Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service-Bahir Dar Branch

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service-Bahir Dar Branch This is official page of Ethiopian Pharmaceuticals Supply Agency Bahir Dar branch

20/12/2023

የሀዘን መግለጫ
⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳

የቅርንጫፋችን የስራ ባልደረባ የነበሩት አቶ ሆሴ ጌቴ ከሰኔ 6 ቀን 2006 ዓ.ም እስከ ግንቦት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ የመጋዘን ሀላፊ በመሆን እዲሁም ከሰኔ 1 ቀን 2013 ዓ.ም እስከ ህይወታቸው ህልፈት ድረስ የመድሀኒት እና የህክምና መሳሪያዎች ስርጭት ባለሙያ በመሆን በአዳማ ቅርንጫፍ አዳማ ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

ይሁን እንጂ አቶ ሆሴ ጌቴ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በአዳማ ሆስፒታል እና ሜዲካል ኮሌጅ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ታህሳስ 6 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።

ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለስራ ባልደረቦቻቸው መፅናናቱን እንመኛለን።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አዳማ ቅርንጫፍ

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አግልግሎት ባህርዳር ቅርንጫፍ የጤና ባለሙያዎች ተከታታይ የሙያ ማጎልበቻ ሰጭነት (CPD Provider) እውቅና ሰርትፍኬት አገኘ፡፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሲፒዲ ማ...
31/07/2023

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አግልግሎት ባህርዳር ቅርንጫፍ የጤና ባለሙያዎች ተከታታይ የሙያ ማጎልበቻ ሰጭነት (CPD Provider) እውቅና ሰርትፍኬት አገኘ፡፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሲፒዲ ማዕከል ፓናል ኦፍ ኤክስፐርት አባለት ሃምሌ 7/2015 ዓ.ም ቅርንጫፍ መስሪያቤቱን በአካል ተገኝተው በመገምገም፣ አስፈለጊውን መስፈርት አሟልቶ በመገኘቱ ከሃምሌ 20/2015 ዓ.ም ጀምሮ የCPD ማዕከልነት የእውቅና ሰርተፍኬት አግኝቷል፡፡

07/05/2023

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ERP ፕሮጀክት በመጀመሪያው ክፍል (Tranche One) 10 ሞጁሎች (Modules) ተግባራዊ ያደርጋል፡፡ እነዚህ ሞጁሎች የሽያጭ እና የስርጭት አስተዳደር (O2C)፣ የሰው ሀብት አስተዳደር (H2R)፣ የስራ አካባቢ ጤነነትና ደህንነት (EHS)፣ የፋይናንስ አስተዳደር (F2R), የግዥ ትንበያ (PI2Pr)፣ የትራንስፖርት ማናጅመንት (TM), የጥራት እና ቁጥጥር (I2R),፣ የግዥ አስተዳደር (P2P)፣ የመጋዘን እና የከምችት አያያዝ (S2S) እና የጥገና አስተደደር (In2Rep) ናቸው፡፡

23/08/2022
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አግልግሎት ባህርዳር ቅርጫፍ ግቢ በፎቶ::
08/08/2022

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አግልግሎት ባህርዳር ቅርጫፍ ግቢ በፎቶ::

በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው የእግር  ኳስ ውድድር የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አግልግሎት ሰሜን ምዕራብ ክላስተር ምስራቅ ክላስተርን 4ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ወደ ቀጣይ ዙር አልፏል፡፡የአግ...
04/08/2022

በቢሾፍቱ ከተማ በተካሄደው የእግር ኳስ ውድድር የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አግልግሎት ሰሜን ምዕራብ ክላስተር ምስራቅ ክላስተርን 4ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ወደ ቀጣይ ዙር አልፏል፡፡
የአግልግሎቱ ቅርንጫፎች ዋናው መስሪያ ቤትን ጨምሮ በሦስት ምድብ ተመድበው ውድድር በማካሄድ ላይ ይገኛሉ፡፡ ከየቡድኑ የሚያልፉ ክላስተሮች በነሃሴ አጋማሽ በጅማ ከተማ በሚካሄደው የዋምጫ ውድድር ላይ ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡

25/07/2022

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አግልግሎት ባህርዳር ቅርንጫፍ አመታዊ ቆጠራ ጨርሶ በ8/11/2014 ዓ.ም መደበኛ ስራውን ጀምሯል፡፡

