የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ

  • Home
  • Ethiopia
  • Awassa
  • የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ

በሲዳማ ክልል የጤናው ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ዝግጅት ሥራዎች ተጠናክረው እየተከናወኑ መሆናቸው ተገለጸ የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሰኔ 6/2018 ዓ.ምበሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ በጤ...
13/06/2026

በሲዳማ ክልል የጤናው ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ዝግጅት ሥራዎች ተጠናክረው እየተከናወኑ መሆናቸው ተገለጸ

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሰኔ 6/2018 ዓ.ም

በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ በጤናው ሴክተር የአገልግሎትና የአስተዳደር ሪፎርም ዝግጅት ሥራዎችን በተመለከተ የግምገማና የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ የጤና ቢሮ የማኔጅመንት አባላት፣ የቢሮው የተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎች እና በሪፎርሙ ሂደት የተሳተፉ አካላት ተገኝተው የጤናው ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ዝግጅት ሥራዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።

በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ፦ በጤና ሴክተሩ እየተዘጋጀ ያለው የሪፎርም ሥራ ፈጣንና ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት፣ ዘላቂ ስኬት ለማስመዝገብ እና ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።

ኃላፊዋ አክለውም ሪፎርሙ ለተቋሙ ራዕይና ግቦች ስኬት ትልቅ ዕድል የሚፈጥር በማውሳት ፥ ሪፎርሙ በጤና ሴክተሩ ውጤታማነት፣ ተደራሽነትና የአገልግሎት ጥራት ላይ የሚያመጣው ለውጥ የክልሉን የጤና ልማት ወደ ከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሸጋግር ገልጸዋል።

እንዲሁም የሪፎርም እቅዱ ከሀገራዊ የጤና ፖሊሲዎችና የለውጥ አቅጣጫዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም ለስኬታማ ትግበራው ጠንካራ መሠረት እንደሚሆን አስረድተዋል።

ኃላፊዋ ለሪፎርሙ ሰነድ ዝግጅት አስተዋፅኦ ያደረጉ ኮሚቴዎችን በማመስገን፣ የቀሩ ሥራዎች በከፍተኛ ትኩረትና ትብብር ተጠናቀው ሪፎርሙ ወደ ትግበራ ምዕራፍ እንዲሸጋገር ጥሪ አቅርበዋል።

በመድረኩ የቀረበው ሰነድ በጤናው ሴክተር የሪፎርም መነሻዎች፣ ግቦች፣ ተግዳሮቶች፣ አስቻይ ሁኔታዎች እና በክልል ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ የለውጥ ሥራዎችን የዳሰሰ ሲሆን፣ በተለያዩ ኮሚቴዎች የተከናወኑ ተግባራትና በቀጣይ የትግበራ ምዕራፍ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይም ውይይት ተደርጓል።

በሪፎርሙ የሚዘረጉ ዘመናዊ የአሠራር ሥርዓቶችና ሲስተሞች ብቁና ተወዳዳሪ የጤና ባለሙያዎችን ለመፍጠር፣ ዘርፉን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለማሸጋገር እና ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።

በመድረኩ በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ አስተያየት ያቀረቡ ሲሆን፣ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል። በመድረኩ የአመራሩና የሰራተኞች ተነሳሽነት፣ ቁርጠኝነትና ተግባቦት ለሪፎርሙ ስኬት ወሳኝ መሆኑም ተገልጿል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
6/10/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር  ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የኦክሲጅን ፋብሪካን ጨምሮ 2.8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸውን  ፕሮጀክቶች  መርቀ...
13/06/2026

የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የኦክሲጅን ፋብሪካን ጨምሮ 2.8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸውን ፕሮጀክቶች መርቀው አገልግሎት አስጀመሩ ።

የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ሰኔ 6/2018 ዓ.ም

የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እና የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 2.8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተደረገባቸውን ዘመናዊ የህክምና፣ የምርምርና የአካባቢ ጤና ፕሮጀክቶች በይፋ አስመርቀዋል።

ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል ዘመናዊ ማዕከላዊ የቀዶ ሕክምና (ኦፕሬሽን) ማዕከል፣ ልዩ የቀዶ ጥገናና የጽንስ ሕክምና ከፍተኛ እንክብካቤ (ICU)፣ የጡት ወተት ባንክ፣ የክሊኒካል ሙከራ ዩኒት (Clinical Trial Unit) እንዲሁም የላቀ የህክምና ቆሻሻ ማቃጠያና የሀብት መልሶ ማግኛ ሥርዓት ይገኙበታል። ፕሮጀክቶቹ የሕክምና አገልግሎትን ለማዘመን፣ የምርምር አቅምን ለማጠናከር እና ለሕብረተሰቡ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለማቅረብ የሚያግዙ መሆናቸው ተገልጿል።

በምረቃው ስርነስርዓት ላይ የተገኙት ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ ባስተላለፉት መልዕክት ፦ በጤናው ዘርፍ እየተመዘገበ ያለው አበረታችና ወጪ ቆጣቢ ውጤት የተቋሙን ትልቅ አቅም እንደሚያሳይ ገልጸው፣ ወደፊትም ከዚህ የላቀ ስኬት እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።

ተመራቂ ፕሮጀክቶቹ የጤና አገልግሎትን ለማስፋፋት፣ የሕብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ እና ጥራት ያለው ሕክምና ለማቅረብ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸውም አስገንዝበዋል።

የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ መንግሥት በመላ ሀገሪቱ እያከናወናቸው ያሉ የጤና ልማት ሥራዎች ለሕዝብ ጥራት ያለው፣ ተደራሽና ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለማድረስ የታለሙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ዶ/ር መቅደስ አክለውም በተለይም የጤና ሥርዓቱ ከሕክምና አገልግሎት ባሻገር በመከላከል፣ በምርምር፣ በእናቶችና ሕፃናት ጤና እንዲሁም በአካባቢ ጤና ጥበቃ ዘርፎች ላይ ትኩረት በመስጠት እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ፣ በገለፃቸው፥ ፕሮጀክቶቹ የህክምና አገልግሎትን፣ የህክምና ትምህርትንና የጤና ምርምርን ለማሳደግ እንዲሁም ለህብረተሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ተገልጿል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ፍፁም ወልደገብርኤል በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው፣ ተመራቂ ፕሮጀክቶቹ ዩኒቨርሲቲውን በህክምና ትምህርት፣ በምርምር እና በልዩ ህክምና አገልግሎት ተወዳዳሪ ማዕከል ለማድረግ እንዲሁም ለነዋሪዎች የተሻለ የጤና አገልግሎት ለማቅረብ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ ገልጸዋል።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ፣ የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ፣ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ፣ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ፣ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ፣ የፌዴራልና የክልል መንግሥት ኃላፊዎች፣ የጤና ዘርፍ አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲውና የኮሌጁ አመራሮች፣ የጤና ባለሙያዎች፣ አጋር ድርጅቶች እና ሌሎች ክቡራን እንግዶች ተሳትፈዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
6/10/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

በጤናው ዘርፍ ሊከሰቱ የሚችሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችንና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ተቋማዊ ቅንጅትና ተጠያቂነት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ ።  የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሰኔ 4/2018 ዓ....
11/06/2026

በጤናው ዘርፍ ሊከሰቱ የሚችሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችንና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ተቋማዊ ቅንጅትና ተጠያቂነት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ ።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም

በጤናው ዘርፍ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች የሙስናና የብልሹ አሰራር ተግዳሮቶችን ለመከላከል ተቋማዊ ቅንጅት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ፤ በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት እና የቢሮው የውስጥ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት በ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ ተገልጿል።

የሲዳማ ክልል መንግሥት ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ በመልዕታቸው የጤናው ሴክተር ከፍተኛ የመንግስትና የሕዝብ ሀብት የሚንቀሳቀስበት፣ መድኃኒቶችና የህክምና ግብዓቶች በስፋት የሚዘዋወሩበት በመሆኑ ለሙስናና ለብልሹ አሰራር ተጋላጭ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

“የጤና ስራ የ24 ሰዓት አገልግሎት ነው” ያሉት ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ፣ ዘርፉ የሕዝብን ሕይወት ከመታደግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ስላለው በሁሉም ደረጃ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን፣ ሌብነትን፣ ስርቆትንና ቸልተኝነትን ለመከላከል በጋራ መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የሲዳማ ክልል ስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ዘላለም ለማ በበኩላቸው ፣ በጤናው ዘርፍ የአገልግሎት አሠጣጥ እና የሀብት አጠባበቅ ረገድ በአሁኑ ሰዓት መሻሻሎች ቢኖሩም አሁንም በአንዳንድ ተቋማት ሊቀረፉ የሚገቡ ብልሹ አሠራር ተግዳሮቶች መኖራቸውን ገልጸዋል ።

