ANRS Bureau of Urban and Infrastructure

ANRS Bureau of Urban and Infrastructure The Bureau is Established by Proclamation No. 280/2021 Issued under the Auspices of the ANRS Council.

"በከተሞች የደቀቁና ከደረጃ በታች የሆኑ አካባቢዎችን በኮሪደር ልማቱ እንዲሻሻሉ  እየተደረገ ይገኛል"አቶ ሱለይማን እሸቱየአብክመ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ም/ቢሮ ኅላፊባለፉት አስር ወራት ...
29/05/2026

"በከተሞች የደቀቁና ከደረጃ በታች የሆኑ አካባቢዎችን በኮሪደር ልማቱ እንዲሻሻሉ እየተደረገ ይገኛል"
አቶ ሱለይማን እሸቱ
የአብክመ ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ም/ቢሮ ኅላፊ

ባለፉት አስር ወራት በክልሉ ከተሞች በኮሪደር ልማቱ 120ሄ/ር ለመሸፈን ታቅዶ የደቀቁና ከደረጃ በታች የሆኑ አካባቢዎችን 91ሄ/ር የሚጠጋ አካባቢ የማሻሻል ስራ በማከናወን የከተሞችን ገፅታ መቀየር ተችሏል።

የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ም/ቢሮ ኅላፊ አቶ ሱለይማን እሸቱ እንደገለጹት አገራዊና ክልላዊ ኢንሼቲቮችን ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ሲሆን በኮሪደር ልማቱ የመንገድ መሠረተ ልማት፣ የአረንጓዴ ልማት፣ የሕዝብ መገልገያ መሠረተ ልማትና የስማርት ከተማ ግንባታ የተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በኮሪደር ልማቱ ከ118ሺህ በላይ ዜጎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው መሆኑን የገለጹት አቶ ሱለይማን የኮሪደር ልማቱ በ35 ከተሞች እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በከተማ አስተዳደሮች፣ በክ/ከተሞችና በመሪ ማ/ቤቶች በ151 ከተሞች የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት እየተተገበረ እንደሚገኝ የገለጹት ም/ቢሮ ኀላፊዉ 281 ፕሮጀክቶች ተለይተው 96 ፕሮጀክቶች የተጠናቀቁ፣ 62 ፕሮጀክቶች ከ50% በላይ የሆኑ፣ 52 ፕሮጀክቶች ከ50% በታች አፈጻጸም ያላቸው ሲሆን 62 ፕሮጀክቶች ደግሞ በጅምርና በጨረታ ሂደት ላይና 9 ፕሮጀክቶች በተለያየ ችግር ምክንያት ወደ ስራ ያልገቡ ናቸዉ ብለዋል።

የመኖሪያ ቤት ልማት በከተሞች የሚስተዋለውን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና ለመቀነስ እንዲሁም የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ቢሮዉ ከፍተኛ ሚና ያለው መሆኑን የገለጹት አቶ ሱለይማን በክልሉ መጠነ ሰፊ የቅድመ ዝግጅትና የትግበራ ስራዎችን እያከናወነ ሲሆን ይህን የቤት ልማት ኢንሼቲቭ ከመንግስት አቅም ባሻገር የግሉን ዘርፍ፣ የልማት አጋሮችንና ማኅበራትን በማሳተፍ የቤት ልማት ስታንዳርዱ የተቀረጸ መሆኑን ገልጸዋል።

በሪልስቴት 1305 ቤቶች፣ በመኖሪያ ቤት ህ/ስ/ማኅ/ 37185 ቤቶች፣ በግለሰቦች 21783 ቤቶችና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ነዋሪዎች 1726 ቤቶች በድምሩ 62ሺህ የሚጠጉ ቤቶች ባለፉት አስር ወራት መገንባታቸውን አቶ ሱለይማን ጨምረዉ ገልጸዋል።

ዘጋቢ: ሙሉጌታ ስመኝ

ዶ/ር ሞላ መልካሙ የአብክመ ቤቶች ልማት ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ሁነው ተሰየሙ!የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ሞላ መልካሙ፣ የክልሉን የቤቶች ልማት ድርጅት በበላይነት እንዲመ...
28/05/2026

ዶ/ር ሞላ መልካሙ የአብክመ ቤቶች ልማት ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ሁነው ተሰየሙ!

የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ሞላ መልካሙ፣ የክልሉን የቤቶች ልማት ድርጅት በበላይነት እንዲመሩ የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሹመዋል።

በክልሉ የቤት ፍላጎትን ማሟላት ከፍተኛ ኃላፊነት ያለበትን ይህንን ተቋም በቦርድ ሰብሳቢነት እንዲመሩ ዶ/ር ሞላ መልካሙ መመረጣቸውን ተከትሎ፣ የቢሮው አመራሮችና ሠራተኞች የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።

የቢሮው አመራሮችና ሠራተኞች ለአዲሱ ተሰያሚ በሰጡት የመልካም ምኞት መግለጫ፤ መጪው የሥራ ዘመን የላቀ ውጤት፣ የሕዝብ ተጠቃሚነትና ስኬት የሚመዘገብበት እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።

ይህ ምደባ በአዲስ መልክ ለተዘጋጀውና በቀጣይ አመት ወደ ተግባር ምዕራፍ ለሚገባው የቤቶች ልማት ስትራቴጂ፣ ፈጣን አፈጻጸምና አዲስ መነቃቃት ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ለኮሪደር ልማት ተነሽዎች  መልሶ ማቋቋም የሚያስችል የመስሪያ ቦታ ርክክብ ተካሄደ!የጎንደር ከተማ አስተዳደር የኮሪደር ልማት ተነሽዎችን መልሶ ለማቋቋም በትኩረት እየሰራ መሆኑን በርክክብ ስነ...
27/05/2026

ለኮሪደር ልማት ተነሽዎች መልሶ ማቋቋም የሚያስችል የመስሪያ ቦታ ርክክብ ተካሄደ!

የጎንደር ከተማ አስተዳደር የኮሪደር ልማት ተነሽዎችን መልሶ ለማቋቋም በትኩረት እየሰራ መሆኑን በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ገልፀዋል።

የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ለኮሪደር ልማት ስራዎች ያበረከቱትን አስተዋፅዎ ያመሰገኑት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው የዛሬው የገቢያና የመስሪያ ቦታ ርክክብ ያደረጉ ግለሰቦች በእጣ የደረሳቸውን የመስሪያ ሽድ በአግባቡ መያዝ እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የጎንደር ከተማ መሰረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ ደግሞ በከተማዋ የሚገኙ የልማት ተነሽዎችን መልሶ ለማቋቋም በተለያዩ አማራጮች ተጠቃሚ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በከተማዋ በኮሪደር ልማት ስራ ከ4ሺ በላይ ነዋሪዎችን መልሶ ለማቋቋም የገቢያ ማዕከላት የመስሪያ ሱቆችን በመስጠት ፣በአክሲዮን በማደራጀት ወደ ስራ እንዲገቡ ለማድረግና የገቢያ ሸድ በመገንባት መልሶ ለማቋቋም እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ዛሬ ዕጣ የተጣሉት የመስሪያ ቦታ ሸዶች ከ91 ሚሊየን ብር ወጭ የተገነባ መሆኑን ተናግረዋል።

የገቢያ ሸዶቹ የትራንስፖርት ተደራሽነትንና በአካባቢው ያለውን የገቢያ እድል ታሳቢ በማድረግ የተገነባ መሆኑን ገልፀዋል።

የአዘዞ ጠዳ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወንደሰን ተስፋዬ ደግሞ ነዋሪዎች በክፍለ ከተማው ለተከናወነው የኮሪደር ልማት ላበረከቱት አስተዋፅዎ ምስጋና አቅርበዋል።

በዚህ ዙር የመስሪያ ቦታ የተሰጣቸው ተጠቃሚዎች የቅድሚያ ቅድሚያ የተሰጣቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መሆናቸውን ገልፀዋል።

