Amhara people History memoirs Center

Amhara  people History memoirs Center Amhara Cultur Art History office was established in 2018. deliver service for peoples such as

የአማራ ክልል ህዝብ ዝክረ-ታሪክ ማዕከል
Amhara people Historical memoirs Center
ነባሩ ስያሜ የአማራ ክልል ህዝቦች ሰማዕታት መታሰቢያ ሀውልት ጽ/ቤት የሚለው በውስጡ ከ1973-1983 ድረስ የአስር ዓመት ሰማዕታት መታሰቢያ ብቻ ይዞ ስለነበር ስያሜውና የውስጥ ይዘቱ አይገናኙም ነበር፡፡
አዲሱ የተቋሙ ስያሜ በይዘት ደረጃ በቀጠናው ያለውን ማህበረሰብ፤ ከፍታ ላይ የደረሰ ታሪክ የነበረን (ላልይበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያን፤ የሾንኬ መንደር፤ ጎንደር ቤተ-መንግስት፤ አንኮበር ቤተ-መንግስት፤ ንጉስ ተክለሃይማኖት ቤተ-መንግስት፤ ንጉስ ሚካኤል ቤተ-መንግስትና ሌሎችንም ይዘክራል፡፡
ክልሉ የተፈጥረ ጸጋ

ባለቤት፤ (ጣና ሃይቅ፡ አባይ ወንዝ፡ ሰሜን ተራሮች ፓርክ፤ አላጣሽ ፓርክ፡ ልዩ ልዩ ፋፋቴዎች)፤ ከየክፍለ ዘመኑ ትውልድ ተሸጋሪ የሆኑ ሰራዎች ማስተማርና ስነ-ልቦናን ለተሻጋሪ ስራ ማዘጋጀት፤ ለአሸናፊነት ስነ-ልቦና መዘጋጀት የሚያነሳሱ፤ ታታሪነትና ጥበብ (ዊዝደም) ያለው ማህበረሰብ መገንባት፤ በራስ ማንነት ቋንቋ ፣ ባህል የሚሰራ ትውልድ ማነጽ፤ ለውጭ ወራሪ የማይበገር ማህበረሰብ መሆኑን ማስተላለፍና ድክመቶች ላይ አለማተኮርን ይይዛል፡፡
ስያሜውና ይዘቱ እንዲጣጣም ባለን ውስን ሙዚየም የክልላችን ህዝብ ታሪክ በጥንታዊ፡ በመካከለኛውና በዘመናዊዉ ታሪክ በማደራጀት በየዘመናቱ የታሪክ አሻራ ጥለው ያለፉት ላይ እንዲያተኩር ይደረጋል፡፡
የሥዕል ጋላሪውም በተፈጥሮ መስዕብ፤ በባህልና ኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች የሚደራጅ ይሆናል፡፡
በአጠቃላይ የአማራ ክልል ህዝብ ዝክረ-ታሪክ ማዕከል /Amhara Regional People Memoirs Cenetr/ ከበሩ ጀምሮ የክልላችን ህዝብ ታሪክ ግቢው እንዲናገር ተደርጎ ይደራጃል፡፡
ስያሜውንና ይዘቱን ለማስረጽ በኪነ-ቅርጽ፤ በመልዕክቶች፤ በንባብ ቤቶች፤ በኢንተርኔት ቴክኖሎጅ፤ በአንፊ ቲያትር፤ በስዕል ጋላሪ፤ በጋርደኖች፤ በመዝናኛ ቤቶች ማህበረሰብ መገንባትና የቱሪስት መዳረሻ ማድረግ ላይ አተኩረን እንሰራለን!
አሻራቸው ለትውልድ የሚያስተላልፉ ተመርጠው በሚሰሩ ኪነ-ቅርሶች (Sculptures) ለአብነት (ንጉስ ላልይበላ፣ አጼ ፋሲለደስ፣ የአጼ ቴዎድሮሰ፣ የአጼ ሚኒሊክ፣ እቴጌ ጣይቱ፣ ንጉስ ተክለሃይማኖት፣ ንጉስ ሚካኤል፣ ደጅአዝማች በላይ ዘለቀ፣ የዘመኑን ተጋድሎ የሚያስታውስ) ሌሎቹ በሙዚየምና በስዕል ጋላሪ ክፍሉ ይካተታሉ፡፡
የሚሰጡንን አስተያየት እንደ አስፈላጊነቱ እንጠቀምበታለን፡፡
058218 0448
058 218 458
058 2180378
0913614454
ባህር ዳር

