Ethiopian Ombudsman Bahirdar Branch

Ethiopian Ombudsman Bahirdar Branch በሕግ የተደነገጉ የዜጎች መብቶችና ጥቅሞች በአስፈጻሚው አካ? አዋጅ ቁጥር 1142/2011 የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋምን እንደገና ለማቋቋም የወጣ አዋጅ፡፡

03/06/2026

ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት የሙስና ወንጀል የሚያስከትለው የህግ ተጠያቂነት

****************

ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት በተገልጋዩ ህብረተሰብ እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል ባለ ግንኙነት የሚፈጸም ተገቢነት የሌለው ተግባር ነው፡፡ ተገልጋዩ የህብረተሰብ ክፍል በህግ ክርክሮች እና በአስተዳደር አካላት የሚሰጡ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን ለማግኘት ወደ ተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ፊት ይቀርባሉ፡፡

በዚሁ ሁኔታ አገልግሎት ፈልጎ የቀረበው ተገልጋይ እንደ ጉዳዩ ባህሪ በህግ እና አሰራር በተቀመጠ ምክንያታዊ ጊዜ ውስጥ ለጉዳዩ እልባት አግኝቶ መሸኘት አለበት፡፡ ይህ የማይሆን ከሆነ ተገልጋዮችን ተገቢ ላልሆነ እንግልት በመዳረግ ጊዜያቸውን፣ ገንዘባቸውን እና ጉልበታቸውን እንዲያባክኑ በማድረግ፣ ለከፋ ምሬት እና ተስፋ በመቁረጥ በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያሻክር ይሆናል፡፡

ያለአግባብ ጉዳይ ማጓተት በሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 18 መሰረት ማንኛውም የመንግስት ወይም የህዝባዊ ድርጅት ኃላፊ ወይም ሠራተኛ በኃላፊነቱ በሥራው ምክንያት በቀረበለት ጉዳይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ጥቅም ለማግኘት ሲል በጉዳዩ ላይ ጥቅም ያለውን ማንኛውንም ሰው ለመጥቀም ወይም ለመጉዳት በማሰብ ከህግ፣ ከመመሪያ ወይም ከተለመደው አሰራር ውጪ ያለበቂ ምክንያት ጉዳዩን ያልወሰነ፣ ያዘገየ ወይም ባለጉዳይን ያጉላላ እንደሆነ እንደ ጉዳዩ ታይቶ በገንዘብ ወይም በእስራት ይቀጣል፡፡

በአዋጁ እንደተደነገገው ጉዳይን ያለአግባብ ማጓተት የሙስና ወንጀል የሆነበትን መሠረታዊ ምክንያት ነው፡፡ በዚህም መሰረት የሙስና ወንጀሎች በመሰረታዊነት የሚፈጸሙት የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለአንዱ ወገን በተለያዩ ምክንያቶች በማዳላት ሌላውን ወገን ለመጥቀም በማሰብ ነው።

የዚህ ወንጀል ፈጻሚዎች ጉዳይን አለአግባብ የማጓተት ተግባር የሚፈጽሙት ባለጉዳዩ በመመላለስ ምክንያት ከሚደርስበት እንግልት ለማምለጥ ሲል ገንዘብ እንዲከፍላቸው ተጽእኖ ለማሳደር አልያም ባለጉዳዩ ተማሮ ጉዳዩን መከታተሉን እንዲተወው በማድረግ የባለጉዳዩን መብት ለመረጡት ሌላኛው ሰው በማስተላለፍ በዚህም የሚከፈላቸውን ተገቢ ያልሆነ የገንዘብ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ ነው ማለት ይቻላል፡፡

የመንግስት መስሪያ ቤቶችም ሆኑ የልማት ድርጅቶች እንዲሁም የህዝባዊ ድርጅቶች ተገልጋዮቻቸውን ሲያስተናግዱ አገልግሎት ወይም ውሳኔ የሚሰጥበት ጉዳይ ያለውን ልዩ ባህሪ ግምት ውስጥ በማስገባት በህግ እና በአሠራር ሥርዓት እንዲሁም የተለመዱ አካባቢያዊ ሁኔታዎችን በማገናዘብ ለተገልጋዮቻቸው በተገቢው ጊዜ ውሳኔ የመስጠት ግዴታ አለባቸው፡፡

