Amhara Diaspora Coordinator Office

Amhara Diaspora Coordinator Office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amhara Diaspora Coordinator Office, Government Organization, Bahir Dar.

ማስታወቂያ፤የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በበይነ መረብ ለማወያየት ጥሪ ማቅረቡን ስለማሰወቅ፤ኮሚሽኑ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ላ...
28/06/2023

ማስታወቂያ፤

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በበይነ መረብ ለማወያየት ጥሪ ማቅረቡን ስለማሰወቅ፤

ኮሚሽኑ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ላይ ባጋራው ማስታወቂያ ዳያስፖራው በምክክር ሂደቱ በንቃት እንዲሳተፍና የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪውን ያቀረበ ሲሆን፣ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንደሚኖሩባቸው አካባቢዎች የሚሳተፉባቸው የተለያዩ የስብሰባ ቀንና ሰዓት ማመቻቸቱን አሳውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎትም ዳያስፖራው ኮሚሽኑ በተከታታይ የሚያወጣቸውን ማስታወቂያዎች በመከታተል በሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ የሚኖረውን ተሳትፎ እንዲያሳድግ ከወዲሁ ጥሪውን ያቀርባል።

ለክትትልና ምዝገባ ያመቻችሁ ዘንድ ኮሚሽኑን ማስታወቂያውን ያወጣበትን ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ሊንክ አያይዘን አቅርበናል።

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=257811013607002&id=100081343145333&mibextid=Nif5oz

የዲያስፖራውን ተሳትፎ ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር  እየተካሄደ ነው  (ግንቦት 25/09/2015 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርእሰ መ...
05/06/2023

የዲያስፖራውን ተሳትፎ ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር እየተካሄደ ነው

(ግንቦት 25/09/2015 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርእሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የዳያስፖራውን ተሳትፎ ለማሳደግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር እየተካሄደ ነው።

በምክክር መድረኩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ተወካዮች፣ የርእሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት አመራሮች፣ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት፣ የመሬት፣ የከተማና ቤቶች ልማት፣ የፍትህ ቢሮ ኃላፊዎች እንዲሁም የዞን አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች እና የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በምክክር መድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሰላማዊት አለማየሁ ሀገራችን ያጋጠማትን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በመፍታት ረገድ ዲያስፖራው ጉልህ ድርሻ አለው ብለዋል።

አገራችን ያለባትን የውጭ ምንዛሬ ጉድለት ለመሙላትና የምንፈልገውን የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማፋጠን ለዳያስፖራው ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ተሳትፎውን ማሳደግ ይኖርብናል ነው ያሉት ኃላፊዋ።

ኃላፊዋ አክለውም፦ ዳያስፖራው መዋለነዋዩን በአገር ውስጥ ኢንቨስት አድርጎ የስራ እድል በመፍጠር ለኢኮኖሚያችን እድገት የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ያልተገባ ቢሮክራሲን በማስቀረት ቀልጣፋና ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

የጋራ ምክክር መድረኩ የዳያስፖራውን ተሳትፎ ለማሳደግና ቅንጅታዊ አሰራርን በመዘርጋት ረገድ ያሉ ጉድለቶችን በጥልቀት በመገምገም የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።

25/05/2023

አብክመ መሬት በ2015 በጀት ዓመት በክልሉ በተለያያ አዞኖችና ወረዳዎች ሚገኙ ነፃ የእርሻ ኢንቨስትመንት መሬቶች የተሻለ የማልማት አቅም ላላቸው ባለሀብቶች ለማስተላለፍ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ።
ዝርዝሩን በበኩር ጋዜጣ ግንቦት 14/2015 እትም ገፅ 24 እና 25 እንዲሁም በቢሮውና በዞኖች የውስጥ ማስታወቂያ መመልከት ይችላሉ።

የመሬት ቢሮ በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች በመሬት ባንክ ውስጥ የሚገኙ የመንግስት መሬቶችን በገጠር መሬት የሊዝ ህግ በውድድር ስርአት ለባለሃብቶች ማስተላለፍ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም የግብርና ኢንቨስትመንት መሬት ፈላጊዎች በሙሉ ከዚህ በታች በዝርዝር የተገለጹትን መስፈርቶች ግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የተዘጋጀ የኘሮጀክት ሀሳብ ሰነድ እና አሰፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን አያይዞ በማቅረብ መመዝገብና መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
1. በግብርና ኢንቨስትመንት መሬት የሚፈልግ ባለሃብት (ድርጅት) ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር የበዓል ቀናትን ጨምሮ አስራ አምስት ተከታታይ ቀናት ጊዜ ውስጥ የኘሮጀክት ሀሳብ (Business plan) ከማመልከቻ ጋር ለአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት መሬት ቢሮ ማቅረብ አለበት፡፡
አመልካቹ የኘሮጀክት ፕሮፓዛል (ሃሳብ) በአማርኛ ወይም በእንግሊዘኛ ቋንቋ አዘጋጅቶ ማቅረብ አለበት፡፡ የሚወዳደርበትን መሬት ለይቶ ማቅረብ አለበት (ማለትም መሬቱ የሚገኝበት ዞን፣ ወረዳ፣ ቀበሌ፣ ልዩ-ቦታ ወይም ብሎክ፣ የመሬቱ ስፋት በሄ/ር እና ለምን አገልግሎት እንደሚውል/የመሬት አጠቃቀሙ/ እና በማስታወቂያው ላይ የተጠቀሰውን የቦታው ተራ ቁጥር መግለጽ አለበት)፡፡

