደረጃጀት፣ በማዘወተሪያ ሥራዎች ግንባታ፣ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ እና በሌሎችም ዘርፍ የተከናወኑ ሥራዎችን በመገምገም በኮንታና በካፋ ዞኖች በአካል ተገኝተው በቢሮ የተገመገመውን አጠቃላይ ሥራዎችን ተዟዙሮ ምልከታ አደርገዋል።

‎የድጋፍና ክትትል ቡድኑ በግንቦ ወረዳ በባህል ማዕከልና በውስጡ የሚገኙ ታሪካዊ ቅርሶች፣ በግቢ ውስጥ ያሉ የበግ፣ የወተት ላሞች፣ የእንቁላል ዶሮዎች እና የተለያዩ ዝሪያ ያላቸው ችግኝ ጣቢያም ተዟዙሮ ተመልክቷል።

‎ቡድኑ በማጠቃለያው ከክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ እስከ ግንቦ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽ/ቤት ድረስ የተደረገላቸው መልካም አቀባበል ምስጋናቸውን በማቅረብ በምልከታቸው የተሻለ አፈጻጸም ማየት መቻላቸውን ጠቅሰው በቀጣይነት የድጋፍና ክትትል ሥራ እንደሚያደርጉም አረጋግጠዋል።

‎የክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ቡድን አባላት ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከመጡ ከድጋፍና ክትትል ቡድን ጋር አብረው በቦንጋ ከተማ በፕሮጀክት ለታቀፉ በብስክሌት ለተደራጁ ስፖርተኞች፣ በፓራሊምፒክ ለተደራጁ ስፖርተኞች እና በግንቦ ወረዳ በእግር ኳስ ለተደራጁ ለታዳጊ ወጣቶች የትጥቅ እና ኳስ ድጋፍም አደርገዋል።

‎መረጃው የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ነው።

ኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን የምልከታ ሥራቸውን በካፋ ዞን ቀጥሏል።‎‎     //ሰኔ 04/2018 ዓ.ም፣ ቦንጋ//‎‎በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከኢፌ...
12/06/2026

ኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን የምልከታ ሥራቸውን በካፋ ዞን ቀጥሏል።

‎ //ሰኔ 04/2018 ዓ.ም፣ ቦንጋ//

‎በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የመጡ የድጋፍና ክትትል ቡድን ከክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ጋር በመሆን በበጀት ዓመቱ በባህልና ስፖርት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራትን በተመረጡ ዞኖች ተገኝተው የምልከታ ሥራቸውን እያከናወኑ ይገኛል።


‎ቡድኑ ዛሬ በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ተገኝተው በስፖርት ዘርፍ የታዳጊ ወጣቶች ፕሮጀክቶች፣ ማህበረሰብ አቀፍ የአካል ብቃት ስፖርት እንቅስቃሴ ሁኔታን፣ የማዘውተሪያ ግንባታ ያለበት ደረጃ፣ በባህል ዘርፍ የባህል ሙዚየም፣ የቅርሶች አሰባሰብና አደረጃጀት፣ ባህላዊ የዳኝነት ሥርዓት አደረጃጀትና ክዋኔ፣ የቤተ-መጽሐፍት አደረጃጀትና አጠቃቀም ሁኔታ፣በኪነ-ጥበብ ዘርፍ የባህል ኪነት አደረጃጀት፣ የዕደ-ጥበብ ሥራ ወጤቶች፣ የባህላዊ ወገሻ ሥራዎችን፣የቡና ሙዚየም እና ሌሎች ሥራዎችን ተዟዙሮ የምልከታ ሥራዎችን አካናወነዋል።

‎የምልከታ ሥራዎች በተመረጡ ወረዳዎችም እንደሚቀጥል ተገልጿል።

‎መረጃው የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ነው።

ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ተልዕኮ ተሰጥቶት ወደ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ያቀናው የድጋፍና ክትትል ቡድን ዛሬ በቦንጋ ከተማ ተገኝተው ከቦንጋ ነዋሪዎች ጋር የአካል ብቃት እንቅስ...
11/06/2026

ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ተልዕኮ ተሰጥቶት ወደ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ያቀናው የድጋፍና ክትትል ቡድን ዛሬ በቦንጋ ከተማ ተገኝተው ከቦንጋ ነዋሪዎች ጋር የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አደርገዋል

