Amhara Region Police

Amhara Region Police law enforcement organization

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በአማራ ክልል በስኬትና  በታላቅ ድል መጠናቀቁ ተገለጸ።በአማራ ክልል በሁሉም አካባቢዎች የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በከፍተኛ ስኬት ስልጡን እና ህዝባዊ ተሳትፎ በጎላ...
02/06/2026

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በአማራ ክልል በስኬትና በታላቅ ድል መጠናቀቁ ተገለጸ።

በአማራ ክልል በሁሉም አካባቢዎች የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በከፍተኛ ስኬት ስልጡን እና ህዝባዊ ተሳትፎ በጎላበት መልክ በታላቅ የህዝብ ድል መጠናቀቁን የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ተወዳዳሪ የሌለው ሚና ለተጫወቱት የክልሉ ፖሊስ፣ ለጀግናዉ የመከላከያ፣ የፌደራል ፀጥታና የብሔራዊ ደህንነት አካላት ፣ለክልሉ ሚሊሻና ሰላም አስከባሪ እና ለመላዉ ህዝባችን በሙሉ የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ የላቀ ምስጋናና እውቅና አቅርቧል።

ሁሌም ሰላምና ልማትን ቀዳሚ የሚያደርገው የክልሉ ህዝብ የምርጫ ካርድ ከመውሰድ ጀምሮ በምርጫው ዕለት በታላቅ ትዕግስት እና ስነ-ስርዓት ድምፅ እስከመስጠት ድረስ ያሳየው ፍቅርና ሀገር ወዳድነት የታሪክ ማህደር የማይረሳው መሆኑን ገልጿል።

በምርጫው ዕለት ህብረተሰቡ ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በነቂስ በመውጣት በክልሉ በሚገኙ የምርጫ ክልሎች ያከናወነው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ያለምንም መሰላቸት እስከ ምሽት ሰአት መከናወኑን አረጋግጧል።

ህብረተሰቡ ረጅም ሰልፎችን በታጋሽነት በመሰለፍ፣ የመምረጥ መብቱን በአግባቡ መጠቀሙ የሰለጠነ ዴሞክራሲያዊ ባህሉን ያሳየበትና ለምርጫው ስኬታማነት ትልቁን ድርሻ ያበረከተበት መሆኑንም ጠቁሟል።

ምርጫው የክልሉን ህዝብ ብስለት፣ ሰላም ወዳድነት እና ለሀገር ግንባታ ያለውን ቁርጠኝነት ዳግም ለዓለም ያስመሰከረበት ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑንም ዋና ጠቅላይ መምሪያው አመላክቷል።

ሀገራዊ ምርጫው በስኬት ሆኖ እንዲጠናቀቅ ሌት ከቀን የህግ ማስከበር ስራቸውን በብቃት ለተወጡት ለክልሉ ፖሊስ አባላት፣ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ለፌዴራል ፖሊስ፣ለብሔራዊ ደህንነት አካላት፣ለክልሉ ሚሊሻና ሰላም አስከባሪ አካላት በሙሉ ታላቅ አክብሮትና እውቅና ሰጥቷል።

የጸጥታ ኃይሉ ሂደቱን በበላይነት በመምራትና የእያንዳንዱን አካባቢ ህብረተሰብ በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ በማንቀሳቀስ፣ ከህዝብ የተውጣጡ የሰላም ኮሚቴዎችንና አደረጃጀቶችን ከራሱ የጸጥታ መዋቅር ጋር በማስተሳሰር የጋራ የሰላም ግንባር መፍጠር በመቻሉ ሰላሙን ማረጋገጥ መቻሉንም አረጋግጧል።

ይህንን ስራ ስኬታማ ለማድረግ የጸጥታ ኃይሉ አባላት ሌት ከቀን ያሳዩት ከፍተኛ ልፋት፣ ድካም እና ተጋድሎ በአንዳንድ ቦታዎች የምርጫውን ሂደት ለማደፍረስና ሁከት ለመፍጠር አልመው የተንቀሳቀሱ ህገ-ወጥ አካላትን የጥፋት ሴራ ቀድሞ በተዘጋጀ ስልታዊ የመከላከል እቅድ ሙሉ በሙሉ ማክሸፍ መቻሉንም አመላክቷል ።

የጸጥታ ኃይሉ የተጣለበትን ታሪካዊ አደራ የመወጣት ጀግንነት፣ ሙያዊ ብቃት እና የገባውን ቃልኪዳን በታማኝነት በመፈጸም የህዝቡን ደህንነት በልዩ ጥንቃቄ የማስጠበቅ ስራ፤ ከተቋማዊ ኩራት ባሻገር ለክልሉና ለሀገሪቱ ታላቅ ክብርን ያጎናጸፈ ተግባር በመሆኑ ላቅ ያለ ምስጋናና እውቅና ሰጥቷል።