2. አንድ ተወዳዳሪ ባለሀብት መወዳደር የሚችለው ሁለት መሬቶችን ብቻ በመምረጥ ነው፡፡ ነገር ግን ከሁለት በላይ በሆነ መሬት አመልክቶ ቢገኝ ሙሉ በሙሉ ከውድድር ውጭ /የሚሰረዝ/ ይሆናል፡፡

3. ተወዳዳሪ ባለሀብቶች ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን በፊት ባሉት 3 ተከታታይ ወራት ጊዜ ውስጥ የፋይናንስ አቅማቸውን የሚያሳይ የባንከ ስቴትመንት በባንኩ ዲስትሪክት ኃላፊ በተፈረመበት መሸኛ አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡

4. አመልካቹ አካል ማህበር ከሆነ በሚመለከተው አካል የጸደቀ የመመስረቻ ጽሁፍ እና ህጋዊ ሰውነት ያገኘበትን ሰነድ ማቅረብ አለበት፡፡

5. አመልካቾች ጠቃሚ ናቸው የሚሏቸውን ሌሎች ተጨማሪ የሰነድ ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ማቅረብ ይችላሉ፡፡

6. አመልካቾች የተንቀሳቃሽ ንብረት ማለትም እንደ እርሻ መገልገያ ማሽነሪ እና የመሳሰሉትን ያላቸው ተወዳዳሪዎች የባለቤትነት ማስረጃዎች ህጋዊ ስልጣን ካለው ተቋም ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
7. ከዚህ በፊት መሬት ወስደው በማልማት ላይ ያሉ ማስጠንቀቂያ ያለባቸው ባለሃብቶች እና መሬታቸው ወደ መሬት ባንክ የገባባቸው ባለሃብቶች በዚህ ውድድር ተሳታፊ አይሆኑም፡፡

8. የውጭ ሃገር የባንክ ስቴትመንት የሚያቀርቡ ባለሃብቶች የሚያቀርቡትን የባንክ ተቀማጭ የገንዘብ አቅም በሃገር ውስጥ ጉዳዩ በሚመለከተው ህጋዊ ተቋም የተገናዘበ ማረጋገጫ ሰነድ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

9. በአንድ መሬት ላይ ብቸኛ ተወዳደሪ በሚቀርብበት ጊዜ፣ የቴክኒክ ግምገማ ከ60% እንዲሁም የፋይናንስ አቅም የሚያሳይ ትራንዛክሽን ደግሞ ከ40% የሚያዝላቸው ሁኖ በሄ/ር የተቀመጠውን ዝቅተኛ መስፈርት/ስታንደርድ/ አሟልቶ ሲገኝ እና በሁለቱም የመገምገሚያ መስፈርቶች በድምሩ ውጤት 50% (ሃምሳ ከመቶ) እና ከዛ በላይ ነጥብ ካመጣ የውድድሩ አሸናፊ ይሆናል፡፡

10. ከላይ በተራ ቁጥር 8 እንደተጠቀሰው የተጠበቀ ሆኖ በአንድ መሬት ላይ ከአንድ በላይ ተወዳዳሪ በሚኖርበት ጊዜ፣ ተወዳዳሪዎች በሚያገኙት የነጥብ ብልጫ የሚለዩ ይሆናል፡፡ ሆኖም ተወዳዳሪዎች በቴክኒክ እና በፋይናንስ ግምገማ ውጤት ከ50% በታች ካመጡ ፕሮጀክቱ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
በአንድ መሬት ላይ ከአንድ በላይ ተወዳደሪዎች ተወዳድረው እኩል ውጤት ካገኙ ለሴት ተወዳደሪዎች፣ በንግድ ማህበራት (አክሲዮን፣ሽርክና፣ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እና የመሳሰሉት) ተደራጅተው ለቀረቡ ባለሃብቶች እንደቅደም ተከተላቸው ቅድሚያ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
11, ሆኖም በአንድ መሬት ሴት ተወዳዳሪዎች ከሴት ተዎዳዳሪዎች፤ወንድ ተወዳዳሪዎች ከወንድ ተወዳዳሪዎች እና በንግድ ማህበር የተደራጁ ተወዳዳሪዎች ከንግድ ማህበር ከተደራጁ ተወዳዳሪዎች እኩል ውጤት ካገኙ በባንክ ስቴትመንት የተሻለ የገንዘብ መጠን ያሳየው (በባንክ ስቴትመንት የተሸለ ነጥብ የተሰጠው) ቅድሚያ ይሰጠዋል ፡፡
12. በተራ ቁጥር 11 ከላይ የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ በሁሉም መስፈርቶች እኩል ውጤት ቢያመጡ ተወዳዳሪዎች በተገኙበት በዕጣ የሚለዩ ይሆናል፡፡

