21/03/2025
የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ መቋቋም ድርጅቶቹ ተወዳዳሪና ውጤታማ በመኾን አማራ ክልል እያጋጠሙት ያሉትን የምጣኔ ሃብት ችግሮች ለመቅረፍ ያስችላል፤
የልማት ድርጅቶቹ በነፃ ገበያው ላይ ተወዳድረው አሸናፊ መሆን እንዲችሉ በንግድ የስራ አመራር ጥበብ የሚመራ ሥርዓትን የሚመጥኑ ሁነው ሊደራጁ ይገባል፤
ድርጅቶች ለሕዝብ የሚያደርጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንዲሆን ዋናው ተልዕኳቸው ሃብት ፈጠራ ሊሆን ይገባል፤
(ክቡር ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ)
የአማራ ክልል በመንግሥት የልማት ድርጅቶች የልህቀት ማዕከል ይኾን ዘንድ በኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ደረጃ ተቋቁሞ አዳዲስ ኢንቨስትመንት ላይ መሠማራት ይጠበቅበታል፤
የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ "ድርጅቶች ለትውልድ ሀብት መፍጠርን ታሳቢ ያደረጉ እንዲሆኑና ከተደጋፊነት ወጥተው ራሳቸውን ችለው ትርፋማ እንዲኾኑ ያስችላቸዋል፤
የሚቋቋመው ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ አመራር መለኪያው ውጤታማነት በመሆኑ ትርፋማነት ላይ ትኩረት አድርጎ ይሰራል፤ ምክትል ርዕሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)
"ልማት ድርጅቶቹ ተገቢ ካልሆነ ጣልቃ ገብነት ነጻ ሁነው በቢዝነስ አስተሳሰብ እንዲመሩ ማድረግ ያስችላል፤"
የአመራር ክህሎትን ከፍ በማድረግና ትብብርን በመፍጠር ስኬታማ እንዲኾኑ ከማስቻሉም ባሻገር የሕዝቡን የመልማት ጥያቄዎች የሚፈቱ ያደርጋቸዋል፤ /የአማራ ፓይፕ ፋብሪካ ዋና ሥራ አሥኪያጅና የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ምሥረታ የጥናት ኮሚቴ ሠብሣቢ ወንዶሰን ጌታነህ/