ተገንብተው ለተጠቃሚዎች የተላለፉት የመስሪያ ሸዶች አሰሪው መስሪያ ቤት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማት ሲሆን ኮንትራክተሩ ደግሞ ፋሲል ኢንተርፕራይ መሆኑ ይታወቃል።

23/05/2026
በጎንደር ከተማ ተደራጅተው ቦታ  ለተወሰነላቸው 550 የመኖሪያ ቤት ህብረት  ስራ ማህበራት የመኖሪያ ቤት መስሪያ ሳይትና ብሎክ ርክክብ ስነ-ስርዓት ተካሄደ።በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙ...
23/05/2026

በጎንደር ከተማ ተደራጅተው ቦታ ለተወሰነላቸው 550 የመኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህበራት የመኖሪያ ቤት መስሪያ ሳይትና ብሎክ ርክክብ ስነ-ስርዓት ተካሄደ።

በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው የመኖሪያ ቤት ቦታ መሰጠቱ ብቻ ሳይሆን የቁጠባ ባህልን ለማሳደግና የቤት ባለቤት መሆን መስራት እንደሚገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

በቀጣይም ለተደራጁ ማህበራት የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት ከተማ አሰተዳደሩ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

በአማራ ክልል ያለውን የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ሞላ መልካሙ ገልፀዋል።

መንግስት የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ለመመለስ የገባውን ቃል እየመለሰ መሆኑን የማህበራቱ የመኖሪያ ቦታ ርክክብ ማሳያ መሆኑን ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል።

መንግስት የተለያዩ የመኖሪያ ቤት አማራጭ ፓሊሲዎችን ቀርፆ እየሰራ መሆኑን የገለፁት ቢሮ ኃፊው መሬትን በምደባ ማስተላለፍ በስፋት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

የአማራ ክልል ህብረት ስራ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ጌትነት አማረ ደግሞ መንግስት የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ጥያቄዎች ለመፍታት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ባለፉት 6 ወራት 59 ማህበራት የመኖሪያ ቤት ቦታ መውሰዳቸውን የገለፁት ኮሙሽነሩ በዛሬው ዕለት የተካሄደው የ5 መቶ 50 ማህበራት የቦታ ርክክብ ስነ-ስርዓት የሚያሳየው ከተማ አስተዳደሩ የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ማሳያ ነው ብለዋል።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር መሬት መምሪያ ኃላፊ አቶ ትዕዛዙ በፀሃ ደግሞ የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባና ከንቲባ ኮሜቴ እንዲሁም ለተግባሩ ስኬት አስተዋፅዎ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።

በጎንደር ከተማ አስተዳደር ህብረት ስራ ማህበራት ማደራጃ ጽ/ቤትአቶ ሲሳይ አዳነ ደግሞ መንግስታችን ሰው ተኮር መሆኑን ያሳየበት ተግባር ነው ያሉት ኃላፊው የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ በቅንነት ውሳኔ ለወሰኑ የከተማዋ አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል።

በዚህ ዓመት ደግሞ በመመሪያው መሰረት ከ2009 ዓም ጀምሮ ተደራጅተው ወረፋቸውን በመጠባበቅ ላይ ለነበሩ ማህበራት ከተማ አስተዳደሩ የመኖሪያ ቤት ችግሩን በመረዳት መፍትሄ በመስጠት ላይ ሲሆን በ2018 ዓም ከዛሬ 6 ወር በፊት በድምሩ ለ69 ማህበራት ቦታ ተጠንቶላቸው የካሳ ክፍያ በመክፈል ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከዚህም በተጨማሪ ወረፋቸውን በመጠባበቅ ላይ ለነበሩ 550 የመኖሪያ ቤት ማህራት በዛሬው ዕለት የሳይትና የብሎክ ርክክብ ተደርጓል ብለዋል።

በአንድ ዓመት ብቻ በድምሩ 719 የመኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማህራት ተጠቃሚ ሆነዋል ያሉት ኃላፊው በበጀት ዓመቱ 15ሺ 818 ነዋሪዎች ተጠቃሚ ሆነዋል።

