Felege brhan police cominication

Felege brhan police cominication Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Felege brhan police cominication, Government Organization, Felege, Bahir Dar.

09/06/2021

በትራፊክ አደጋ የሠው ህይወት አለፈ
******************
በምስራቅ ጎጃም ዞን በፈለገ ብርሃን ንዑስ ወረዳ ፈለገ ብርሃን ከተማ ቀጠና አራት ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ ሰኔ 02/2013ዓ/ም ከጥዋቱ 1:30 ከባህርዳር ወደ አድስ አበባ ሲሄድ የነበረ ኢ.ት ኮድ 3 ሠሌዳ ቁጥር 85203 የሆነ የህዝብ ማመላለሻ አባይ ባስ መንገድ አቋርጠው በመሄድ ላይ ያሉ ሁለት ሠዎችን በመግጨት አንድኛዋ እዚያው ላይ ህይወቷ ያለፈ ሲሆን ሁለተኛዋ ደግሞ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባታል።
ስለሆነም አሽከርካሪዎች ፍጥነታችሁን ቀንሳችሁ አሽከርክሩ እያልን እግረኞች ደግሞ መንገድ ከማቋረጣችሁ በፊት ግራ ቀኛችሁን አይታችሁ ማቋረጥ እንዳለባችሁ እና ግራ መስመር ይዛችሁ እንድትጓዙ እንዲሁም ማቋርጥ ያለባችሁ በዘብራ መንገድ መሆኑን አውቃችሁ ለህብረተሰቡ ት/ት በመሥጠት እራሣችንን እና ህብረተሠባችንን ከትራፊክ አደጋ እንከላከል እያልን መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ።

የፈለገ ብርሃን ንዑስ ወረዳ ፖሊስ የኮሚኒኬሽን ክፍል

Send a message to learn more

02/01/2021

በፈለገ ብርሃን ንዑስ ወረዳ ከፀጥታ ሀይሎች ጋር ስለ ጥይት ተኩስ ውይይት ተደረገ
********************************************
በምስራቅ ጎጃም ዞን በፈለገ ብርሃን ንዑስ ወረዳ ታህሳስ 24 ቀን 2013ዓ/ም የ10(አስሩም) ቀበሌዎች የፀጥታ ሀይሎች በፈለገ ብርሃን ከተማ ስለ ጥይት ተኩስ እና ስለ ሌሎች የፀጥታ ስራ የውይይት መድረክ አካሂደዋል።
በውይይቱም የተነሡ ሃሳቦች የጥይት ተኩሥ እንዴት እናስቁም ፣ ያለ ዕድሜ ጋብቻን እንዴት እናስቁም፣ከባዕላት ጋር ተያይዞ ችግሮች እንዳይፈጠሩ እንዲሁም አካባቢያቸውን እንዴት መጠበቅ እንዳለባቸው ውይይ ተካሂዷል።ሰለዚህ ማንኛውም የፀጥታ ሀይል የተሰጠውን ተልእኮ በአግባቡ ተቀብሎ መፈፀም ያለበት መሆኑን የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል ።
ዋና ሳጅን ይልቃል አስሬ የፈለገ ብርሀን ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ኮሚኒኬሽን ሚዲያ ክፍል ተወካይ

02/01/2021

የፈለገ ብርሃን ንዑስ ወረዳ የፀጥታ ሀይሎ ስለ ጥይት ተኩስ ውይይት አደረጉ

በምስራቅ ጎጃም ዞን በፈለገ ብርሀን ንዑስ ወረዳ በፈለገ ዛቸና ቀበሌ ልዩ ቦታው እናት ጭየ ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ ታህሳስ 21ቀን 2013 ዓ/ም ከጠዋቱ 12:00 ስዓት ላይ ካሶኒ ሲኖ የጭነት...
30/12/2020