ይህ ሳይሆን ቀርቶ ያለ በቂ ምክንያት ህግ እና አሰራርን በመጣስ ተገልጋዮችን ለማንገላታት እና ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት እንዲሁም አገልግሎት ጠያቂው ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ ጉዳይን ያለበቂ ምክንያት ማጓተት በህግ የሚያስጠይቅ እና የሚያስቀጣ የሙስና ወንጀል ተግባር መሆኑን መረዳት ይገባል፡፡

ተገልጋዩ ማህበሰረብ በመንግስትም ይሁን ህዝባዊ ተቋማት አገልግሎት ለማግኘት ሲሄድ በህግ እና አሠራር ስርዓት የተቀመጡ የአሰራር ደረጃዎችን ተረድቶ በዛ ውስጥ ውሳኔ እንዲያገኝ መጠየቅ እና ይህ በማይሆንበት ጊዜ ጉዳዩን ያለ በቂ ምክንያት የሚያጓትቱ የመንግስት እና ህዝባዊ ድርጅት ሠራተኞች እና ኃላፊዎች ላይ የህግ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው አካላት በመጠቆም ተባባሪ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

ትውልድን በሥነምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!

የሙስና ወንጀል መጠቆሚያ አማራጮችን፣ ወቅታዊ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት👇🏾

ሞባይል መተግበሪያ

ስልክ ተጠቃሚዎች
https://play.google.com/store/apps/details...

or iPhone ስልክ ተጠቃሚዎች
https://apps.apple.com/us/app/ncrs/id659366231

ለሀብት ማሳወቅና ምዝገባ፦ https://feaccears.gov.et/

ዌብሳይት፦ https://www.feacc.gov.et

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/feaccOfficial/

ቴሌግራም፦ https://t.me/feacc

ዩትዩብ፡- https://www.youtube.com/-corrupti149

ትዊተር፦ https://twitter.com/EthiopiaFeacc በመወዳጀት ይከታተሉን።

21/05/2026
21/05/2026

☞ በተቋማት ውስጥ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የሚያግዙ ስልቶች

☞ የፋይናንስ እና የአስተዳደር ሂደቶችን ግልጽ ማድረግ፤
☞ ውሳኔዎችን ለሕዝብ እና ለሠራተኞች በግልጽ ማቅረብ፤
☞ የግዥ ሂደቶችን በክፍት ውድድር ማካሄድ፤
☞ ህግን በእኩል መተግበር፤
☞ ተጠያቂነትን ማጠናከር፤
☞ ጠንካራ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓትን መዘርጋት፤
☞ የሰራተኞችን ስነ-ምግባር ማሻሻል፤
☞ የገንዘብ እና የንብረት አጠቃቀምን ግልፅ ማድረግ፤
☞ የህዝብ ተሳትፎን ማበረታታት ፤
☞ ጥቆማ ሰጪዎችን ማበረታታት፤
☞ ቴክኖሎጂን በመጠቀም አሰራርን ማዘመን፤
☞ በየጊዜው ኦዲት እና ክትትል ማድረግ፤

በአንድ ማዕከል አገልግሎት እና በመረጃ መብት         መካከል ያለው ትስስር...........06/09/2018.........በአንድ ማዕከል አገልግሎት እና በመረጃ መብት መካከል ያለው ትስ...
14/05/2026

በአንድ ማዕከል አገልግሎት እና በመረጃ መብት
መካከል ያለው ትስስር
...........06/09/2018.........