ምርጫውን ለማወክ የሞከሩ ማናቸውንም የፀረ-ሰላም ኃይሎች የጥፋት አጀንዳ ሙሉ በሙሉ ያከሸፈ ታላቅ የህዝብ ድል የተመዘገበው ህዝቡ ያሳየው አስተዋይነት እና የሰላም ባለቤትነት ስሜት በመኖሩ እንደሆነም አክሏል።

ለታሪካዊ ድሉ መገኘት ህዝቡ ከጸጥታ ኃይሉ ጎን በመቆም፣ መረጃዎችን በወቅቱ በመለዋወጥ እና ለሰላም ጥበቃው ግንባር ቀደም ጠባቂ በመሆን ያሳየው ጠንካራና የተቀናጀ ጥምረት ዋነኛ መሠረት ነበር ተብሏል።

በምርጫው ወቅት የታየውን መልካም የህዝብና የፖሊስ ቅንጅታዊ አሰራርና አደረጃጀት ይበልጥ በማጠናከር የክልሉን ዘላቂ ሰላምና ልማት ለማረጋገጥ የክልሉ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ቀጣይም በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቋል።

ምርጫው በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ለሲቪክ ማህበራት፣ ለብዙሃን መገናኛ አካላት ፣ ለዉጭና የአገር ዉስጥ ታዛቢዎች እና ለሰላም ወዳዱ ማህበረሰብ በሙሉ በድጋሚ የላቀ ምስጋና በማቅረብ፤ የተጀመረውን የሰላምና የዴሞክራሲ ጉዞ በጋራ ለማስቀጠል የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ጥሪ አስተላልፏል።

የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ
ግንቦት 25/2018 ዓ.ም
ባህር ዳር

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የጸጥታ ሁኔታን በተደራጀ መንገድ በማዕከላዊ መቆጣጠሪያ ክፍል ክትትል እየተደረገ ይገኛል።ኮሚሽነር ጀኔራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) እና የዋና ጠቅላይ መምሪያው ማኔጅመ...
01/06/2026

የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የጸጥታ ሁኔታን በተደራጀ መንገድ በማዕከላዊ መቆጣጠሪያ ክፍል ክትትል እየተደረገ ይገኛል።

ኮሚሽነር ጀኔራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) እና የዋና ጠቅላይ መምሪያው ማኔጅመንት እና የሚመለከታቸው አመራሮች የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የፓትሮል እና የደኅንነት ሁኔታ በቀጥታ እየተከታተሉ ነው።

የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጀኔራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) እና የዋና ጠቅላይ መምሪያው ከፍተኛ ማኔጅመንት አባላት በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለውን የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሰላም እና የደኅንነት ሁኔታ ከቁጥጥር ክፍል (Command Room) ሆነው በቀጥታ እየተከታተሉ ይገኛሉ።

አሁን ላይ ከመቆጣጠሪያ ክፍሉ ከሚደረገው ቀጥታ ክትትል መረዳት እንደሚቻለው በሁሉም አካባቢዎች የምርጫው ሂደት በሰላማዊ እና በተረጋጋ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የምርጫው ሂደት ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ጀግናው የሀገር መከላከለያ ሰራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ፣ የደህንነት ተቋማት እና የክልሉ አድማ መከላከል እና የመደበኛ ፖሊስ ሰራዊት እንዲሁም የክልሉ የጸጥታ ኃይል ማናቸውንም የጸጥታ ስጋቶች አስቀድሞ ለመከላከል ቁጥጥሩንና ፈጣን ምላሽ የመስጠት ስራውን አጠናክሮ ማስቀጠሉ ታውቋል።

በአማራ ክልል  የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ  ድምጽ  የመስጠት ሂደት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ቀጥሏልበአማራ ክልል በዛሬው ዕለት እየተካሄደ የሚገኘው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሁሉም አካባቢዎች ፍጹ...
01/06/2026

በአማራ ክልል የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምጽ የመስጠት ሂደት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ቀጥሏል

በአማራ ክልል በዛሬው ዕለት እየተካሄደ የሚገኘው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሁሉም አካባቢዎች ፍጹም ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ስነ-ስርዓትን በተከተለ መልኩ ቀጥሏል።ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊችም በየምርጫ ጣቢያዎቹ በመገኘት ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።

የኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ በባህርዳር ከተማ ምርጫ ክልል፣ የኢፌድሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር በጎንደር ከተማ ምርጫ ክልል ፣ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር) በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቡ የምርጫ ክልል ፣የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ክብርት ፋንቱ ተስፋዬ በኮምፖልቻ ምርጫ ክልል እንዲሁም ቁጥራቸው የበዛ መራጮች በማለዳው በየምርጫ ጣቢያዎቹ በመገኘት በመሰለፍ ድምፃቸውን በነፃነትና በታላቅ የሀገራዊ ኃላፊነት ስሜት እየሰጡ ይገኛሉ።

ህዝቡ ያለምንም የፀጥታ ስጋት በነፃነትና በሉዓላዊነት ስሜት መብቱን እየተጠቀመ በመሆኑ የክልሉን አስተማማኝ ሰላምና የህዝቡን ከፍተኛ የዴሞክራሲ ባህል ማሳያ ነው።

የአማራ ክልል በከፍተኛ መነሳሳትና በነቂስ ወጥቶ የሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ  ድምጹን  እየሰጠ ይገኛል ።በአማራ ክልል በሚገኘው በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች በሚገኘው በ130 ምርጫ ክልል ህብረተሰ...
01/06/2026

የአማራ ክልል በከፍተኛ መነሳሳትና በነቂስ ወጥቶ የሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምጹን እየሰጠ ይገኛል ።

በአማራ ክልል በሚገኘው በሁሉም ዞኖችና ወረዳዎች በሚገኘው በ130 ምርጫ ክልል ህብረተሰቡ ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎቹ በመገኘት 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ በከፍተኛ መነሳሳት እያካሄደ ይገኛል።

በአሁኑ ሰዓት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንፈስ ድምጹን የመስጠት መብቱን እየተጠቀመ ይገኛል።

ይህ ታሪካዊ የምርጫ ሂደት በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ያለምንም የጸጥታ እንቅፋትና በከፍተኛ ሰላማዊነት እየተከናወነ መሆኑ፣ የህብረተሰቡን የነቃ ተሳትፎና የመላዉ የጸጥታ መዋቅሩን ዝግጁነት የሚያሳይ ነው።

30/05/2026

"የጸጥታ መዋቅራችን የጥፋት ኃይሎችን የመግታት ሙሉ አቅም ስላለው ህብረተሰቡ በምርጫው ዕለት ያለምንም ስጋት ወጥቶ መምረጥ ይኖርበታል!" ኮሚሽነር ጀኔራል ዘላለም መንግስቴ ( ዶ/ር)

30/05/2026

"ህብረተሰቡ የጸጥታ ስጋቶችን ሲመለከት በተለመደው የስልክ መስመር ከመጠቆም ባለፈ፣ በአዲሱ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFP app) አማካኝነት በጽሑፍ፣ በምስልና በድምጽ ፈጣን ጥቆማ በመስጠት ሰላሙን በጋራ መጠበቅ ይኖርበታል!"
ኮሚሽነር ጀኔራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር) የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ

30/05/2026

"ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍጹም በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ የክልሉ ፖሊሰ ከጀግናዉ መከላከያ፣ ከፌደራል ፖሊስ፣ የደህንነት አካላትና ሌሎች ከክልላችን የፀጥታ ሀይሎች ጋር በመቀናጀት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በተሟላ ዝግጅትና ቁመና ላይ ይገኛል!" የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ዘላለም መንግስቴ (ዶ/ር)

ፖሊስ ምርጫው  በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም የጸጥታ ኃይሉ በከፍተኛ ዝግጁነት ወደ ተግባር መግባቱ ተገለጸ። 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም በአማራ ክልል የሚገኘው የጸጥታ ኃይል በ...
29/05/2026

ፖሊስ ምርጫው በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም የጸጥታ ኃይሉ በከፍተኛ ዝግጁነት ወደ ተግባር መግባቱ ተገለጸ።

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ እንዲፈፀም በአማራ ክልል የሚገኘው የጸጥታ ኃይል በሰው ኃይልና በሎጀስቲክስ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ተግባር መግባቱ ታወቀ።

የክልሉ የፖሊስ ኃይል ከመከላከያ፣ ከፌዴራልና ከሌሎች የክልሉ የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት፤ በየመንገዱ፣ በየኬላውና በየሰፈሩ በቂ የሰው ኃይል በማሰማራት ቀንና ሌሊት በትጋት እየሰራ ይገኛል።