በምስራቅ ጎጃም ዞን በፈለገ ብርሀን ንዑስ ወረዳ በፈለገ ዛቸና ቀበሌ ልዩ ቦታው እናት ጭየ ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ ታህሳስ 21ቀን 2013 ዓ/ም ከጠዋቱ 12:00 ስዓት ላይ ካሶኒ ሲኖ የጭነት መኪና ሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 E T A04818 የሆነ መኪና ከአዲስ አበባ ወደ ጎንደር ፈሳሽ እና ደረቅ ሳሙና ጭኖ ሲሄድ ችግሩ ባልታወቀ ምክንያት በመገልበጡ የመኪናው ረዳት የአካል ጉዳት የደረሰበት ሲሆን ሹፌሩ መብራቱ አሰግዶም የተባለው ግለሰብ ህይወቱ አልፏል ።ስለሆነም አሽከርካሪዎች ፍጥነታችሁን በመቀነስ እና የትራፊክን ህግ በማክበር ማሽከርከር ያለባችሁ መሆኑን መልክታችንን እያስተላለፍን የእግረኛ ተጓዦችም ብትሆኑ ግራመስመራችሁን ይዛችሁ መንቀሳቀስ ያለባችሁ መሆኑን መልክታችንን እናስተላልፍለን።
የፈለገ ብርሀን ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ኮሚኒኬሽን ሚዲያ ክፍል ተወካይ

ዋና ሳጅን ይልቃል አስሬ

18/12/2020

አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
*******************በምስ/ጎ/አስ/ዞን/በፈለገ ብርሀን ንዑስ ወረዳ ወፊት ቀበሌ ነዋሪ የሆነዉ አቶ የኔሰው ያዉቃል(እንዳዉቄ) የተባለው ግለሰብ የ18 አመት ወጣት አስገድዶ በመድፈሩ የወረዳው ፖሊስ ፅ/ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ምርመራውን ሲያጣራ ቆይቶ የምርመራ መዝገቡን ለወረዳው ዐ/ህግ አቅርቦ ዐ/ህግም ምርመራ መዝገቡን በማየት በተከሳሹ ላይ ክስ መስርቶበት ሲከራከር ከቆየ በኃላ ታህሳስ 9 ቀን 2013 ዓ/ም ፈለገ ብርሀን ንዑስ ወረዳ ፍ/ቤት ቀርቦ 5(አምስት)አመት ፅኑ እስራት ተቀጣ።
ስለዚህ ማንኛውም የህብረተሰብ ክፍል ከእንደዚህ አይነት ድርጊት እራሱን እንዲከላከል እና ሌላውን ህብረተሰብ እንዲያስተምር ስንል መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ።

ዋ/ሳጅን ይልቃል አስሬ
የፈለገ ብርሀን ንዑስ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት ሚዲያ ክፍል

ሀሰተኛ የብር ኖት ይዞ የተገኘው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ    በምስ/ጎጃም ዞን በፈለገ ብርን ንዑሥ ወረዳ ፖሊስ  ጽ/ቤት አባላት ባደረጉት ድንገተኛ የመኪና ፍተሻ ህዳር 16/2013ዓ/ም ከረ...
04/12/2020