ማሳሰቢያ
1, ቀሪዎቹን የማወዳደሪያ መስፈርቶች በተመለከተ ለኢንቨስትመንት እንዲውል ተሻሽሎ በወጣው የገጠር መሬት አሰጣጥ እና አጠቃቀም መመሪያ ቁጥር 13/2013 ዓ.ም መመልከት ይቻላል፡፡

2, ለውድድር የሚቀርቡ አስፈላጊ መረጃዎችን በታሸገ ኢንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

3, ለውድድር የሚቀርብ የባንክ ስቴትመንት ማስታወቂያው እስከ ወጣበት ቀን ድረስ ያለው ያልተቆራረጠ ወደ ኋላ የ3 ተከታታይ ወራት የባንክ እንቅስቃሴ መቅረብ ይኖርበታል፡፡ ሆኖም ከተጠቀሰው ቀን ወደፊትም ሆነ ወደኋላ ጨምሮ ቢቀርብ ከውድድሩ ይሰረዛል፡፡

4, በግሉ ለመወዳደር ጥያቄ ያቀረበ አመልካች ለውድድሩ ያቀረበውን የባንክ ስቴትመንት ድጋሚ ይሄው ተወዳዳሪ በአባልነት የተካተተበት ማህበር ተወዳዳሪ ሆኖ ቢቀርብ ለማህበሩ በማወዳደሪያነት አይያዝም፡፡ በተመሳሳይ መልኩ በግሉ የእርሻ ማሽነሪ ያለው አካል በአባልነት የተካተተበት ማህበር ተወዳዳሪ ሆኖ ሲቀርብ ይሄው የግል ማሽነሪ ለማህበሩ በማወዳደሪያነት አይያዝም፡፡

5, ማስታወቂያው ከወጣ ከአስራ አምስተኛው ቀን በኋላ የሚቀርብ ጥያቄ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡

6, በተራ ቁጥር 4 እና 5 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ የምዝገባው ቀን ካለፈ በኋላ የሚቀርብ ማንኛውም ሰነድ እና ተወዳደሪዎች ከተመዘገቡ በኋላ የምዝገባ ጊዜ ባይጠናቀቅም የተጨማሪ ሰነድ ይያዝልኝ ወይም ቀድሞ ገቢ የተደረገ ሰነድ ይቀየርልኝ ጥያቄ ተቀባይነት የለውም፡፡

7, አመልካቾች ለውድድር የሚያቀርቡት የኘሮጀክት ሃሳብ፣ ለመወዳደር ካመለከቱበት ዞን፣ ወረዳ፣ የመሬት ስፋት፣ የመሬት አጠቃቀም እና ተራ ቁጥር ጋር መገናዘብ የሚገባው ሲሆን ከተዘረዘሩት ውስጥ በአንዱም ቢሆን ካልተጣጣሙ ውድቅ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም እያንዳንዳቸው ለውድድር የቀረቡ መሬቶች ለየብቻቸቸው የፕሮጀክት ሀሳብ ሊዘጋጅላቸው ይገባል፡፡

8, አመልካቾች የፕሮጀክት ሃሳባቸውን እና ሌሎች ለውድድር አሰፈላጊ የሆኑ ሰነዶችን የሚያቀርቡት ማስታወቂያው አየር ላይ በዋለበት ጊዜ ውስጥ ባሉት የስራ ቀናት በመንግስት የስራ ሰዓት ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡
9. የኘሮጀክት ሃሳብ (Business plan) እና ሌሎች ጠቃሚ ማስረጃዎችን ቢቻል የድርጅቱ ማህተም ተደርጎበት እና የባለሀብቱ ፊርማ ተፈርሞበት ለአብክመ መሬት ቢሮ በውስጥ ማስታወቂያ በሚገልጸው ቢሮ ቁጥር በስራ ሰዓት መቅረብ ይኖርበታል፡፡

