02/02/2023
የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ 1ኛ መደበኛ ጉባኤ የውሳኔ አቅጣጫዎች ዙሪያ ከበየዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አባላት ጋር ውይይት እያካሔደ ነው ።
ጥር 24/2015 ዓ.ም
ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ ብልጽግና የሚተጋ ወጣት እንፍጠር በሚል መሪ ቃል በበየዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አባላት በ1ኛው የወጣቶች ሊግ መደበኛ ጉባኤ የውሳኔ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት እያካሔደ ነው ።
በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የበየዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስማማው ሃብቴ እንደገለጹት ወጣቶች የሚያገኙትን እድል ወደ ድል በመቀየር ለሀገር ዘላቂ የሆነ እድገት፣ ሰላምና ብልጽግና እንዲመጣ የበኩላቸውን ድርሻ መወጣት ይጠበቅባቸዋል ብለው
የበቃ ወጣት እንዲፈጠር እና ጠንካራ የሆነ የሊግ መዋቅር እንዲኖረን ከተፈለገ በብዛትም በጥራትም እስከ ቀበሌና ድረስ አባላትን የማጠናከር ስራ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
የውይይቱን ሰነድ ያቀረበው የበየዳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ኃላፊ የሆነው ወጣት ተስፋኢየሱስ ወርቄ ቅድመ ጉባኤና ድህረ ጉባኤው ላይ የወሰናቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በቀጣይነት ሊጉ ከጉባኤ እስከ ጉባኤ ወስኗል በዚህም:-
የጠንካራ መዋቅር ግንባታ፣ ለዘላቂ ሰላም እና ሀገራዊ አንድነትን ማጠናከር ሚናው የጎላ አደረጃጀት መሆን፣ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ላይ የጎላ ሚና መጫዎት የሚችል ተቋም መገንባት፣ የወጣቱን ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችል ተቋም መፍጠር፣ የኢትዮጵያን ሀገር መንግስት የሚያጎለብቱ፣ ህብረ
ብሄራዊ አንድነትና ወንድማማችነትን የሚቀርጹ ተግባራትን መንደፍና እና የወጣቶችን አህጉራዊና አለም አቀፍ ተሳትፎና ሚና ማሳደግ የሚሉ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ በዝርዝር አብራርተዋል።
ወጣት ተስፋኢየሱስ አያይዘውም በጉባኤ ውሳኔዎቻችን ላይ የተቀመጡ ውሳኔዎች አዳዲስ ፈጠራን በመጨመር መተግበርና ለመዋቅራችን መጠናከር ወሳኝ ነው ብለዋል ፡፡