በአንድ ማዕከል አገልግሎት እና በመረጃ መብት መካከል ያለው ትስስር የሚጀምረው "የመረጃ መበታተን" (Information Fragmentation) ከሚፈጥረው እንግልት እንደሆነ ብዙዎች ይመሰክራሉ። በአብዛኛው የመንግስት መዋቅር ውስጥ መረጃዎች በተለያዩ መሥሪያ ቤቶችና ኤጀንሲዎች ስር የተቆለፉ ናቸው። ዜጋው መረጃን ለማግኘት እያንዳንዱን ተቋም በተናጠል መጠየቅ አለበት ማለት ነው።

የአንድ ማዕከል አገልግሎት (እንደ መሶብ ያሉ አሰራሮች) ሲዘረጉ ግን ይህንን መበታተን ያስቀራሉ ተብሎ ይታሰባል። መረጃን የማማከል (Centralization) እና ለተጠቃሚው የማቅረብ (Decentralization of Access) ሚና ይጫወታሉ ብሎ መናገር ይቻላል። የአንድ ማዕከል አሰራር የመረጃ መብት ህጉ በተግባር እንዲተረጎም ምቹ "መድረክ" (Platform) ሆኖ ያገለግላል ተብሎ ይታባል። እናንተስ ምን ታስባላችሁ?

የመረጃ የማግኘት መብት (Right to Access Information) ፅንሰ-ሃሳብ..........06/09/2018...........እንደሚታወቀው የመረጃ የማግኘት መብት በዲሞክራሲያዊ አስተዳ...
14/05/2026

የመረጃ የማግኘት መብት
(Right to Access Information) ፅንሰ-ሃሳብ
..........06/09/2018...........

እንደሚታወቀው የመረጃ የማግኘት መብት በዲሞክራሲያዊ አስተዳደር ውስጥ "ኦክስጅን" ተብሎ ይጠቀሳል (Mendel, 2008)። በታሪካዊ አመጣጡ መረጃ የማግኘት መብት ከሃሳብን በነጻነት ከመግለጽ መብት (Freedom of Expression) ጋር በቅርቡ የተሳሰረ ቢሆንም፣ ባለፉት አርባ አመታት ግን ራሱን የቻለ "የመጠየቅ መብት" (Right to Know) ሆኖ ሊጎለብት ችሏል።

እንደ ንድፈ-ሃሳቡ እሳቤ፣ በመንግስት እጅ የሚገኝ መረጃ ሁሉ ባለቤቱ ህዝብ ነው፤ መንግስት የመረጃው "ባለአደራ" (Trustee) እንጂ "ባለቤት" አይደለምብሎ መናገር ይቻላል (Stiglitz, 2002)። በመሆኑም መረጃን ለዜጎች ግልጽ ማድረግ የመንግስት የበጎ ፈቃድ ስጦታ ሳይሆን ህጋዊና ሰብአዊ ግዴታው ነው ማለት ነው።

ከዚህ አንጻር መረጃ የማግኘት መብት ለሶስት ዋና ዋና ምሰሶዎች መከበር ወሳኝ ሚና እንዳለው ይታመናል፡፡

1. ለተጠያቂነት (Accountability)፦ ዜጎች የመንግስትን አሰራር እና የህዝብ ሀብት አጠቃቀም መቆጣጠር የሚችሉት መረጃ ሲኖራቸው ብቻ ነው።
2. ለግልጽነት (Transparency)፦ ሚስጥራዊነትን በመስበር በሙስና ላይ የብርሃን ጨረር ይፈነጥቃል።
3. ለዜጎች ተሳትፎ (Public Participation)፦ መረጃ የሌለው ማህበረሰብ ትርጉም
ያለው የፖለቲካም ሆነ የኢኮኖሚ ውሳኔ ላይ መሳተፍ አይችልም።

ስናጠቃልለው ባህላዊው ቢሮክራሲ መረጃን እንደ "ጉልበት እና ስልጣን" (Information as Power) የሚመለከተው ሲሆን የመንግስት ሰራተኞች መረጃን በቆለፉ ቁጥር ተሰሚነታቸው የሚጨምር ይመስላቸዋል። ይህ "የሚስጥራዊነት ባህል" (Culture of Secrecy) የመረጃ ነጻነት አዋጆችን ውጤታማነት ከሚያደናቅፉ ትልልቅ ስነ-ልቦናዊ ተግዳሮቶች አንዱ ነው ተብሎ ይታሰባል።

© ህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን

14/05/2026
11/05/2026

መልካም አስተዳደር በተለያዩ ተቋማት ምልከታ

……03/09/2018…….