የትራፊክ ፖሊስን ጨምሮ መላው የጸጥታ አካል የትራንስፖርት እንቅስቃሴው የተሳለጠ እንዲሆንና የሕዝቡ መደበኛ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ እንዳይስተጓጎል በየተሰማራበት ቦታ ውጤታማ ሥራ እያከናወነ መሆኑ ተረጋግጧል።

ሕገ-ወጥ የታጠቁ ኃይሎች በሕዝቡ ላይ ውዥንብር ለመፍጠርና እንቅስቃሴን ለማደናቀፍ የሚያስተላልፉት መረጃ መሬት ላይ የሌለና ፍጹም የሐሰት በመሆኑ ሕብረተሰቡ ሳይደናገጥ መደበኛ ተግባሩን እንዲያከናውን አሳስቧል።

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ባለሀብቶችና አሽከርካሪዎች የጸጥታ ኃይሉን አስተማማኝ ከላላ በመተማመን የተለመደውን የሕዝብ አገልግሎት ያለ ምንም ስጋት እንዲቀጥሉ ጥሪ ቀርቧል።

የጸጥታ ኃይሉ የክልሉን ሰላም ለማፍረስና ምርጫውን ለመበጥበጥ የሚሞክር የትኞቹንም ሕገ-ወጥ አካላት እንቅስቃሴ ለማክሸፍና ሕግና ሥርዓትን ለማስከበር ከመቼውም ጊዜ በላይ በላቀ ተጠንቀቅና ዝግጁነት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

“በምርምርና ፈጠራ የታገዘ ፖሊሳዊ አገልግሎት ለዘላቂ ሰላም፤” 4ኛው የምርምር ሲምፖዚየም በአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተካሂዷል።የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ “ምርምርና ፈጠ...
28/05/2026

“በምርምርና ፈጠራ የታገዘ ፖሊሳዊ አገልግሎት ለዘላቂ ሰላም፤” 4ኛው የምርምር ሲምፖዚየም በአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተካሂዷል።

የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ “ምርምርና ፈጠራ ለተሻለ የፖሊስ አገልግሎት እና ዘላቂ ሠላም!” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየው 4ኛው የምርምር ሲምፖዚየም ተጠናቋል።

በዚህ መድረክ ላይ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች፣ የፖሊስ ስትራቴጂክ እና ከፍተኛ አመራሮች፣ ተመራማሪዎችና የዘርፉ ምሁራን ታድመዋል።

በሲምፖዚየሙ መክፈቻ ላይ መሪ ቃሉን መነሻ በማድረግ ቁልፍ ንግግር ያደረጉት ረዳት ኮሚሽነር ግዛቸው ከበደ የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ የአካዳሚክስ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት እንደገለጹት ወቅቱ የሚጠይቀውን ቀልጣፋ፣ ዘመናዊና ውጤታማ የፖሊስ አገልግሎት ለመስጠት የምርምርና የፈጠራ ስራዎች ወሳኝ ሚና አላቸው።

ይሄንን ሳይንሳዊ መንገድ መከተል ለአካባቢው ህዝብ አስተማማኝና ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ጠንካራ መሰረት ይጥላል ሲሉ ረዳት ኮሚሽነር ግዛቸው ከበደ አክለው አብራርተዋል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የ6ኛ ዕዝ አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ብርሃኑ ጥላሁን በበኩላቸው፤ በምርምር የተደገፈ ፖሊሳዊ አገልግሎት መስጠት በክልሉ አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

ከጸጥታ መዋቅሩ ጎን ለጎን የጥናትና ምርምር ተቋማት የሚያመነጯቸው ግኝቶች በወረቀት ላይ ብቻ መቅረት እንደሌለባቸውና በተግባር ላይ መዋል እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር አበበ ደለለ በበኩላቸው የወቅቱ የጸጥታና ደህንነት ሁኔታ ፖሊሳዊ አገልግሎቱ ካለበት ልማዳዊ አሰራር ወጥቶ ወደ ላቀ ሳይንሳዊ ምዕራፍ እንዲሸጋገር እንደሚያስገድደው በስፋት አብራርተዋል።

የክልሉ የፖሊስ ሰራዊት በንድፈ-ሀሳብ ብቻ ሳይሆን በዘመናዊ እውቀት፣ በተግባራዊ ክህሎት እና በከፍተኛ ስነ-ምግባር የታነጸ ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።

“የእኛ ዋና ተልዕኮ ህዝብን በታማኝነት፣ በቅንነትና በሙያዊ ብቃት ማገልገል ነው። ይህንን ለማሳካት ደግሞ ሰራዊታችን በየደረጃው የህዝብን ደህንነት በዘላቂነት ማረጋገጥ የሚያስችል የዕውቀትና የክህሎት ባለቤት መሆን አለበት” ሲሉ ምክትል ኮሚሽነር አበበ ደለለ አጽንኦት ሰጥተው አብራርተዋል።

