Awabel Wereda Justice Office-አዋበል ወረዳ ዓቃቤ ህግ ጽ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Bahir Dar
  • Awabel Wereda Justice Office-አዋበል ወረዳ ዓቃቤ ህግ ጽ/ቤት

Awabel Wereda Justice Office-አዋበል ወረዳ ዓቃቤ ህግ ጽ/ቤት To creat legal awareness to the societies

11/04/2023

የከባድ ስርቆት ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች
በፅኑ እስራት ተቀጡ
ተከሳሽ 1ኛ.አቶ እንቻለዉ ጌታቸዉ 2ኛ. አቶ አዝመራዉ ወንድምነህ 3ኛ. አቶ ስናማዉ ዘዉዴ 4ኛ. አቶ ሙሉጌታ ፈንታ የተባሉት ተከሳሾች የኢፌድሪ የወንጀል ህግ 669/3/(ለ) ስር የተመለከተዉን በመተላለፍ በ28/07/2015 ዓ.ም በሌሊት ባልታወቀ ሰዓት በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር እነራታ/08/ ቀበሌ ልዩ ቦታዉ የብራጌ ተብሎ ከሚጠራዉ አካባቢ ላይ ንብረትነታቸዉ የአቶ ጌታቸዉ ብናልፍ የሆኑትን 04 (አራት) ከብቶች ቤት ከፍተዉ የሰረቋቸዉ በመሆኑ በፈፀመዉ ከባድ የስርቆት ወንጀል ተከሰዋል ሲል ዐ.ህግ ክስ መስርቶ አቅርቧል።
የአዋበል ወረዳ ፍርድ ቤት ለተከሳሾች መጥሪያ እንዲደርሳቸዉ በማድረግና በችሎት ቀርበዉ የክስ ቻርጅ ተነቦላቸዉ የእምነት ክህደት ቃላቸዉን እንዲሰጡ ሲጠየቁ ክሱን አንቃወምም፤ የወንጀሉንም ድርጊት ፈፅመናል በማለት በዝርዝር አምነዉ ቃላቸዉን የሰጡ በመሆኑና ዐ.ህግ በአስተያየቱ በአመኑት መሰረት የጥፋተኝነት ዉሳኔ ይሰጥልኝ በማለቱ ፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ዉሳኔ ከሰጠ በኋላ ማክበጃና ማቅለያ ምክንያት በመቀበል ተከሳሾችን ያርማል ሌለዉን የህብረተሰብ ክፍል ያስተምራል በሚል አራቱም ተከሳሾች እያንዳንዳቸዉ በ08 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ የአዋበል ወረዳ ፍርድ ቤት በ29/07/2015 ዓ.ም በዋለዉ ችሎት የቅጣት ዉሳኔ ሰጥቷል።
የአዋበል ወረዳ ፍርድ ቤት

የአዋበል ወረዳ ዐ/ህግ ጽ/ቤት እና ፍ/ቤት በቀን 27/04/2015 ዓ.ም በለጋ የሌቭ ቀበሌ የተካሄደ የህዝብ የምክክር መድረክ
09/01/2023

የአዋበል ወረዳ ዐ/ህግ ጽ/ቤት እና ፍ/ቤት በቀን 27/04/2015 ዓ.ም በለጋ የሌቭ ቀበሌ የተካሄደ የህዝብ የምክክር መድረክ

የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በፅኑ  እስራት ተቀጣ:-ተከሳሽ  ቂርቆስ ላመስግን ጌታነህ የተባለው የሉማሜ ከተማ ነዋሪ የሆነው የ23 ዓመት ወጣት በሉማሜ የመጀመሪያ ሆስፒታል ጥ...
22/12/2022

የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ:-
ተከሳሽ ቂርቆስ ላመስግን ጌታነህ የተባለው የሉማሜ ከተማ ነዋሪ የሆነው የ23 ዓመት ወጣት በሉማሜ የመጀመሪያ ሆስፒታል ጥበቃ ስራ ሲሰራ ጥቅምት 12 ቀን 2015 ዓ/ም ከሌሊቱ 7:00 ሰዓት ሲሆን በሉማሜ ከተማ የሉማሜ የመጀመሪያ ሆስፒታል ለወሊድ የመጣች ልጇን በማስታመም የመጣች እናትን አስገድዶ በመድፈሩ የሉማሜ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ምርመራውን አጣርቶ ለአዋበል ወረዳ ዐ/ህግ ልኳል::የአዋበል ወረዳ ዐ/ህግም ተከሳሹ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ.የወንጀል ህግ አንቀጽ 620/1/ ን በመተላለፍ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ፈፅሟል በማለት በአዋበል ወረዳ ፍ/ቤት ክስ መስርቶበት ተከሳሹም ፍ/ቤት ቀርቦ ሲጠየቅ የተከሰሰበትን የወንጀል ድርጊት ክዶ በመከራከሩ የዐ/ህግ ምስክሮች ቀርበው እንዲሰሙ ከተደረገ በኋላ ተከሳሹ እንዲከላከል ብይን ተሰጧል::ፍ/ቤቱም ተከሳሽም የመ/ምስክር አለኝ በማለቱ አስቀርቦ ከሰማ በኋላ የተከሳሽ የመ/ምስክሮች የዐ/ህግን ክስና ማስረጃ ማስተባበል ስላልቻሉ ህዳር 30 ቀን 2015 ዓ/ም ባዋለው ችሎት ተከሳሹን በወ/መ/ሥ/ሥ/ህግ አንቀጽ 149(1) መሠረት በተከሰሰበት ድንጋጌ ጥፈተኛ ነው በማለት የዐ/ህጉንና የተከሳሹን የቅጣት አስተያየት ተቀብሎ ተከሳሹን ያርማል ያስተምራልና ሌሎች መሠል አጥፊዎችን ያስጠነቅቃል ያስተምራል ያለውን የአምስት ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራ እንዲቀጣ በማለት የቅጣት ውሳኔ ሰጧል::