‎ //ሰኔ 04/2018 ዓ.ም፣ ቦንጋ//

‎የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር መስሪያ የድጋፍና ክትትል ቡድን በክልሉ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የተከናወኑ ተግባራትን ገምግሞ በዞኖች ያሉ ሥራዎች በአካል ተዟዙሮ እየተመከቱም ይገኛሉ።

‎ዛሬ በጠዋት ክፍለጊዜ ከቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች ጋር የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ ጀምረዋል።

‎የሌሎች ሥራዎች ምልከታ መርሃ-ግብር የሚቀጥል ይሆናል።

‎መረጃው የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ነው።




ኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ተገኝተው በክልሉ በባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ በባህልና ስፖርት ዘርፍ የተከናወነውን ተግባራት በዞኖች ተዟዙሮ ምልከታ እያደረ...
10/06/2026

ኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ተገኝተው በክልሉ በባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ በባህልና ስፖርት ዘርፍ የተከናወነውን ተግባራት በዞኖች ተዟዙሮ ምልከታ እያደረጉ ይገኛሉ።

‎ //ሰኔ 03/2018 ዓ.ም//

‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ ሥራዎችን የሚገመገሙ የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን ዛሬም በኮንታ ዞን ተገኝተው በባህልና ስፖርት ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራትን ተዟዙሮ ምልከታ አደርጓል።

‎በስፖርት ዘርፍ የታዳጊ ስፖርተኞች ፕሮጀክት ያለበት ደረጃ፣ በባህል ዘርፍ በዝሆን ዳና ሎጅ ውስጥ የሚገኘው የኮንታ ብሔረሰብ ቅርሶችን፣ በባህል ማዕከል ውስጥ ያለው ቅርሶችን፣ የዕድ ጥበብ ሥራ ውጤቶችን፣ ኪነ-ጥበብ ሥራዎችን፣ የቤተመጻሕፍት አገልግሎትን፣ የባህላዊ መድኃኒት እና ጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክን ጨምሮ ቡድኑ ጉብኝት አደርገዋል።

‎ቢሮ በጭዳ ከተማ እና በአመያ ከተማ በፕሮጀክት ለታቀፉ ለታዳጊ ስፖርተኞች የትጥቅ ድጋፍም አደርገዋል።

‎በሌሎች ዞኖችም የምልከታና የትጥቅ ድጋፍ የሚቀጥል እንደሆነም ተገልጿል።

‎መረጃው የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ነው።

ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለድጋፍና ክትትል የተሰማራው የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ቡድን የቢሮ ሥራዎች ግምግማ አጠናቀው በዞኖች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛል።‎‎በዚሁ መሠረት ...
09/06/2026

ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለድጋፍና ክትትል የተሰማራው የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ቡድን የቢሮ ሥራዎች ግምግማ አጠናቀው በዞኖች የመስክ ምልከታ እያደረጉ ይገኛል።

‎በዚሁ መሠረት ዛሬ በጠዋት ክፍለ-ጊዜ በታርጫ ከተማ የባህል ሙዚየም፣ የባህል አደራሽ ግንባታ እና በታርጫ ከተማ በታዳጊ ወጣቶች የታቀፈውን U-13 ስፖርተኞችን ተዟዙሮ ተመልክቷል።

‎በቀጣይነትም በተመረጡ ዞኖች፣ ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደሮች ውስጥ በባህል ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያዎችና ጽ/ቤቶች በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራትን የሚገመገሙት ይሆናል።

‎መረጃው የባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ነው።

08/06/2026
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ  ለክልሉ ባህልና ስፖርት ዘርፍ እድገትና ውጤታማነት እያደረገ ያለው ድጋፍና ክትትል የሚደነቅ ነው_አቶ ፋንታሁን ብላቴ‎‎የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የድጋፍና ክት...
08/06/2026

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለክልሉ ባህልና ስፖርት ዘርፍ እድገትና ውጤታማነት እያደረገ ያለው ድጋፍና ክትትል የሚደነቅ ነው_አቶ ፋንታሁን ብላቴ

‎የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የድጋፍና ክትትል ቡድን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በባህልና ስፖርት ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራትን በጋራ ለመገምገም ያለመ የምክክርና የጋራ መድረክ አካሂዷል።

