13/07/2023
ለባህርዳር ነዋሪዎች በሙሉ፦
በ2014 ዓ.ም በጎደለ ማህበር እናስገባለን በሚል በርካታ ሰወችን ሲያጭበረብሩ የነበሩ ደላሎች እንደነበሩ ይታወቃል።
በአሁኑ ሰዐት እግድ ባልተነሳበት ሁኔታ በፀጥታ መዋቅርም ሆነ በሲቪል ማህበረሰብ ስም እናደራጃለን በሚል፣ የኃላፊው ቤተሠብ፣ ወንድም፣ ጓደኛ ነኝ፣ አውቀዋለሁ፣ በሚልና ከጽፈት ቤቱ ሙያተኞች ጋር እግባባለሁ በማለት ህዝብን ገንዘብ ያለአግባብ ለመቀበል የሚንቀሳቀሱ ደላሎች መኖራቸዉን ጥቆማ ደርሶናል።
ስለሆነም መኖሪያ ቤት ፈላጊው ህዝብ እግድ ተነስቶ የህብረት ስራ ተቋሙ የማደራጀት ሥራ መጀመሩን በማሥታወቂያ እስኪገልጥ ህዝቡ ራሱን ከሌቦች እና አጭበርባሪዎች፤ ነጣቂዎች እንዲጠብቅ እያሳሰብኩ አስመሣይ ነጣቂዎች ሲገጥሟችሁ በአካባቢዉ ላሉ የፀጥታ አካላት ጥቆማ እንድትሠጡ ትብብራችሁን እንጠይቃለን።