20/12/2022

አፍሮ በመጨረሻ ከአሜሪካ ሆኖ ሚሳይሉን አስወንጭፏል!

10/12/2022
05/12/2022

ሁለት ህፃናትን በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ ያደረገችው ህይወት መኮንን በሞት እንድትቀጣ ተወሰነ

ህዳር 26/2015 ዓ.ም የዋለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ሰው ግድያና ከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት ተከሳሿን በወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ 02/2006 መሰረት በእርከን 39 ስር በማሳረፍ በሞት እንድትቀጣ ሲል ወስኖባታል፡፡ በተከሳሽ ላይ የተወሰነው እስኪፈፀም ድረስ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንድትቆይ ሲል ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ በሴቶች እና ህጻናት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ ዳይሬክቶሬት ነሃሴ 26 ቀን 2014 ዓ/ም በለሚኩራ ክ/ከ አራብሳ ኮንዶሚኒዬም እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በቤት ሰራተኛነት ተቀጥራ በምትሰራበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የሁለት ህፃናትን ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲያልፍ አድርጋለች ሲል በከባድ የግድያ ወንጀል እና እንዲሁም ተከሳሽ የሟቾችን የቤተሰብ ሰነድ ማስረጃዎች ማጥፋት ወንጀል ጥቅምት 15 ቀን 2015 ዓ.ም በህይወት መኮንን ላይ ተደራራቢ ክስ መመስረቱ ይታወሳል፡፡

ተከሳሽ አስቀድማ ለፖሊስ በፖሊስ ጣያ እና በፍርድ ቤት የሰጠችውን የእምነት ቃል በዐቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶ ፍርድ በቤት ቀርባ ወንጀሉን ስለመፈጸሟ ስትጠየቅ “ድርጊቱን አልፈጸምኩም ጥፋተኛም አይደለሁም” በማለት ብትክድም ወንጀሉን ስለመፈጸሟ ዐቃቤ ህግ የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን አቅርቦ ለችሎቱ በማስረዳቱ፣ ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ሕግ ምስክሮች በክሱ ዝርዝር የተመለከቱትን ያስረዱ በመሆኑ ተከሳሽ በተከሰሰችባቸው ከባድ የሰው ግድያ እና ሰነድ ማጥፋት ወንጀል እንድትከላከል ብይን ቢሰጥም የመከላከያ ማስረጃ የለኝም በማለት የገለፀች በመሆኑ ፍርድ ቤቱ የጥፋተኝነት ፍርድ ሰጥቷል፡፡

ዛሬ ህዳር 26 ቀን 2015 ዓ.ም የተሰየመው ችሎትም ተከሳሽ ጥፋተኛ መባሏን ተከትሎ የዐቃቤ ህግን የቅጣት አስተያየትና የተከሳሽን የቅጣት ማቅለያ መርምሮ ውሳኔ የሰጠ ሲሆን፣ በዚህም ዐቃቤ ህግ በቅጣት አወሳሰን መመሪያ መሰረት ወንጀሉ ከባድ ደረጃ ተብሎ እንዲሰላለትና በሞት እንድትቀጣ አስተያየት ሰጥቷል፡፡

በተከሳሽ በኩልም ከዚህ ቀደም ወንጀል ፈፅሜ የማላውቅ፣ ወንጀሉን የፈጸምኩት ከእውቀት ማነስና ያልተማርኩ በመሆኔ መሆኑ፣ እጄን ለፖሊስ አምኜ የሰጠው በመሆኔ ከግምት ገብቶ ቅጣቱ ይቅለልልኝ በማለት 5 የቅጣት ማቅለያዎችን ከመንግስት በተመደበላት የተከላካይ ጠበቃ አማካኝነት የጠየቀች ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ማቅለያዋን አልተቀበለውም፡፡