‎መድረኩ በዋናነት በዘርፉ የተከናወኑ አበይት ተግባራትን በጋራ ለመገምገም፣ ጥንካሬዎችን ለማጉላት እና የታዩ ክፍተቶችን በጋራ ለመቅረፍ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

‎የውይይት መድረኩን የመሩ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ብላቴ ፣ የፌደራል ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ለክልሉ የባህልና ስፖርት ዘርፍ ልማት እያደረገ ያለው ድጋፍና ክትትል ከፍተኛና የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

‎አቶ ፋንታሁን አክለውም "ቢሮአችን የክልሉን እምቅ የባህልና የስፖርት ሀብት በመጠቀም፣ የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

‎የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የድጋፍና ክትትል ቡድን መሪ ወ/ሮ አበባ አማረ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ እየተከናወኑ ያሉ የድጋፍና ክትትል ስራዎች በየደረጃው ባሉ የአፈፃፀም ክፍተቶች ላይ ከፍተኛና ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ ይገኛሉ ብለዋል።

‎ወ/ሮ አበባ አክለውም ይህ ዓይነቱ አሰራር በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱና በክልሎች መካከል ያለውን የስራ ግንኙነትና ትስስር ይበልጥ ያጠናክራል።

‎በክልሉ በዘርፉ የተመዘገቡ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመለየት፣ ልምድ እንዲሆን ለሌሎች ክልሎች ለማቅረብና ለማስፋፋት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥረም ጨስረድተዋል።

‎የድጋፍ ቡድኑ አባላት እንደተናገሩት፣ በጋራ የተደረገው ግምገማ በክልሉ ያሉትን አበረታች ስራዎች ይበልጥ ለማጉላትና በቀጣይም ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር አመልክተዋል።

የባርታ ፏፏቴ፤ ከለምለም አረንጓዴ ተክሎች በስተጀርባ የተሸሸገው የተፈጥሮ ድንቅ ስጦታ‎‎የተፈጥሮ መስህብ የሆነውን የባርታ ፏፏቴ ከአዲስ አበባ በ453 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ...
08/06/2026

የባርታ ፏፏቴ፤ ከለምለም አረንጓዴ ተክሎች በስተጀርባ የተሸሸገው የተፈጥሮ ድንቅ ስጦታ

‎የተፈጥሮ መስህብ የሆነውን የባርታ ፏፏቴ ከአዲስ አበባ በ453 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ከቦንጋ ከተማ ተነስተው በስተደቡብ አቅጣጫ 5 ኪሎ ሜትር ገደማ ብቻ በመጓዝ ያገኙታል።

‎ከ70 ሜትር ከፍታ ቁልቁል የሚወረወረው እና 20 ሜትር ስፋት ያለው ይህ ፏፏቴ፣ ከግርጌው ባለው የተፈጥሮ ገንዳ ላይ የሚያርፍበት ዕይታ ለዓይን ይማርካል።

‎የባርታ ፏፏቴ ውበት በውኃው ፍሰትና በለምለሙ የአረንጓዴ ተክሎች ሽፋን ብቻ የሚወሰን አይደለም። አካባቢው ለተለያዩ ብርቅዬ ወፎች እና ማራኪ የዓሣ ዝርያዎች አስተማማኝ መጠለያና መገኛ በመሆኑም ይታወቃል።

‎ይህ ተፈጥሯዊ ስምምነት ስፍራውን ለአዕምሮ እረፍት፣ ለአዕዋፋት አድናቂዎች እና ከተፈጥሮ ጋር ጊዜ ማሳለፍ ለሚሹ ጎብኚዎች ሁሉ ፍጹም ተስማሚ ያደርገዋል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል።

የ2018 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና የወንዶች እና ሴቶች ውድድር ከሐምሌ 5 - ነሐሴ 3 በድሬዳዋ ከተማ እንደሚካሄድ የውድድር ዳይሬክቶሬት አስታውቋል።
04/06/2026

የ2018 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና የወንዶች እና ሴቶች ውድድር ከሐምሌ 5 - ነሐሴ 3 በድሬዳዋ ከተማ እንደሚካሄድ የውድድር ዳይሬክቶሬት አስታውቋል።

Address

Bonga

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Southwest Culture Tourism & Sport Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Southwest Culture Tourism & Sport Bureau:

Share