Awelachew Diaspora, [5/24/2023 5:03 PM]
10. የምዝገባው ጊዜ በተጠናቀቀ በ30 የስራ ቀናት ውስጥ አሽናፊዎችን እና ውጤታቸውን በተቋሙ የውሰጥ ማስታወቂያ ይገለፃል፡፡
11, በውጤቱ ቅሬታ ያለው አመልካች ቢኖር ጊዜያዊ ውጤቱ በተገለጸ በአምስት ተከታታይ የስራ ቀናት ጊዜ ውስጥ ቅሬታውን በጽሁፍ ለአብክመ መሬት ቢሮ ማቅረብ ይችላል፡፡
12, አሸናፊ የሆነው ባለሃብት/ድርጅት/ ውጤቱ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ30 ቀናት ውስጥ ቀርቦ ውል ካልያዘ መብቱን መጠቀም እንዳልፈለገ ተቆጥሮ በነጥብ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አሸናፊ ባለሃብት ወይም ድርጅት ውል እንዲወስድ ይደረጋል፡፡

13, ከባለሃብት ተመልሰው ለውድድር የወጡ መሬቶች በካሳ ህጉ መሰረት ካሳ የሚያስከፍል ንብረት /ግንባታ፣አት/ፍራፍሬ እና መሰል ንብረቶች/ ካሉ አሸናፊው ግለሰብ/ድርጅት በካሳ ህጉ መሰረት ውል ከመውሰዱ በፊት ተገቢውን ካሳ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡
14, ቢሮው ውድድሩን እንደ አሰፈላጊነቱ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
የአብክመ መሬት ቢሮ
ባህር ዳር

ማስታቀዊያ፤የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በበይነ መረብ ለማወያየት ዝግጅት ማጠናቀቁን እንደገለጸ ስለማሳወቅ፤ኮሚሽኑ በይፋዊ ...
10/05/2023

ማስታቀዊያ፤

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በበይነ መረብ ለማወያየት ዝግጅት ማጠናቀቁን እንደገለጸ ስለማሳወቅ፤

ኮሚሽኑ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ላይ ባጋራው ማስታወቂያ ዳያስፖራው በዚህ ታሪካዊ የምክክር ሂደት ውስጥ እንዲሳተፍና የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪውን ያቀረበ ሲሆን፣ የስብሰባውን ቀንና ሰዓት እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በቅርቡ የሚያሳውቅ መሆኑን ገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎትም ዳያስፖራው ኮሚሽኑ በተከታታይ የሚያወጣቸውን ማስታወቂያዎች በመከታተል በሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ የሚኖረውን ተሳትፎ እንዲያሳድግ ከወዲሁ ጥሪውን ያቀርባል።

ለክትትል ያመቻችሁ ዘንድ ኮሚሽኑን ማስታወቂያውን ያወጣበትን ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ሊንክ አያይዘን አቅርበናል።

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=229197633135007&id=100081343145333&sfnsn=mo&mibextid=RUbZ1f

23/03/2023

የወጪ ንግድ ቀረጥ ማበረታቻ መመሪያ እየተሻሻለ ነው
--------------------------------------------
መጋቢት 14/2015 ዓ.ም ኢኢቢ፡ ባህርዳር
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አምራች ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና ስትራቴጂክ ገቢ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት እንዲሁም የወጪ ንግድን ለማሳደግ በ2007 ዓ.ም የተዘጋጀውን የወጪ ንግድ ቀረጥ ማበረታቻ መመሪያ እየተሻሻለ ነው፡፡
በስራ ላይ የቆየው ሀገር አቀፍ ስታንዳርድ የግብዓት-ምርት ጥምርታ ሰነድና መመርያ ከዘርፉ ዕድገትና ከስርዓቱ አዲስ መሆን ጋር ተያይዞ የተጠቃሚዎችን ፍላጎት ማሟላት ባለመቻሉ ነው እንዲሻሻል የተደረገው፡፡
በመሆኑም መመሪያውን በማሻሻል በዘርፉ እያደገ የመጣውን ፍላጎት በሚፈለገዉ ደረጃ ለማርካት እና በቀጣይ ከዘርፉ የሚጠበቀውን የወጪ ንግድ ገቢ ግብን ለማሳካት የሚያስችሉ ከመመሪያዉ ጋር በማጣቀሻ የሚካተቱ የሁሉንም ዘርፎች ስታንዳርድ ፣የግብዓት ጥምርታ ዝርዝር ሁለገብ ግብአቶች የመለየትና የማካተት ስራ እየተከናወነ ነው፡፡

281 ፕሮጀክቶች 81 ቢሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ ኢንቨስትመንት ፍቃድ መውሰዳቸውን የጎንደር ከተማ አስተዳደር አሳወቀ። ከተማ አስተዳደሩ ዛሬ ለ33 ባለሀብቶች 24 ሄክታር መሬት የቦታ ...
04/03/2023