ከዚህ ጋር በተያያዘም ክብርት ኮሚሽነሯ ለህብረተሰቡ አገልግሎት ማነቆ የሚሆኑ የመድሃኒት አያያዝ ጉድለቶችን እና በአጠቃላይ የሀብት አያያዝ ከብልሹ አሠራር የጸዱ እንዲሆኑ ሁሉም የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል ።

ሙስናንና ብልሹ አሰራርን ከመፈጠሩ በፊት ለመከላከል በተቋማት ውስጥ ግልጽነት፣ ተጠያቂነትና ቀልጣፋ አሰራር የተረጋገጠበት የአስተዳደር ሥርዓት መገንባት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

መድረኩ ላይ የቢሮው የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት እና የቢሮው የውስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርበው ውይይት በማድረግ ፣ በቀጣይ የተሻለ አሠራር በሁሉም መዋቅሮች ደረጃ እንዲፈጠሩ ፣ በጤና ተቋማት ግልጽ አሰራርን በማስፈን፣ የሚመደበውን በጀት ከብክነትና ከጉድለት በመጠበቅ፣ ውጤታማ የሀብት አጠቃቀምን ማሳደግና የጤና ሥርዓቱን አቅም ማጠናከር ዋና ትኩረት እንደሚሆን አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠቃሏል ።

በመጨረሻም በመድረኩ ላይ የሲዳማ ክልል ምክር ቤት የሴቶችና ማህበራዊ ዘርፍ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ አየለች ሌዳሞ ፣ የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ፣ የሲዳማ ክልል ስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ወ/ሮ ዘላለም ለማ ፣ የክልሉ ጤና ቢሮ እና የፀረ ሙስና ኮሚሽን የማኔጅመንት አባላት፣ የዞን ጤና ዴስክ፣ የወረዳ፣ የሆስፒታሎች የስነምግባር ኦፊሰሮች እንዲሁም ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
4/10/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት ህክምና ማዕከል አገልግሎት ለማጠናከር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ገለፁ።የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሰኔ 03/2018 ዓ...
10/06/2026

የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት ህክምና ማዕከል አገልግሎት ለማጠናከር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ገለፁ።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም

የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ሀዋሳ የኩላሊት እጥበት ማዕከል ውስጥ ያሉ ታካሚዎችን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል።

ክቡር ከንቲባው በጉብኝታቸው በማዕከሉ ህክምና እየተከታተሉ የሚገኙ ታካሚዎችን በመጠየቅ በቀጣይ ድጋፍ ቢደረግልን በሚል ታካሚዎች ያነሷቸውን ጥያቄዎች በማድመጥ ምላሽ ሰጥተዋል።

በተለያየ የሀገራችን ክፍል አረጋውያንና ህፃናትን በመደገፍ ፈር ቀዳጅ የሆነችው ሲስተር ዘቢደር አሁን ደግሞ የኩላሊት እጥበት ማዕከልን በማስጀመርና በማስፋፋት ለወገኖቿ ደራሽ መሆኗን በተግባር እያሳየች በመሆኗ ያላቸውን አክብሮት እና ምስጋና ገልፀው፤

በማዕከሉ ህክምና እየተከታተሉ ያሉ ታካሚዎችም ከአቅም ውስንነት ጋር አያይዘው ያነሷቸውን ችግሮች ደረጃ በደረጃ ለመፍታት መንግስትም የድርሻውን እንደሚወጣ፣ ራሳቸውን ጨምሮ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ሙሉ አባል በመሆን አላማውን እንዲደግፉ ጥሪ በማስተላለፍ ድጋፋቸውን በፊርማቸው አረጋግጠዋል።

ታካሚዎቹ ላነሷቸውን ጥያቄዎች የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ተወካይ አቶ ሙንጣሻ ብርሀኑ ፣የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት ደቡብና ሲዳማ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ እና የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ የሀዋሳ ኩላሊት እጥበት ማዕከል አምባሳደር አቶ ዘመን ለገሰ እስካሁን የተኬደበትን ርቀትና በቀጣይ የሚሟሉ ጉዳዮችን አብራርተዋል።