መልካም አስተዳደር (Good Governance) የሚለው ጽንሰ-ሀሳብ እንደ ተቋማቱ ዓላማና ግብ የተለያየ ትኩረትና ትርጓሜ ይሰጠዋል፡፡ ይሁን እንጂ ሁሉም ተቋማት የሚስማሙባቸው መሰረታዊ የሆኑ የጋራ እሴቶች ይኖራሉ፡፡

የተለያዩ ተቋማት የሚሰጡትን ትርጓሜና ትኩረት በሚከተለው መልኩ ማየት ይቻላል፡-

1. የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP)

UNDP ለመልካም አስተዳደር ሰፊና ሁሉን አቀፍ ትርጓሜ ይሰጣል፡፡ ለእነርሱ መልካም አስተዳደር ማለት "በሁሉም ደረጃዎች የአንድን ሀገር ጉዳዮች ለማስተዳደር ስልጣን የሚተገበርበት መንገድ" ነው በማለት ይተረጉመዋል፡፡
በዚህም UNDP ስምንት መሰረታዊ ባህሪያትን ያስቀምጣል፡-
• ተሳትፎ (Participation): ወንዶችም ሆኑ ሴቶች በውሳኔ አሰጣጥ ላይ ያላቸው ድምፅ።
• የህግ የበላይነት (Rule of Law): የህግ ማዕቀፎች ፍትሃዊ መሆንና ያለ አድልዎ መተግበር።
• ግልጽነት (Transparency): መረጃዎች ለሚመለከታቸው ሁሉ ተደራሽ መሆን።
• ምላሽ ሰጪነት (Responsiveness): ተቋማት ለባለድርሻ አካላት በተገቢው ጊዜ ምላሽ መስጠት።
• ስምምነትን መፈለግ (Consensus Orientation): የህብረተሰቡን ሰፊ ፍላጎት መሰረት ያደረገ መግባባት መፍጠር።
• ፍትሃዊነትና አካታችነት (Equity and Inclusiveness): ሁሉም ዜጎች በህብረተሰቡ ውስጥ እኩል ድርሻ እንዳላቸው እንዲሰማቸው ማድረግ።
• ውጤታማነትና ብቃት (Effectiveness and Efficiency): ሃብትን በአግባቡ በመጠቀም የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ።
• ተጠያቂነት (Accountability): የመንግስት፣ የግል ዘርፍና የሲቪል ማህበራት ለህዝብና ለባለድርሻ አካላት ተጠያቂ መሆን።

2. የዓለም ባንክ (World Bank)

የዓለም ባንክ ትርጓሜ በዋናነት ከኢኮኖሚ እድገትና ከልማት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ባንኩ መልካም አስተዳደርን "ለልማት ሲባል የአንድን ሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሃብቶች ለማስተዳደር ስልጣን የሚተገበርበት መንገድ" ሲል ይገልጸዋል፡፡
ትኩረቱም በሦስት ዋና ዋና ነጥቦች ላይ ነው፡-
1. የፖለቲካ ሥርዓቱ ዓይነት።
2. ለልማት ሲባል ሃብትን የማስተዳደር ሂደትና አቅም።
3. ፖሊሲዎችን የመቅረጽና ተግባራዊ የማድረግ አቅም።

3. ዓለምአቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF)

IMF ለመልካም አስተዳደር የሚሰጠው ትርጓሜ ጠበብ ያለና ከማክሮ ኢኮኖሚ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ትኩረቱ የሚከተሉት ላይ ነው፡-
• የመንግስት የፋይናንስ አያያዝ ግልጽነት።
• የማዕከላዊ ባንክ ነጻነትና ብቃት።
• ሙስናን መዋጋትና ግልጽ የሆኑ የንግድ ህጎችን ማስፈን።