281 ፕሮጀክቶች 81 ቢሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ ኢንቨስትመንት ፍቃድ መውሰዳቸውን የጎንደር ከተማ አስተዳደር አሳወቀ።

ከተማ አስተዳደሩ ዛሬ ለ33 ባለሀብቶች 24 ሄክታር መሬት የቦታ ርክክብ አድርጓል።

ከ33 ባለሀብቶች መካከል 13 ዲያስፖራ መሆናቸው ተገልጿል።

ባለሀብቶች የተሰማሩት በኬሚካል፣ በምግብነክ፣ በጨርቃጨርቅ እና በብረታብረት ዘርፍ ነው።

የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ባዩህ አቡሃይ ጎንደርን ያላት ፀጋ አቅም ተጠቅመን መቀየር አሁን ላለው አመራር እና ህዝብ ገዳይ እንጅ ትላንትን በመውቀስ መቀጠል አያስፈልግም ብለዋል።

ከተማችን ለመቀየር ሁላችንም መዘጋጀት አለብን ያሉት ምክትል ከንቲባው ከተማ አስተዳደሩ የሚያጋጥሙ ችግሮች እንደሚፈታ ገልጸዋል።

ጎንደር ከተማ በኢንቨስትመንት ትልቅ አቅም ያላት በመሆኑ ጎንደር የሚወዱና የጎንደር ተወላጆች ኢንቨስት እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የጎንደር ከተማ ብልጽግና ፖርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አወቀ አስፈሬ የገበሬ ካሳ ከፍለው ቦታ ለተረከቡ ባለሀብቶችና ዲያስፖራዎች ምስጋና አቅረበዋል።

በመንግስት በኩል የሚገጥሙ ችግሮች መንግሰት ለመፍታት ዝግጁ መሆኑን አቶ አወቀ ተናግረዋል።

የጎንደር ከተማ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግርማይ ልጃለም በበኩላቸው እጅ ለእጅ ተያይዘን ጎንደርን የኢንዱስትሪ ማዕከል ማድረግ ይገባል ብለዋል። ለባለሀብቶች ካርታችሁን ከተረከባችሁ ጀምሮ ወደ ስራ እንድትገቡ ሲሉ የመምሪያ ኃላፊው አሳስበዋል።

በፋይናንስ ተቋማት በኩል የብድር አገልግሎት እንደሚመቻችላቸው አቶ ግርማይ ገልጸዋል።

ከባለሀብቶች ከሰጡት አስተያየት መካከል አቶ በላይ ደሴ ጎንደር ከተማ በሁሉም ዘርፍ ለኢንቨስትመንት ምቹ መሆኑ ይታወቃል። የፋይናንስ ተቋማት የብድር አገልግሎት ችግር አለ ይህ መስተካከል አለበት።

የከተማ አስተዳደሩ ኢንቨስትመንት መመሪያ በ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት 281 ፕሮጀክቶች 81 ቢሊዮን ካፒታል አስመዝግበው ኢንቨስትመንት ፍቃድ መውሰዳቸው ተገልጿል። 281 ፕሮጀክቶች ለ89 ሽህ ዜጎች የስራ እድል እንደሚፈጥሩ ተጠቁሟል።

መረጃው የጎንደር ከተማ መንግስት ኮምንኬሽን ነው

17/02/2023

በተጠናቀቀው ስድስት ወር በኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት የተከናወኑ ዋና ዋና የዳያስፖራ ተሳትፎ ስራዎችን ለማሳወቅ የተዘጋጀ መግለጫ፤

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት የዳያስፖራ ስራዎችን እንዲያስተባብር በተሰጠው ሀላፊነት መሰረት በልዩ ልዩ የዓለም ክፍል ከሚገኙ የኢፌዴሪ ሚሲዮኖችና የዳያስፖራ አደረጃጀቶች እንዲሁም በሀገር ውስጥ ከሚገኙ ልዩ ልዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እንደሚሰራ ይታወቃል።

በመሆኑም በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ አገልግሎቱ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ስራዎች ለማሳወቅ ይህ መግለጫ ተዘጋጅቷል።

ከበጀት አመቱ አጋማሽ የስራ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ በዳያስፖራ ማህበረሰብ ልማት ስራዎች ከ700 በላይ የዙም እና የገጽ ለገጽ መድረኮችን በማካሄድ ከ190ሺ በላይ የዳያስፖራ ማህበረሰብ አባላትን በልዩ ልዩ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ማወያየትና ከ180 በላይ የዳያስፖራ ማህበራት፣ ሙያ ተኮር በጎ አድራጎት ድርጅቶችና ሌሎች አደረጃጀቶችንም ለማጠናከር ተሰርቷል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ግንዛቤ እንዲኖረውና የኢትዮጵያ ጥቅሞች እንዲከበሩ የሚያደርጉ በርካታ የፐብሊክና ዲጂታል ዲፕሎማሲ ስራዎችም ተከናውነዋል።