የዘንድሮውን ልዩ የሚያደርገው ተዋጽኦውን የጠበቀ ሴቶችን፣አካል ጉዳተኞችን፣ ወጣቶችን፣ የሀገር ባለውለታ የሆኑትን ምልስ ወታደሮችን፤ በስራ ላይ ያሉ የመከላከያ እና ሌሎች የፀጥታ አካላትን፣የመንግስት እና የግል ትምህር ቤቶች መምህራንን ፣ የዩኒቨርስቲ መምህራን እና ሰራተኞችን፣ የሆስፒታል እና የጤና ጣቢያ የጤና ባለሙያዎችን፣ ከአረብ ሀገር ስደት ተመላሾችን፣ የሃይማት አባቶችን፣ በተለያዩ ተቋማት የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞችን ፣ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችን የተካተቱ መሆኑን አብራርተዋል።

ከ550 ማህበራት መካከል ለ26 ማህበራት በጎንደር ከተማ አስተዳደር ለሚሰሩ በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች ለሚሰሩ መምህራን ለዩኒቨርስቲ መምህራን 40 ማህበራት ለሆስፒታል እና ለሌሎች ጤና ባለሙያዎች14 ማህበራት በስራ ላይ ላሉ የመከላከያ እና ሌሎች የፀጥታ አካላት 52 ማህበራት ለምልስ ወታደሮች 64 ማህበራት መሰጠቱን ተናግረዋል።

በከተማችን ላሉ በርካታ ወጣቶች፣ ለመንግስት ሰራተኞች፣ ከአረብ አገር ስደት ተመላሾች፣ ለአካል ጉዳተኞች ለአይነ ስውራን እና ለሀይማኖት አባቶች 418 ማህበራት ናቸው፡፡

ማህበራት የተደራጁበትን ቀንና ዓ.ም ለመለየት የመስራች ቃለ ጉባኤያቸውን እና ሲደራጁ የከፈቱትን የባንክ አካውን ትና የተከፈተበትን ቀን መነሻ በማድረግ በቅደም ተከተል መሰጠቱን ተናግረዋል።

ቀሪ ማህበራት 597 በላይ አሉን ያሉት ጽ/ቤት ኃላፊው ከተማ አስተዳደሩ በከተማችን ያለውን የመኖሪያ ቤት እጥረት ግምት ውስጥ በማስገባት መፍትሄ የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።

በመጨረሻም የማህበራቱ የመኖሪያ ቤት ብታ ድልደላ የተደራጁበትን ጊዜና የቆጠቡትን ጊዜ መነሻ በማድረግ በሁለት ቀበሌዎች በተለዩ አራት ቦታዎች ላይ ድልደላ ተካሂዷል።

ክቡር ርዕሰ መስተደድር አቶ አረጋ ከበደ በክልላችን በተካሄደው የወጣቶች ድጋፍ ሰልፍ አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት‼️
22/05/2026

ክቡር ርዕሰ መስተደድር አቶ አረጋ ከበደ በክልላችን በተካሄደው የወጣቶች ድጋፍ ሰልፍ አስመልክቶ ያስተላለፉት መልዕክት‼️

በኢንዱስትሪ ፈጣን እድገት ላይ የምትገኘው ደብረ ብርሃን ከተማ፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ የሚቀረጽበትን ትምህርት ቤት ዛሬ መርቃለች። በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የከተማ ሴፍቲኔት ፕ...
22/05/2026

በኢንዱስትሪ ፈጣን እድገት ላይ የምትገኘው ደብረ ብርሃን ከተማ፣ የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ የሚቀረጽበትን ትምህርት ቤት ዛሬ መርቃለች።

በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የከተማ ሴፍቲኔት ፕሮግራም አማካኝነት ከ 82 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት የተገነባው «የምስረታ አንደኛና መካከለኛ ትምህርት ቤት» በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