ሀሰተኛ የብር ኖት ይዞ የተገኘው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
በምስ/ጎጃም ዞን በፈለገ ብርን ንዑሥ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አባላት ባደረጉት ድንገተኛ የመኪና ፍተሻ ህዳር 16/2013ዓ/ም ከረፋዱ 4:30ግለሠቡ አቶ ከቤ አይጠገብ አድራሻው እነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ሠኞ ገብያ 016ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ከመርጦለ ማሪያም ወደ ሸበል በረንታ ሲሄድ 59400(አምሳ ዘጠኝ ሺህ አራት መቶ) ባለ200 ሀሰተኛ ብር ኖት መያዙን ከላይ በተጠቀሰው ቀን ያሥተላለፍን መሆኑ ይታወቃል ስለሆነም ግለሠቡን ለማረም በ24ሰአት ውስጥ የፈ/ብ/ን/ወረዳ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ክፍል ምርመራውን አጣርቶ ለምስ/ጎጃም ዞን ዐቃቢ ህግ ጽ/ቤት መዝገቡን በመላክ ዐቃቢ ህግም በተከሳሹ ላይ ክስ መስርቶ ለምስ/ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት መዝገቡን አቅርቧል ።
ፍርድ ቤቱም የተከሳሽን የእምነት ክህደት ቃል በመቀበል እና የዐቃቢ ህግ ምስክሮችን ቃል ከተቀበለ በኋላ በተከሳሹ ላይ ተከሳሹን ያስተምራል እንድሁም ሌላውን ማህበረሠብ ከእንደዚህ አይነት ወንጀል እንድቆጠቡ በሚል እሳቤ በተከሳሹ ላይ ህዳር 24 ቀን 2013 ዓ/ም በዋለው ችሎት በተከሳሹ ላይ የአምስት(5) ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ።
ይህን አስመልክቶ ማህበረሰቡ ከእንደዚህ አይነት ወንጀሎች እና ልዩ ልዩ ወንጀሎች እንዲቆጠቡ እናም ወንጀሎች ሲፈጸሙ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ መሥጠት ይኖርባቸዋል።
ዋ/ሳጅን ይልቃል አስሬ
የፈ/ብ/ን/ወ/ፖ/ጽ/ቤት የኮሚኒኬሽን ሚዲያ ክፍል
ወንጀልን በጋራ እንከላከል!!!

ዛሬ በቀን  16/03/2013ዓም  በፈለገ  ብርሃን  ንዑስ ወረዳ  ፈለገ ዛቸና ቀበሌ ልዩ ቦታው ችግኝ ጣቢያው ተብሎ ከሚጠራው ቦታ ላይ የፈለገ ብርሃን  ንዑስ ወረዳ የፖሊስ  አመራር እና ...
25/11/2020

ዛሬ በቀን 16/03/2013ዓም በፈለገ ብርሃን ንዑስ ወረዳ ፈለገ ዛቸና ቀበሌ ልዩ ቦታው ችግኝ ጣቢያው ተብሎ ከሚጠራው ቦታ ላይ የፈለገ ብርሃን ንዑስ ወረዳ የፖሊስ አመራር እና አባላት ባደረጉት ድንገተኛ የመኪና ፍተሻ ከጥዋቱ 4:30 ላይ በህዝብ ተሽከርካሪ አባ ዱላ መኪና ላይ ከመርጦለማሪያም ወደ ደብረ ወርቅ ተሳፍሮ በመሄድ ላይ ያለ አቶ ከቤ አይጠገብ ሽፈራው አድራሻው እነብሴ ሳር ምድር ወረዳ 016ቀበሌ ሠኞ ገብያ ነዋሪ የሆነው ግለሰብ ባለ200 (ሁለት መቶ) ብር ኖት 59.400(አምሣ ዘጠኝ ሺ አራት መቶ ብር)የሀሰተኛ ብር ኖት (ከለር ኮፒ)የተደረገ ብር ይዞ ሲንቀሳቀስ በፖሊስ በድንገተኛ የመኪና ፍተሻ በቁጥጥር ስር ውሏል። ስለዚህ ማንኛውም ህብረተሠብ በሀሰተኛ ብር እንዳይታለል እና እንዳይጭበረበር ጥንቃቄ እንድታደርጉ እና ሲያጋጥማችሁ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ እንድሰጡ እናሳስባለን። ዋ/ሳጅን ይልቃል አስሬ የኮሚ/ሚዲ/ክፍል

24/11/2020

ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን ለአማራ ክልል ልዩ ሀይል እና ሚኒሻ የፈለገ ብርሃን ወረዳ የፖሊሥ አባሎች 1500 ብር ድጋፍ አድርገዋል

23/11/2020

ውድ ደንበኞቻቸውን የተለያዩ ችግሮች ሲገጥማችሁ በዚህ ገፅ ታገኙናላችሁ

Address

Felege
Bahir Dar
121212

Telephone

+251928580783

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Felege brhan police cominication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share