ከዳያስፖራ ተሳትፎ አኳያ በተሰሩ ስራዎች ከ40 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡና በተለያዩ የኢንቨስትመንት የስራ መስኮች ለመሳተፍ ጥያቄ ላቀረቡ ከ800 በላይ የዳያስፖራ አባላት የተለያዩ ድጋፎች ተሰጥተዋል። የኢንቨስትመንት ጥያቄ ካቀረቡ ዳያስፖራዎች መካከልም ከ27 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 223 ዳያስፖራዎች የመሬትና ስራ ለመጀመር የሚያስችሉ ሌሎች ግብአቶች እንዲሟላላቸው ድጋፍ ተደርጓል። በውሃ፣ በቴክኖሎጂ፣ በጤና እንዲሁም በአስተዳደር ዘርፎች 86 የዳያስፖራ አደረጃጀቶችና ግለሰቦችን ያሳተፉ የእውቀትና ክህሎት ሽግግር የተካሄደባቸው ስልጠናዎችና የቴክኖሎጂ ድጋፍ ስራዎች ተከናውነዋል። ከአራት ሺ በላይ የዳያስፖራ አባላት የውጭ ምንዛሬ አካውንቶችን በመክፈት ከአራት ሚሊዮን ዶላር በላይ ተቀማጭ ያደረጉ ሲሆን፣ ከ2.9 ቢሊዮን ዶላር በላይ ወደ ሀገር ቤት በሬሚንስ መልክ ልከዋል።

ለልዩ ልዩ ጉዳዮች ሀብት ለማሰባሰብ በተከናወኑ ተግባራትም ለታላቁ የኢትዮጵያ ሀዳሴ ግድብ ግንባታ ድጋፍ እንዲሆን ከ731ሺ ዶላር በላይ በውጭ ሀገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ማሰባሰብ ተችሏል። የተለያዩ ግብረ-ሰናይ ድርጅቶችን፣ የዳያስፖራ ማህበራትን፣ ሙያ ተኮር በጎ አድራጎት ድርጅቶችንና ታዋቂ ግለሰቦችን በማስተባበርም ከ20 ሚሊየን ብር በላይ ለበጎ አገልግሎት ሥራዎች እንዲሁም ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍና ለመሰረተ-ልማቶች መልሶ ግንባታ ከአምስት ሚሊየን ዶላር በላይ በገንዘብና ከ12 ሚሊዮን ዶላር በላይ በአይነት ድጋፍ መሰብሰብ ተችሏል፡፡ ይህም በበጀት አመቱ አጋማሽ ከዳያስፖራው የተሰባሰበውን የገንዘብና የአይነት ድጋፍ መጠን ከ900 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ እንዳደረሰው ያሳያል።

በተያዘው ሁለተኛ አጋማሽ የበጀት ዓመትም የዳያስፖራ ተሳትፎ ስራዎችን ለማሳደግ የተነደፉ አዳዲስ ስልቶችን በመጠቀም፣ ሚሲዮኖችና የዳያስፖራ አደረጃጀቶችን በማስተባበር የዳያስፖራውን ተሳትፎ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚሰራ ይሆናል።

***

የመጀመሪያው የዳያስፖራ አደረጃጀቶች የእውቅና መርሀ ግብር ተካሄደየመጀመሪያው የዳያስፖራ አደረጃጀቶች የእውቅና መርሀ ግብር ክብርት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የተከበሩ የፓርላማ ...
27/01/2023

የመጀመሪያው የዳያስፖራ አደረጃጀቶች የእውቅና መርሀ ግብር ተካሄደ

የመጀመሪያው የዳያስፖራ አደረጃጀቶች የእውቅና መርሀ ግብር ክብርት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የተከበሩ የፓርላማ አባላት፣ ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ ክብራን ሚኒስትሮች፣ ሚኒስትር ዴኤታዎችና የተቋማት ሀላፊዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የዳያስፖራ አደረጃጀት አመራሮችና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት ተካሄደ።

በወቅቱም በአስራ አንድ ልዩ ልዩ ዘርፎች በሁለንተናዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጎ ተሳትፎ ያደረጉና ከሀያ አምስት ሀገራት የተውጣጡ ሀምሳ ሁለት የዳያስፖራ አደረጃጀቶች እውቅና የተሰጣቸው ሲሆን፣ የአደረጃጀቶቹን እንቅስቃሴ የሚያስተዋውቅ መጽሐፍም ተመርቋል።