ይህ ዘመናዊ የትምህርት ተቋም ከመነሻው እስከ ፍጻሜው ስኬታማ ሆኖ ለአገልግሎት እንዲበቃ፣ የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ የምግብ ዋስትናና ሴፍቲኔት ፕሮጀክት ድጋፍና የቅርብ ክትትል ማድረጉ ተገልጿል።

በምረቃው መርሃ-ግብር ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ክላስተር አስተባባሪ ክቡር ዶ/ር አሕመዲን መሐመድ፣ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ አቶ ፋንታ ደጀን፣ እንዲሁም የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በጋራ በመሆን የትምህርት ቤቱን የሪባን የመቁረጥ ሥነ-ሥርዓት አከናውነዋል።

ትምህርት ቤቱ ዘመናዊ የመማሪያ ክፍሎችንና ምቹ ሁኔታዎችን ያካተተ በመሆኑ፣ በአካባቢው ለዘመናት የነበረውን የትምህርት ቤት ተደራሽነት ጥያቄ በዘላቂነት የሚመልስና ለነዋሪው ትልቅ የምስራች ይዞ የመጣ ታላቅ ስጦታ ሆኗል።

የክቡር ርዕሰ መስተደድር  አቶ አረጋ ከበደ መልዕክት‼️
21/05/2026

የክቡር ርዕሰ መስተደድር አቶ አረጋ ከበደ መልዕክት‼️

21/05/2026
በጎንደር ከተማ በማራኪ ክፍለ ከተማ በሳሙናበር ቀበሌ ሻይ ቡና የብልፅግና የማኔፌስቶ ትውውቅ ፕሮግራም ተከናወነ።በመረሀ ግብሩ የአብክመ ከተማ ልማት ቢሮ ኋላፊክቡር ዶ/ር ሞላ መልካሙ፤ በጎን...
21/05/2026

በጎንደር ከተማ በማራኪ ክፍለ ከተማ በሳሙናበር ቀበሌ ሻይ ቡና የብልፅግና የማኔፌስቶ ትውውቅ ፕሮግራም ተከናወነ።

በመረሀ ግብሩ የአብክመ ከተማ ልማት ቢሮ ኋላፊ
ክቡር ዶ/ር ሞላ መልካሙ፤ በጎንደር ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ ፤ የመምሪያ ኃላፊዎች እንዲሁም የክ/ከተማና የቀበሌ አመራሮች ተገኝተዋል።

ጠንካራ ሀገር መንግስት ለመገንባታ የመሪዎች ሚና ወሳኝ በመሆኑ ህዝቡ ሀገርን ወደ የተሻለ ደረጃ ለማሻገር ለሀገራዊ ምርጫ ዕጩነት ለቀረቡት አባላት ትኩረት በመስጠት ሁለንትናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ትኩረት መስጠት እንዳለበት ተገልጿል።

የዘንድሮ ምርጫ ለየት የሚያደርገዉ አንድነታችን እና አብሮነታችን በሚያጠናክር ሁኔታ በቅንጅት በመስራት የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነትን እና ዘላቂ ሰላምን ለማጽናት በሚያስችል ሁኔታ በአንድ ላይ ተደምረን ወደ ስራ መግባታችን ለየት ያደርገዋል ተብሏል።

በሻይ ቡና ፕሮግራሙ የብልፅግና ፓርቲ ለ7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ ያዘጋጀውን ማኑፌስቶ እና የስንዴ ነዶ የምርጫ ምልክት ይፋ የማድረግ መርሐ ግብር የተካሄደ ሲሆን ምርጫችን ሀገርን አፅንቶ የሚያስቀጥል መሆኑን በመርሐግብሩ ተጠቁሟል።

ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገርነት ለማሸጋገር ለምናደረገው ጉዞ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ፍትሐዊ ምርጫ ማካሄድ እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን ምርጫው ቅቡልነት ፍትሐዊና አካታች እንዲሆን ሁሉም መስራት እንደሚገባ ተገልጿል።

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ANRS Bureau of Urban and Infrastructure posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share