ማዕከሉ የኩላሊት እጥበት ማዕከል ብቻ ሳይሆን ንቅለ ተከላም እንዲጀመር ለማድረግ የሆስፒታል ግንባታው በአጭር ጊዜ እንዲፋጠን ርብርብ እንደሚደረግ የገለፁ ሲሆን ሰኔን የኩላሊት ጤና ወር በማድረግም የአባላትን ቁጥር ወደ 50 ሺህ ለማድረስ ይሰራልም ብለዋል።

የሜሪጆይ ኢትዮጵያ መስራችና ስራ አስኪያጅ ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ እስካሁን ለማዕከሉ እየተደረገ ያለውን ድጋፍ አድንቀው በክቡር ከንቲባ ጥራቱ በየነ አማካኝነት ወደፊት ሊደረግ ለታሰበው እገዛ በታካሚ ወገኖችና ቤተሰቦቻቸው ስም አመስግነዋል።

በማዕከሉ ህክምናቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ታካሚዎች በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ህክምናውን ለማግኘት ለእንግልትና ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጉ እንደነበር አስታውሰው ፤ ማዕከሉ ይህን ጫና እንደቀነሰላቸውና ክፍያውም ዝቅተኛ መሆኑን ነገር ግን ካለባቸው የአቅም ውስንነት አንፃር ዛሬም የመንግሥትንና የወገኖቻቸውን ድጋፍ እንደሚሹ ጠይቀዋል።


የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
3/10/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

10/06/2026

ህይወት ታዳጊው ጉዞ !

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን የህክምና አገልግሎትን ጥራትና ተደራሽነት ተግባር የሚያሳየውን ይህንን አጭር ዶክመንተሪ ቪዲዮውን ይመልከቱ፣ ሀሳብዎን በኮሜንት ያካፍሉን፣ ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!





አይፓስ (IPAS)  ኢትዮጵያ ለሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ከ2.3 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የህክምና ግብዓቶችን ድጋፍ አደረገ  ።    የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሰኔ 1 /2018 ዓ.ምበሲዳማ...
08/06/2026

አይፓስ (IPAS) ኢትዮጵያ ለሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ከ2.3 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የህክምና ግብዓቶችን ድጋፍ አደረገ ።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሰኔ 1 /2018 ዓ.ም

በሲዳማ ክልል የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎቶችን ይበልጥ ለማጠናከር እና የእናቶችና ሕፃናት ጤና ውጤቶችን ለማሻሻል፣ አይፓስ ኢትዮጵያ (IPAS ) ከ2.3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የህክምና ግብዓቶችና ቁሳቁሶችን ለሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ አስረከበ።

ድጋፉን የተረከቡት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትልና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ በመልዕክታቸው ፦ ድጋፉ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎቶችን ተደራሽና ጥራታማ ለማድረግ ከሚደረጉ ጥረቶች አንዱ ሲሆን፣ በተለይም የእናቶችና ሕፃናት ጤና ውጤቶችን ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል” ብለዋል።

በዛሬው ዕለት የተደረገው ድጋፍ በፍላግሺፕ ደረጃ በሚከናወኑ ፕሮግራሞች በተለይም በጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም አማካይነት የIUCD አገልግሎትን ለማስፋፋት፣ የጤና ተቋማትን ዝግጁነት ለማሻሻል እና የአገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ ያለመ መሆኑም ተጠቁሟል።

አይፓስ ኢትዮጵያ የሲዳማ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ፕሮግራም መሪ አቶ ቴዎድሮስ ቶሎሳ በበኩላቸው፣ ድርጅታቸው የመንግሥትን የጤና ፖሊሲዎችና ስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎች በመከተል ከሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን ገልጸው፣የስነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎቶችን ለማጠናከር ተከታታይና በቂ የግብዓት አቅርቦት ወሳኝ መሆኑ ድጋፉ የህንን ግብ ለማሳካት ትልቅ አቅም እንዳለው አስረድተዋል፡፡

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
1/10/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ  የ2019 በጀት ዓመት ወረዳን መሰረት ያደረገ ዕቅድ  ማስጀመሪያ  ክልላዊ መድረክ ተካሄደየሲዳማ ክልል  ጤና ቢሮ ግንቦት 29/2018 ዓ.ምየሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የ...
06/06/2026

በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የ2019 በጀት ዓመት ወረዳን መሰረት ያደረገ ዕቅድ ማስጀመሪያ ክልላዊ መድረክ ተካሄደ