4. ሲቪል ማህበራትና ግለሰቦች

የተለያዩ ማህበራትና ምሁራን እንደየቆሙለት ዓላማ ትርጓሜ ይሰጣሉ፡-
• የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፡ መልካም አስተዳደርን ከሰብዓዊ መብቶች መከበርና ከዲሞክራሲያዊ ተሳትፎ ጋር በጥብቅ ያገናኙታል፡፡
• የግል ዘርፉ (Business Sector): ለእነርሱ መልካም አስተዳደር ማለት ቢሮክራሲ የቀለለበት፣ ሙስና የሌለበትና ግልጽ የሆኑ የንግድ ህጎች ያሉበት አካባቢ ማለት ነው፡፡
• የአካባቢ ጥበቃ ተሟጋቾች፡ የወደፊቱን ትውልድ ጥቅም ግምት ውስጥ ያስገባ የሀብት አጠቃቀምን (Sustainability) እንደ አንድ የመልካም አስተዳደር መለኪያ ያዩታል፡፡

ስናጠቃልለው ምንም እንኳን ትርጓሜዎቹ ቢለያዩም፣ የመልካም አስተዳደር ማጠንጠኛው ተጠያቂነት፣ ግልጽነት፣ የህግ የበላይነትና የህዝብ ተሳትፎ ናቸው፡፡ እነዚህ እሴቶች ሲሟሉ ተቋማት ለዜጎች የሚሰጡት አገልግሎት ጥራት ይጨምራል፣ ፍትሃዊነትም ይሰፍናል ተብሎ ይታመናል፡፡

09/05/2026

Ahadu TV / አሐዱ ቴሌቪዥን's Post
Ahadu TV / አሐዱ ቴሌቪዥን
April 23 at 5:30 PM
·
መረጃ በማይሰጡ ኃላፊዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ የሚያስችል ሕግ ተዘጋጀ
አዲሱ የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ የግል ተቋማት ጭምር መረጃ እንዲሰጡ የሚያስገድድ አንቀጽ በማካተት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል።
ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. (አሐዱ ሬዲዮ) - የመገናኛ ብዙሃን እና የመረጃ ነፃነት የየራሳቸው ባህሪ ቢኖራቸውም እስካሁን የመገናኛ ብዙሃን እና መረጃ ነፃነት አዋጅ ቁጥር 590/2000 በሚል በአንድ ላይ ተጣምረው ቆይተዋል።
ይህ ደግሞ ግልጽ የአሰራር ስርዓት እንዳይዘረጋ ማድረጉን የተናገሩት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ፤ የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ ለብቻው ተረቅቆ መቅረቡን ገልጸዋል።
ሰባት ክፍሎች እና 60 አንቀጾችን የያዘው ይህ የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ ፤ በዋናነት አዋጁን የማስፈጸም ሙሉ ስልጣን ለኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ይሰጣል። ማንኛውም ዜጋ መረጃ በሚጠይቅበት ወቅት መረጃ በማይሰጡ ኃላፊዎች ላይ ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑም ተገልጿል።
ረቂቅ አዋጁ የመንግስት ተቋማትን ብቻ ሳይሆን ከህዝብ አገልግሎት ጋር በቀጥታ የሚገናኙ የግል ድርጅቶችንም ጭምር መረጃ እንዲሰጡ የሚያስገድድ አንቀጽ ማካተቱ በጥንካሬ ተነስቷል። ይህም ጥሩ ድንጋጌ መሆኑን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ረቂቅ አዋጁ ይፋ የማይደረጉ መረጃዎች በማለት በአንቀጽ 18 ላይ በዝርዝር ያስቀመጠው ድንጋጌ የክርክር መነሻ ሆኗል። በዚህም መሰረት የመከላከያ እና የሀገር ደህንነት መረጃዎች ፣ የፍርድ ቤት ምርመራ ሂደቶች እና የድርጅት ሚስጥሮች የህግ ጥበቃ እንደሚያገኙና ይፋ እንደማይደረጉ ይገልጻል።
የምክር ቤት አባሉ ዶ/ር ደሳለኝ ይህ አንቀጽ ለተለያየ ትርጉም የተጋለጠ በመሆኑ እና ለብልሹ አሰራር ምቹ ሁኔታ ሊፈጥር ስለሚችል በዝርዝር እንዲታይ ምክረ ሃሳብ አቅርበዋል።
አሐዱ በረቂቅ አዋጁ ዙሪያ ሙያዊ ማብራሪያ እንዲሰጡበት ጠበቃ እና የህግ አማካሪ የሆኑት አቶ ዳንኤል ፍቃዱን አነጋግሯል። የህግ ባለሙያው የረቂቅ አዋጁ ዋነኛ አላማ ሁለቱን አዋጆች መለያየት መሆኑን አብራርተዋል።
በአዋጁ ከተካተቱ መሰረታዊ ድንጋጌዎች መካከል የመንግስት ኃላፊዎች ተጠያቂ የሚሆኑበት እና መረጃ የሚሰጡበት ጊዜ ገደብ መወሰኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ጋዜጠኞች ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዳይታሰሩ የሚያግድ ድንጋጌ መካተቱንም ገልጸዋል።
አዋጁን የማስፈጸም ስልጣን ለህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም መሰጠቱን የገለጹት የህግ ባለሙያው ትችት በቀረበበት የደህንነት መረጃዎች አያያዝ ዙሪያም አስተያየታቸውን ሲሰጡ አዋጁ ወደ ፊት ሲጸድቅ የትኛው መረጃ በሚስጥርነት እንደሚፈረጅ ግልጽና በማያሻማ መንገድ ሊቀመጥ ይገባል ብለዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይህንን መረጃ የመጠየቅ ፣ የማግኘት እና የማስተላለፍ ጉዳዮችን የሚመለከተውን የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 10/2018 ሆኖ ለተጨማሪ ምርመራ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ/ም ለዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መምራቱ ይታወሳል።
በፋሲል አረጋይ