የዕለቱ የክብር እንግዳ ክብርት የኢፌዴሪ ፕሬዚደንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ባስተላለፉት መልዕክት እውቅናው ለሀገራቸው በጎ ስራ እየሰሩ ለሚገኙና በመላ ዓለም ላሉ የዳያስፖራ አባላት ሁሉ ነው ብለዋል። አክለውም ኢትዮጵያ ለሀገራቸው መልካም ነገር የሚያከናውኑ አካላትን ሁሌም ታስታውሳለች ያሉ ሲሆን፣ መንግስትም ዳያስፖራው ከሀገሩና ከህዝቡ ጋር ተቀራርቦ እንዲሰራ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ብለዋል። ኢትዮጵያ ያለፉትን ሁለት ዓመታት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ማለፏን ያስታወሱት ፕሬዚደንት ሣህለወርቅ ዘውዴ፣ የዳያስፖራው ማህበረሰብ በሰላም ግንባታና በመልሶ ማቋቋም ስራ ላይ ሀገሩንና ህዝቡን እንዲያግዝ ጥሪ አቅርበው፣ ዳያስፖራው ተባብሮ ሊሰራና ሀገሩም ቋሚ አጀንዳው ልትሆን ይገባል ብለዋል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን በበኩላቸው በመላ አለም የሚገኙ የዳያስፖራ አባላቶች ኢትዮጵያ ችግርና ፈተና በገጠማት ጊዜ ለሀገራቸው የሰሩት ስራ በወርቃማ ብዕር የሚፃፍና ሁሌም በታሪክ የሚጠቀስ ነው ብለዋል። የዳያስፖራው ማህበረሰብ ከዚህ ቀደም በሀገር ሁለንተናዊ ተግባራት ላይ የነበረውን ተሳትፎ ይበልጥ በማሳደግ በኢትዮጵያ እየተከናወነ ባለው የሰላም ግንባታ ላይም በጎ ሚናውን በመወጣት የሀገር አለኝታነቱን ዳግም እንዲያረጋግጥ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሀመድ እንድሪስም በበኩላቸው ዳያስፖራው ማህበረሰብ ለሀገሩ በተለያዩ መስኮች እያሳየ ላለው ተሳትፎ መንግስት ሁሌም እውቅና እንደሚሰጥ ገልጸው፣ ዳያስፖራው የሚሳተፍባቸው ልዩ ልዩ ዘርፎችን ታሳቢ ያደረጉ ተመሳሳይ የእውቅና መድረኮች መካሄዳቸው ይቀጥላል ብለዋል። መድረኩ የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ ላሉ የዳያስፖራ አደረጃጀቶች እውቅና በመስጠት እስካሁን የነበሩ በጎ ጥረቶችን ለማመስገን፣ ለጠራና ከፍ ላለ ሀገራዊ ራዕይ ለማነሳሳት፣ ለተሻለ ስራ፣ ለተደራጀ እንቅስቃሴና በጥምረት ለሚመራ የዳያስፖራ ተሳትፎ በር ለመክፈት እንዲሁም ለቀጣይ ስራዎችን በአደራ መልክ ለማስረከብ መዘጋጀቱን አስገንዝበዋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይም የዳያስፖራ አደረጃጀቶቹ በቀጣይ ከሀገራቸው ጋር የሚኖራቸው ግንኙነትና ተሳትፎ የሚመራባቸው መሰረታዊ መርሆዎችን የያዘ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።

ዳያስፖራዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በስፋት እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል /አቶ መላኩ አለበል/------------------------------------ጥር 15/2015ዓ.ም (ኢ.ሚ) በ...
24/01/2023

ዳያስፖራዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በስፋት እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል /አቶ መላኩ አለበል/
------------------------------------
ጥር 15/2015ዓ.ም (ኢ.ሚ) በውጪ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በስፋት በመሰማራት ሀገራቸውንና እራሳቸውን እንዲጠቅሙ ምቹ ሁኔታ መኖሩን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ተናግረዋል።
ዳያስፖራዎችና ባለሀብቶች የተሳተፉበት "ኢትዮጵያ ታምርት" የኢንቨስትመንት ፎረም በጎንደር ከተማ ተካሂዷል።