ፕሬዝዳንቱ አያይዘውም ይህ 4ኛው የምርምር ሲምፖዚየም እንዲሁ በየዓመቱ የሚደረግ ተራ ስብሰባ ሳይሆን፣ የአማራን ህዝብ ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለማስጠበቅ የሚያግዙ ስልታዊ አቅጣጫዎች የሚቀመጡበት መድረክ መሆኑን ጠቁመዋል።

መድረኩ በተጨባጭ መሬት ላይ ያሉ የጸጥታ ፈተናዎችን በሳይንሳዊ ጥናትና ምርምር በተደገፈ አሰራር ለመፍታት እና አዳዲስ ስልቶችን ለመንደፍ የሚያስችል ዋና የዕውቀት መፍለቂያ መሆኑንም ገልጸዋል።

ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ በአሁኑ ወቅት የነገውን ፖሊስ የመገንባት ትልቅ ራዕይ ሰንቆ እየሰራ መሆኑን የጠቀሱት ምክትል ኮሚሽነሩ በተለይም በቴክኖሎጂ አጠቃቀም የበቃ፣ ከዘመኑ ጋር እኩል የተራመደ እና በቴክኒክና ታክቲክ የላቀ ዘመናዊ የፖሊስ ሰራዊት ለመገንባት በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

የወንጀል መከላከልም ሆነ የምርመራ ስራዎች በቴክኖሎጂ ሲታገዙ የህዝቡን እምነት የሚያተርፍና አጥፊዎችን በቀላሉ ለህግ የሚያቀርብ ተቋም መፍጠር እንደሚቻልም በዝርዝር አስገንዝበዋል።

በሲምፖዚየሙ ላይ ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን፤ ከነዚህም መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦
• “Police operational roles and crime prevention effectiveness in volatile security context”

• “Challenges of policing in enforcing law and public order during armed conflict”

• “Unpacking predictors of police violence in Ethiopia: A post-1991 perspective”

• “Examining the effect of authentic and transformational leadership styles on police officers' motivation”

• “Police education and training as drivers of police reform in Ethiopia”

በቀረቡ ጥናታዊ ጽሑፎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ 4ኛው የምርምር ሲምፖዚየም መካሄድ ጀመረ።የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ "ምርምርና ፈጠራ ለተሻለ የፖሊስ አገልግሎት እና ዘላቂ ሠላም!" በሚል መ...
28/05/2026

የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ 4ኛው የምርምር ሲምፖዚየም መካሄድ ጀመረ።

የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ "ምርምርና ፈጠራ ለተሻለ የፖሊስ አገልግሎት እና ዘላቂ ሠላም!" በሚል መሪ ቃል ለሁለት ቀናት የሚቆየውን 4ኛውን የምርምር ሲምፖዚየም ማካሄድ ጀምሯል።

በዚሁ ከፍተኛ የፖሊስ ምርምር መድረክ ላይ በሀገር መከላከያ ሰራዊት የ6ኛ ዕዝ አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ብርሃኑ ጥላሁን፣ የአማራ ክልል ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር አበበ ደለለ፣ በብርጋዴር ጀኔራል ሶፍያን መሀመድ 602ኛ ኮር አዛዥ፣ አቶ ዳንኤል ደሳለኝ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ፣ አቶ ተሾመ ዋለ የደብረማርቆስ ከተማ ከንቲባ፣ የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ስትራቴጂክ እና ከፍተኛ አመራሮች፣ አባላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።

ከዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ በዚሁ ለሁለት ቀናት በሚቆየው ሲምፖዚየም ላይ በፖሊሳዊ አገልግሎት አሰጣጥ፣ በፈጠራ ስራዎችና በዘላቂ ሰላም ግንባታ ዙሪያ ትኩረታቸውን ያደረጉ አምስት የምርምር ጽሁፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ይደረግባቸዋል።

ይህ የምርምር መድረክ የፖሊስ ተቋምን የአሰራር ስርዓት በሳይንሳዊ እውቀትና በምርምር ውጤቶች ለማዘመን፣ የጸጥታ ፈተናዎችን በዘላቂነት ለመቅረፍ እና የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት አስተማማኝ በሆነ መልኩ ለማረጋገጥ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ታምኖበታል።

Address

Police Commission
Bahir Dar
244

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Region Police posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Region Police:

Share