04/06/2026
በሁሉም ፈጣሪ አምላክ ረድቶን 7ኛውን ዙር ምርጫ ባጠናቀቅንበት ማግስት ዛሬ 8ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት ክፍት አድርገናል።
ለህዝባችን በገባነው ቃል መሰረት ዛሬ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ባለ 7 ወለል ህንፃ ገንብተን በቴክኖሎጂ ተደራጅቶ 96 ተገልጋዮችን በአንድ ጊዜ የሚያስተናግዱ መስኮቶች ያሉት፣ በ22 ተቋማትና በ114 አገልግሎቶች ስራ አስጀምረናል።
ማዕከሉ ከፍ ባለ ጥራት እጅግ ውብ፣ ፅዱ፣ አካታች የሆነ ለአካል ጉዳተኞች ምቹ፣ የህፃናት ማቆያ ያለው፣ ለሰራተኞችም ለተገልጋዮችም ምቹ ሆኖ የተገነባ ነው።
በቀጣይም በርካታ አገልግሎቶችን ወደ መሶብ ማዕከል በማስገባት ነዋሪዎች ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት እንዲያገኙ እናደርጋለን።
የከተማችን ነዋሪዋች መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አግልግሎት ለዘመናት አስልቺ ከነበረውና ውጣ ውረድ ከበዛበት እና በእጅ መንሻ ከተማረራችሁበት ቢሮክራሲ የሚያላቅቃችሁ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ! በማዕከላቱ በቦታ ሳትገደቡ በሚቀርባችሁ በየትኛውም ማዕከል በመገኘት ተገልገሉ።
ይህ ማዕከል ተጠናቆ ስራ እንዲጀምር ያስተባበራችሁትን በሙሉ ከልብ አመሰግናለሁ ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቧቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