ፍርድ ቤቱ ሌሎች አጥፊዎችን ያስጠነቅቃል በማለት ተከሳሿ በሞት እንድትቀጣ ሲል ወስኖባታል፡፡
የኢፌዴሪ ፍትህ ሚኒስተር

26/11/2022

የህክምና ትምህርት ሳይማር በሀሰት ማስረጃ "ዶክተር" ሆኖ ሲያገለግል የነበረው እና ሁለት ሰዎችን በስህተት ለሞት የዳረገው ሰው በእስራት ተቀጣ
።።።፨፨፨።።።
የጃዊ ሆስፒታል ቅጥር ሰራተኛ ሆኖ ሲያገለግል የነበረው የሀሰት ዶ/ር ጌትነት ወንድ አወቅ የተባለው ተከሳሽ በድሬዳዋ ዩንቨርስቲ ሳይማር በሜዲስን የዶክትሬት ዲግሪ እንደተማረ በሀሰት በተዘጋጀ የዶክትሬት ሰርቲፊኬት የትምህርት ማስረጃ አቅርቧል።

በአብክመ ጤና ቢሮ ከ4/2/2014-4/2/2019 ዓ.ም የሚያገለግል የሚል የሀሰት የሙያ ፈቃድ በመያዝ በአብክመ ጤና ቢሮ ስር ባሉት ሆስፒታሎች በማችንግ ፈንድ ኘሮግራም በJunior General Medical practitioner የቋሚ ቅጥር ማስታወቂያ ተወዳድሮ 50% በማምጣት በደረጃ 14 ብር 9056 እየተከፈለው ሲሰራም ነበር ነው የተባለው።

በህክምና የእውቀት ችግር ምክንያት በተፈጠረ ስህተት ሟች የተመኝ አምላክ የተባለችውን የ7 ወር ህፃን እና ሟች የኔወርቅ ደሳለው የተባለችውን የ25 ዓመት ወጣት ለሞት የዳረገ መሆኑምን ተመላክቷል።

በፈፀመው የሙስና ወንጀል መንግሥታዊ ወይም ህዝባዊ ድርጅት ሰነዶችን አስመስሎ ማዘጋጀት ወደ ሀሰት መለወጥ ወይም በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል ሙስና ወንጀል በዐ/ህግ ክስ ቀርቦበት በአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀን 15/3/2015 ዓ.ም በዳንግላ ከተማ ባስቻለው ተዘዋዋሪ ችሎት በ11ዓመት ፅኑ እስራት እና በብር 5,000 መቀጣቱን የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ አያና ታደለ አረግጠውልናል ።ምንጭ :-ANRS Suprem crt page

የአዋበል ወረዳ ዐቃቤ ህግ ጽ/ቤት ለቀበሌ ማህበራዊ ፍ/ቤት ዳኛች እና አስተዳደር ፀጥታዎች  በማህበራዊ ፍ/ቤት አዋጅና በአሠራር ጉዳይ በወጀል ከተማ    ስልጠና ሰጠ
08/06/2022

የአዋበል ወረዳ ዐቃቤ ህግ ጽ/ቤት ለቀበሌ ማህበራዊ ፍ/ቤት ዳኛች እና አስተዳደር ፀጥታዎች በማህበራዊ ፍ/ቤት አዋጅና በአሠራር ጉዳይ በወጀል ከተማ ስልጠና ሰጠ

12/02/2021
25/12/2020

ከባድ የስርቆት ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ:-
ተከሳሽ አሸብር/አየለ/ ዘበናይ የተባለው የደባይ ጥላት ግን ወረዳ ነዋሪ የሆነው የ20ዓመት ወጣት የማይገባውን ብልፅግና ለማግኘት በማሰብ ካልተያዘው ግብረ አበሩ ጋር በሆን ግንቦት 21 ቀን 2012 ዓ/ም ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት ሲሆን በአዋበል በዱቄ ቀበሌ ጋተነስ ከተባለ ቦታ የግል ተበዳይ አቶ ገበየሁ ይግረም ንብረት የሆኑትን አራት/4/በሬዎች የዋጋ ግምታቸው 58,000 የሆኑ በሬዎች በር ከፍቶ በመውሰዱ የአዋበል ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ምርመራውን አጣርቶ ለአዋበል ወረዳ ዐ/ህግ ልኳል::የአዋበል ወረዳ ዐ/ህግም ተከሳሹ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ.የወንጀል ህግ አንቀጽ 669(3)ለ ን በመተላለፍ ከባድ የሥርቆት ወንጀል ፈፅሟል በማለት በአዋበል ወረዳ ፍ/ቤት ክስ መስርቶበት ተከሳሹም ፍ/ቤት ቀርቦ ሲጠየቅ የተከሰሰበትን የወንጀል ድርጊት ሙሉ በሙሉ ስላመነ ፍ/ቤቱም ታህሳስ 15 ቀን 2013 ዓ/ም ባዋለው ችሎት ተከሳሹን በወ/መ/ሥ/ሥ/ህግ አንቀጽ 134(1) መሠረት ጥፈተኛ ነው በማለት የዐ/ህጉንና የተከሳሹን የቅጣት አስተያየት ተቀብሎ ተከሳሹን ያርማል ያስተምራልና ሌሎች መሠል አጥፊዎችን ያስጠነቅቃል ያስተምራል ያለውን የአራት/4/ ዓመት ፅኑ እስራ የቅጣት ውሳኔ ሰጧል::

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Awabel Wereda Justice Office-አዋበል ወረዳ ዓቃቤ ህግ ጽ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share