22/04/2026
እንኳን ለበዓለ ትንሳዔው ሰላም አደረሳችሁ!አደረሰን! በትንሳኤው ሞት የተሸነፈበት፤ አዲስ ሕይወትና ደስታ የተገኘበት ነው። የትንሳዔ በዓል የነጻነትና የምስጋና በዓል ነው። መዳን የታየበት ተ...
11/04/2026

እንኳን ለበዓለ ትንሳዔው ሰላም አደረሳችሁ!አደረሰን!
በትንሳኤው ሞት የተሸነፈበት፤ አዲስ ሕይወትና ደስታ የተገኘበት ነው። የትንሳዔ በዓል የነጻነትና የምስጋና በዓል ነው።
መዳን የታየበት ተስፋ የተገለጠበት፤ ቂም የተሻረበት ፍጹም ሰላምና ታላቅ ፍቅር የተሰጠበት ነው። በዚህም ከትንሳዔው ትልቅ ጸጋ ተገኝቷል፤ ይህም ከጨለማ ወደ ብርሃን፤ ከሞት ወደ ሕይወት መሸጋገር እንደሚቻል ያስረዳናል።
ለሰው ልጅ ደህንነት ሲል ፁኑ ግፍና በደልን በፅናት ሽሮ አዳምና ዘሩን ከሞት ወደ ሕይወት ቀይሯል። የትንሳዔው ዓላማም ለሕይወት ነው። በትንሳዔው ሞት የተሸነፈው በይቅርታና በትህትና ነው።
በድጋሜ መልካም በአል ይሁንልን!

03/04/2026
03/04/2026

የአማራ ክልል መንግሥት ለ1ሺህ 224 ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ።

የአማራ ክልል መንግሥት ለ1ሺህ 224 ታራሚዎች ይቅርታ አድርጓል።

የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ምክትል ኀላፊ አያሌው አባተ (ዶ.ር) ይቅርታ የተደረገላቸውን ታራሚዎች አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸውም የይቅርታ መስፈርቱን ላሟሉ ታራሚዎች ይቅርታ ተደርጓል ብለዋል።

የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ በክልሉ የይቅርታ አሰጣጥ መስፈርትን መሠረት በማድረግ በክልሉ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች በ2018 ዓ.ም በመጀመሪያ ዙር ይቅርታ እንዲደረግላቸው ባቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ላይ የአማራ ክልል መሥተዳድር ምክር ቤት መጋቢት 18/2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ሥብሠባ ተወያይቶ መስፈርቱን ላሟሉ 1ሺህ 224 ታራሚዎች ይቅርታ እንዲደረግላቸው ውሳኔ አሳልፏል ነው ያሉት።

ታራሚዎች የይቅርታ መስፈርቱን አሟልተው በመገኘታቸው ይቅርታ የተደረገላቸው መኾናቸውን ገልጸዋል።

ይቅርታ እንዲደረግላቸው ከቀረቡ ታራሚዎች መካከል 239 ታራሚዎች የይቅርታ መስፈርቱን አሟልተው ባለመገኘታቸው የይቅርታው ተጠቃሚ አለመኾናቸውን በመግለጫቸው አንስተዋል።

ይቅርታ ከማያሰጡ ምክንያቶች መካከል የተፈጸመው የወንጀል ክብደት፣ ለተጎጅ ቤተሰብ ካሳ አለመክፈል እና ከተጎጅ ቤተሰብ ጋር እርቅ አለመፈጸም የሚሉት እንደሚገኙበት ተናግረዋል።

ከአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው የይቅርታ ተጠቃሚዎች ወደ ኅብረተሰቡ በሚቀላቀሉበት ጊዜ በልማት ሥራዎች፣ በማኅበራዊ እና በልዩ ልዩ መልካም ተግባራት ላይ መሳተፍ እና መተባበር እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: http://facebook.com/AmharaCommunications
Telegram ፡ https://t.me/amharacommunications
Twitter: https://twitter.com/Amhara_GCAO
You Tube: https://www.youtube.com/
Ticktock: https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8uQMisH1Hd7&_r=1
Website: https://www.amharacomm.gov.et