08/05/2026

የሕዝብን አደራ በአግባቡ የመወጣት ጥበብ ሊኖር ይገባል።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

የሕዝብን አደራ መሸከም ትልቅ ክብር እንደሆነ ሁሉ፣ ያንን አደራ በአግባቡ መወጣት ደግሞ ጥበብንና የፀና የሥነ ምግባር ቁመናን ይጠይቃል።

ኃላፊነትን እንደ ሹመት ወይም እንደ ሥልጣን ሳይሆን እንደ አገልግሎት ማየት የመጀመሪያው ጥበብ ነው። "መሪ ማለት የሕዝብ አገልጋይ ነው" የሚለውን መርህ በመያዝ፣ ከግል ጥቅም ይልቅ የጋራ ጥቅምን ማስቀደም አደራን ለመጠበቅ ይረዳል።

አደራን መወጣት የሚቻለው አሰራርን ግልጽ በማድረግ ነው። ውሳኔዎች እንዴትና ለምን እንደተወሰኑ ለሕዝብ ግልጽ መሆን አለባቸው። ይህም ጥርጣሬን ያስወግዳል። ለሚሰሩ ስህተቶች ኃላፊነት መውሰድ እና ለማስተካከል ዝግጁ መሆን የሕዝብን እምነት ያተርፋል።

የሕዝብ አደራ ከግል ስሜት ወይም ከዘመድ አዝማድ ትስስር በላይ ነው። ሁሉንም ሰው በሕግ ፊት እኩል ማየት እና የአሰራር ስርዓቶችን በጥብቅ መከተል ከሙስና እና ከአድልዎ ይጠብቃል።

ዘመናዊ አሰራሮችን እና ዲጂታል መሣሪያዎችን መጠቀም አገልግሎትን ያቀልጣል። አሰራሮች በቴክኖሎጂ ሲታገዙ የሰዎች ንክኪ ስለሚቀንስ፣ ለአላስፈላጊ መጉላላትና ለሙስና የሚጋለጡ ቀዳዳዎች ይደፈናሉ። ይህም አደራን በታማኝነት ለመወጣት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል።

"የሕዝብ አደራ የክብር ሸክም ነው፤ በቅንነት ስንሸከመው ለሀገር ኩራት፣ ለራስ ደስታ ይሆናል!"

08/05/2026

ርኅራኄን መሠረት ያደረገ አገልግሎት
(Compassionate Service)

30/08/2018

Address

0947111122
Bahir Dar
1957

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Ombudsman Bahirdar Branch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Ombudsman Bahirdar Branch:

Share