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ግንቦት 29/2018 ዓ.ም

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የ2019 በጀት ዓመት ወረዳን መሰረት ያደረገ የጤና ዕቅድ ዝግጅትን ለማጠናከርና በሁሉም የጤና ስርዓት ደረጃዎች የተቀናጀ አፈጻጸም ለማረጋገጥ ያለመ ክልላዊ መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ባስተላለፉት መልዕክት ፥ ቢሮው መረጃን መሠረት ያደረገ የጤና ሥርዓት ግንባታን እንደ ዋና ምሰሶ ወስዶ እየሠራ መሆኑን ገልፀዋል።

ዶ/ር ሰላማዊት አክለውም የሀገሪቱን የጤና ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ፕላን (HSTP-II) ከዓለም አቀፍ የልማት ግቦች ጋር በማቀናጀት የሚዘጋጁ ዕቅዶች የሕዝቡን ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጡ ጠቁመው፣ የክልሉን የጤና ሥርዓት ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር ለሀገራዊው የጤና ትራንስፎርሜሽን ግብ ስኬት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወቱ አስረድተዋል።

በተለይም የወረዳዎች ዕቅድ የሚዘጋጀው በትክክለኛ የመነሻ መረጃ (Baseline) ላይ ተመስርቶ መሆን እንዳለበት ገልጸው፣ የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ፣ የጤና ተቋማት አቅም፣ የአገልግሎት ሽፋን፣ የጥራት መመዘኛዎችና የልማት አጋሮች ድጋፍ በተገቢው ሁኔታ ተገምግሞ ወደ ዕቅድ ሊገባ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የተሻለ መረጃ፣ የተሻለ ዕቅድ፣ የተሻለ የጤና አገልግሎት” በሚል መርህ ታሳቢ ያደረገው ይህ ዕቅድ የሲዳማ ክልል የጤና ሥርዓት ለውጥን የሚያፋጥን መሠረታዊ ሰነድ እንደሚሆን ተጠቁሟል::

በመድረኩ በዕቅድ ዝግጅቱ ወቅት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም በጥልቀት እንደሚተነተን ተገልጿል። በዚህም የታዩ ጠንካራ አፈጻጸሞች፣ ያጋጠሙ ችግሮች፣ የመረጃ ክፍተቶችና ስጋቶች በመለየት ለ2019 በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም እንዲመዘገብ መሠረት ይጣላል ተብሏል።

መድረኩ ወረዳዎች በቀጣይ ለሚያዘጋጁት የጤና ዘርፍ ዕቅድ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን በማሰባሰብ እና የአፈጻጸም አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ተብራርቷል ።

የዕቅድ ሂደቱም “አንድ ዕቅድ፣ አንድ በጀት እና አንድ ሪፖርት” በሚለው መርህ ላይ ተመስርቶ በሁሉም የጤና ዘርፍ መዋቅሮች መካከል ተናባቢነትን ማጠናከር እንደሚጠበቅ በመድረኩ በተደረገው የጋራ ውይይት ተገልጿል።

በመጨረሻም በመድረኩ ላይ የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የማኔጅመንት አባላት፣ የቢሮው ተጠሪ ተቋማት፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ፣ እንዲሁም በዕቅድ ዝግጅቱ የተሳተፉ የቢሮው ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
29/09/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

በሲዳማ ክልል የወባ በሽታ ስርጭትን ለመግታት ህዝባዊ ንቅናቄ ለመፍጠር ያለመ የምክክር መድረክ ተካሄደየሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ግንቦት 29/2018 ዓ.ምበሲዳማ ክልል እየታየ የመጣውን...
06/06/2026

በሲዳማ ክልል የወባ በሽታ ስርጭትን ለመግታት ህዝባዊ ንቅናቄ ለመፍጠር ያለመ የምክክር መድረክ ተካሄደ

የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ግንቦት 29/2018 ዓ.ም

በሲዳማ ክልል እየታየ የመጣውን የወባ በሽታ ስርጭት በዘላቂነት ለመግታት፣ ለመቆጣጠርና የቅድመ መከላከል ሥራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ የምክክር መድረክ ተካሄደ::

ሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ ባስተላለፉት በመልዕክት፥ የወባ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በክልሉ ውስጥ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል። ሆኖም የአየር ንብረት ለውጥ በክልሉ የወባ በሽታ ስርጭትን እያስፋፋ በመምጣቱ በሽታውን ለመግታት የተቀናጀ ርብርብ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።