01/04/2026
01/04/2026

ሀገር የምታተርፈው ከሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር ነው።

በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሠብሣቢ ተስፋሁን አለምነህ የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተመለከተ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት ምርጫ ዜጎች የሉዓላዊ ሥልጣን ባለቤትነታቸውን የሚያረጋግጡበት መሳሪያ ነው።

የሥልጣን ምንጭ ሕዝብ እንደኾነና ይህም የሚረጋገጠው በምርጫ እንደኾነ ጠቁመዋል። ሕዝብ የፈለገውን ወደ ሥልጣን የሚያወጣበት እና ከሥልጣን የሚያወርድበት መንገድ ስለመኾኑም አብራርተዋል።

ሥልጣን በሰላማዊ መንገድ እንዲሸጋገር እና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በሕዝብ ድምጽ ተመርጦ ቅቡልነት ያገኘ መንግሥት መኖር ወሳኝ መኾኑንም አስገንዝበዋል።

ዜጎች በድምጻቸው የሚመርጡት እና ቅቡልነት ያለው መንግሥት ለዘላቂ ሰላም መደላድልን ይፈጥራል ነው ያሉት።

ፍትሐዊ፣ ተዓማኒ እና ሰላማዊ በኾነ ምርጫ የሚመጣ መንግሥታዊ ሥርዓት ዘላቂ ሰላምንም ይዞ ይመጣል ብለዋል። በሰላም እና በምርጫ ጉዳይ የጋራ ምክር ቤቱ ወጥ አቋም ወስዶ እየሠራ ስለመኾኑም አንስተዋል።

በዚህም ከመንግሥት ጋር ተቀራርቦ በጋራ እየሠራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። ችግሮች ሲፈጠሩም በጠረጴዛ ዙሪያ እንዲፈቱ እየሠራ ይገኛል ነው ያሉት።

አቶ ተስፋሁን የፖለቲካ ልዩነቶቻችንን በሠለጠነ እና በሰላማዊ መንገድ የምንፈታበት አውድ ለመፍጠር ምክር ቤቱ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መኾኑንም አመላክተዋል።

በተለይም ክልሉ በገጠመው የሰላም እጦት ወቅት የጋራ ምክር ቤቱ ትልቅ የፖለቲካ አቋም ወስዶ ችግሮችን በጠረጴዛ ዙሪያ ብቻ እንዲፈቱ ቁርጠኛ ኾኖ እየሠራ መቆየቱን ገልጸዋል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሀገርን በማሥቀደም መሥራት እንደሚገባቸው ተናግረዋል።

እኔ ብቻ አውቅልሀለሁ የሚለው አስተሳሰብ ተገቢ እንዳልኾነም አብራርተዋል። ምርጫ አያስፈልግም የሚለውን ኋላቀር አስተሳሰብ ታግሎ በማሸነፍ ቅቡልነት ያለው ምርጫ እንዲኖር ችግሮችን ተጋፍጦ ማለፍ ያስፈልጋል ብለዋል።

በትጥቅ ትግል የሚመጣ ዴሞክራሲ የለም ያሉት አቶ ተስፋሁን ሀገር የምታተርፈው ከሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር መኾኑንም አስገንዝበዋል።

ከሰላም አማራጭ ውጭ የሚካሄዱ የኃይል እንቅስቃሴዎች አውዳሚ ናቸው ብለዋል። ሀሳብ አለኝ የሚል ሁሉ ሀሳቡን ይዞ ለሕዝብ በመቅረብ የመምረጥ ዕድሉን ለሕዝብ መስጠት እንደሚገባ ነው ያብራሩት።

~•~•
🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊

"የጎርጎራ ቃልኪዳናችን፤ ለዘላቂ ሰላም እና ለሁለንተናዊ ብልጽግናችን"
•~•~•
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የፓርቲያችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ትዊተር :- twitter.com/AppAmhara?s=09
ዩቲዩብ :- youtube.com/channel/UCxQ5MOnm-YH514Qdta0Kysg
ቴሌግራም:- t.me/amharaapp
ቲክቶክ፡- tiktok.com/

Address

Bahir Dar
1561

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara people History memoirs Center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara people History memoirs Center:

Share