በፎረሙ ላይ የኢንደስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል እንደተናገሩት "ኢትዮጵያ ታምርት" በሚለው ሀገር አቀፍ መርሃ-ግብር የኢንዱስትሪ ዘርፉን እድገት ለማሳለጥ የሚያግዙ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።
የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ማሳደግ የህልውና ጉዳይ እንደሆነ ገልጸው፣ አሁን የሰፈነው ሰላም የዘርፉን እንቅስቃሴ ለማጎልበት ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
"ባለፉት ዓመታት የሀገሪቱ ኤክስፖርት ምርት እያደገ መጥቷል" ያሉት ሚኒስትሩ፣ የኢንዱስትሪዎች ማደግ ለሥራ ዕድል ፈጠራ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ዳያስፖራዎች በሀገሪቱ የተለያዩ ክልሎች በተገነቡ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ገብተው የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግርን ከማፋጠን ባለፈ ለወጪ ምርቶች ማደግ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል።
"ለቀጣይ አምስት ዓመታት በተነደፈው ሀገራዊ የኢንዱስትሪ እድገት ስትራቴጂ መሰረት ለዘርፉ እድገት ርብርብ ይደረጋል" ያሉት አቶ መላኩ፣ ለስኬቱ የዳያስፖራው ማህበረሰብ ተሳትፎም ወሳኝ መሆኑን አመልክተዋል።
በተለይ በውጪ የሚኖሩ ዳያስፖራዎች በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ በስፋት ተሰማርተው ሀገራቸውንና እራሳቸውን እንዲጠቅሙ ምቹ ሁኔታ መኖሩን አንስተዋል፡፡
በአማራ ክልል 6 የኢንዱስትሪ አካባቢዎች ተለይተው መደራጀታቸውን የገለጹት ደግሞ የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሃላፊ አቶ እንድሪስ አብዱ ሲሆኑ ባላፉት ስድስት ወራት በክልሉ ከ344 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ 2ሺህ 575 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደዋል ነው ያሉት።
ባለሀብቶቹ በቀጣይ ወደ ሥራ ሲገቡ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩም አመልክተዋል።
"ኢትዮጵያ ታምርት" በሚል መሪ ሀሳብ በተካሄደው የኢንቨስትመንት ፎረም የከተማዋን የኢንቨስትመንት አማራጮች የሚያስተዋውቅ ጥናታዊ መረጃ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።
በኢንቨስትመንት ፎረሙ ላይ የፌዴራል፣ የክልል እና የጎንደር ከተማ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ ባሀለብቶችና በውጪ ሀገር የሚኖሩ ዳያስፖራዎች ተሳትፈዋል።
ምንጭ ፡-አሚኮ

19/01/2023

የአማራ ዳያስፖራ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በመላው ዓለም ለምትኖሩ የክርስትና ዕምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሙሉ መልካም የጥምቀት በዓል እንዲሆንላችሁ ይመኛል!

Amhara Diaspora Affairs Coordinating Office wishes Ethiopian Christians in the diaspora a happy Epiphany!

የአማራ ክልል ዳያስፖራ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በመላው ዓለም ለምትገኙ የዳያስፖራ አባላት በሙሉ አዲሱ የፈረንጆች  2023 ዓመት የስኬት  ዘመን እንዲሆንላችሁ ይመኛል!Amhara Diaspora ...
01/01/2023

የአማራ ክልል ዳያስፖራ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በመላው ዓለም ለምትገኙ የዳያስፖራ አባላት በሙሉ አዲሱ የፈረንጆች 2023 ዓመት የስኬት ዘመን እንዲሆንላችሁ ይመኛል!

Amhara Diaspora Coordinating office wishes to all Ethiopians in the diaspora a successful New Year 2023!

በባህር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ ገብታችሁ መስራት ለምትፈልጉ ባለሃብቶች የቀረበ ጥሪ !   *****ባሕርዳር፤ሕዳር 29/2015 ዓ.ም (ኢኢቢ) የባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ በፌደራል መንግስት ...
08/12/2022

በባህር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ ገብታችሁ መስራት ለምትፈልጉ ባለሃብቶች የቀረበ ጥሪ !
*****
ባሕርዳር፤ሕዳር 29/2015 ዓ.ም (ኢኢቢ) የባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ በፌደራል መንግስት ወጭና በክልሉ መንግስት ትብብር የመብራት፣የውኃ፣የቆሻሻ ማስወገጃ፣የእሳት አደጋ…ወዘተ) መሰረተ-ልማቶችና የአንድ ማዕከል አገልገሎት ተሟልቶለት ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል፡፡
ስለሆንም አሁን ላይ የተወሰኑ ሸዶች ለኪራይ ዝግጁ የሆኑ ስለሆነ ተከራይተው ለመስራት ፍላጎቱ ላላቸው ወይም በፓርኩ ውስጥ ባለው ከ3ኛ ወገን የፀዳ ክፍት መሬት ውስጥ የራሳቸውን ሸድ ገንብተው መስራት ለሚፈልጉ ባለሃቦች ጥሪ የቀረበ ስለሆነ አቅሙና ፍላጎቱ ያላችሁ ባለሃብቶች ጥያቄያችሁን ለክልሉ ለኢንዱስሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ በማቅረብ መነጋገር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Diaspora Coordinator Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share