28/05/2022

ሱክሳሚቶኒየም (Suxamethonium) የተሰኘው የሠመመን ሰጭ መድሃኒት ሰኞ ግንቦት 22/2014 ዓ.ም ጀምሮ ባህርዳር ቅርንጫፍ ሰር ላሉ ተቋማት ይሰረጫል!
በአለም አቀፍ የአቅርቦት ሰንሰለት ተግዳሮቶች ምክንያት ሰሞኑን እጥረት ይታይበት የነበረው ሱክሳሚቶኒየም የተባለው ሰመመን ሰጭ በመድኃኒት ወደ ሀገር ውስጥ ገብቶ ለቅርንጫፎች በመሰራጨት ላይ መሆኑንና ከሰኞ ግንቦት 22/2014 ዓ.ም ጀምሮ በቅርንጫፋቸን ስር ላሉ ጤና ተቋማት መሰረጨት እንደሚጀምር አቶ ማርልኝ አናውጤ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ባህርዳር ቅርንጫፍ ምክትል ስራ-አስኪያጅ ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት 37 ሺህ 500 ቪያል ሱክሳሚቶኒየም ከህንድ ወደ ሃገር ውስጥ አስገብቷል፡፡

21/05/2022
17/04/2022

በኢትዮጵያ መድሐኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ውስጥ የመጋዝን ኃላፊ ሆኖ ሲሰራ ድንገት በተደረገ ፍተሻ የዋጋ ግምታቸው ከ5 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ የሆኑ በሀገር ውስጥ በቀላሉ የማይገኙና አጅግ ውድ የሆኑ መድሐኒቶች ጎድለት የተገኙበት ግለሰብ በፅኑ እስራና በገንዘብ ቅጣት አንዲቀጣ ተወሰነበት ።

ሚካዔል ዘውገ ተሰማ የተባለው ተከሳሽ የሙስና ወንጀል ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ በመተላለፉ ነው በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ ዳይሬክቶሬት ጄነራል ክስ የተመሰረተበት ።

የቅጣት ውሳኔውን ያሳለፈው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ ወንጀል ችሎት ነው ።
ተከሳሹ በኢትዮጵያ መድሐኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ውስጥ የመጋዝን ኃላፊ ሆኖ ሲሰራ ታህሰስ 06/2014 ዓ.ም ከቀኑ 3፡00 ሰዓት ላይ በተደረገበት ድንገተኛ ኦዲት ወይም ፍተሻና ቆጠራ ሲካሄድ ከተረከበው መድሐኒት ውስጥ ለኩላሊት እና ለሾተላይ ህክምና አገልግሎት የሚውሉ የዋጋ ግምታቸው 5‚643‚997‚35 ( አምስት ሚሊየን ስድት መቶ አርባ ሶስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ሰባት ብር ከሰላሳ አምስት ሳንቲም ) የሚያወጡ Anti-Rho(D) Immune Globvilin 300 Mcg in 2ml vital injection የተባሉ መድሐኒቶችን አጉድሎ በመገኘቱ በፈፀመው ከባድ የአምነት ማጉደል ወንጀል ነው በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ ዳይሬክቶሬት ጄነራል ክስ የተመሰረተበት ።

ተከሳሽ በችሎት ቀርቦ ክሱ ደርሶትና ተነቦለት የእምነት ክህደት ቃሉን ሲጠየቅ ” እኔ ድርጊቱን አልፈፀምኩም ጥፋተኛም አይደለሁም ”ሲል ቃሉን ሰጥቷል ።

ዐቃቤ ህግ በበኩሉ የተከሳሽን ጥፋተኝነት ለፍርድ ቤቱ ያስረዱልኛል ያላቸውን ዝርዝር ሰባት የምስክሮች ቃል እና የሰነድ ማስረጃዎች በማቅረብ በበቂ ሁኔታ ለችሎቱ በማስረዳቱ ተከሳሽ ዐቃቤ ህግ ያቀረበበትን ክስ መከላከልና ማስተባበል ባለመቻሉ ግራ ቀኙን ክርክር ያዳመጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 5ኛ ወንጀል ችሎት በተከሳሽ ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፏል ።

በዚህም መሰረት ተከሳሽ ከዚህ በፊት የጥፋተኝነት ሪከርድ የሌለበት ߹የቤተሰብ አስተዳዳሪ ߹ የጤና እክል ያለበት መሆኑ በማስረጃዎች የተረጋገጠ ስለሆነ አራት የቅጣት ማቅለያዎች ተይዘውለት በ8 ዓመት ፅኑ እስራትና በ15 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ ተወስኖበታል ።

ከዚህ በተጨማሪ በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዐቃቤ ህግ ዳይሬክቶሬት ጄነራል በተቋም ላይ ሌሎች መሰል ወንጀሎች ተፈፅመው ከሆነና አንዳይፈፀሙ በማሰብ ከኢትዮጵያ መድሐኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑ ታውቋል ።

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service-Bahir Dar Branch posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share