አቶ በላይነህ አክለውም ኢትዮጵያ በ2030 ወባን ለማጥፋት ያስቀመጠችውን ብሔራዊ ግብ ለማሳካት የህብረተሰቡ ንቁ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ ወባ ለህብረተሰቡ የጤናና የልማት እንቅፋት እንዳይሆን የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት የህብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግ ሥራዎች በሰፊው ሊጠናከሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በክልሉ ከፍተኛ የወባ ሥርጭት አለባቸው ተብለው በተለዩ 15 ወረዳዎችና በሌሎች የክልሉ አካባቢዎች የወባ መከላከልና ቁጥጥር ሥራዎች ውጤታማ እንዲሆኑ መላው ኅብረተሰብ፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የሚዲያ ተቋማት የሚጠበቅባቸውን ሚና በንቃት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደስታ ዶጊሶ በበኩላቸው፣ የመድረኩ ዋና ዓላማ በህብረተሰቡ ዘንድ ሰፊ ንቅናቄ በመፍጠር የወባ በሽታን በተቀናጀ መንገድ መከላከል መሆኑን ገልጸዋል።

ወባን ለመቆጣጠር በጤናው ዘርፍ ብቻ የሚደረግ ጥረት በቂ እንዳልሆነ የጠቀሱት ዳይሬክተሩ ሁሉም የመንግሥት መዋቅሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች፣ የሚዲያ አካላት ፣ የሃይማኖት ተቋማትና ህብረተሰቡ በትብብርና በቅንጅት ከሰሩ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል አስገንዝበዋል፡፡

ዳይሬክተሩ እንዳሉት፣ የህብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግና በወባ መከላከል ሥራዎች ውስጥ ተሳትፎውን ለማጠናከር የተለያዩ የተግባቦትና የማንቃት ሥራዎች እየተከናወኑና ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሁሉም የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል ። ወባን ለመከላከል ማህበረሰቡን ማሳተፍ፣ ማስተሳሰርና ባለቤትነት እንዲወስድ ማድረግ የላቀ ሚና እንዳለውም አክለዋል።

በመድረኩ ላይ የክልሉ የወባ በሽታ አሁናዊ ሁኔታ፣ በዞንና በወረዳ ደረጃ ያለው የበሽታ ስርጭት፣ ለወባ ተጋላጭነት መንስኤዎች፣ የቤት ውስጥ የጸረ-ወባ ኬሚካል እርጭት (IRS) ዘመቻ ዝግጁነት እንዲሁም የወባ ማጥፊያ መድኃኒቶችና የበሽታ መመርመሪያ መሣሪያዎች አቅርቦትን በተመለከተ ሰነዶች ቀርበዋል፡፡

በውይይቱም የወባ በሽታ መከላከል ሥራን ለማጠናከር የማህበረሰብ ተሳትፎና የተቋማት ቅንጅት ወሳኝ መሆኑ በቀረቡ አጀንዳዎች ዙሪያ በተደረገው ሰፊ ውይይት ተገልጿል፡፡
ወባን መከላከል የሁላችንም ኃላፊነት ነው፤ የአካባቢ ንጽህናን እንጠብቅ፣ አጎበሮችን ለታለመላቸው ዓላማ ብቻ እንጠቀም፣ ያቆሩ ውሃዎችን እናስወግድ፤ በጋራ በመረባረብ ከወባ የጸዳ ማህበረሰብ እንገንባ" ሲሉም አሳስበዋል።

በመጨረሻም በመድረኩ ላይ የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የማኔጅመንት አባላት፣ የቢሮው ተጠሪ ተቋማት፣ከከተማ አስተዳደር፣ ከዞን ጤና ዴስኮች፣ የወባ ጫና ከፍተኛ ከሆነባቸው ወረዳዎች የስራ ኃላፊዎች ፣ ሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሚዲያ አካላት እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
29/09/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

ከ3.5 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የሕክምና ቁሳቁሶች ለሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ተበረከቱየሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ግንቦት 28/2018 ዓ.ምየሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የእናቶች፣ የጨቅላ...
05/06/2026

ከ3.5 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የሕክምና ቁሳቁሶች ለሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ተበረከቱ

የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ግንቦት 28/2018 ዓ.ም

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የእናቶች፣ የጨቅላ ሕፃናትና የሕፃናት ጤና አገልግሎትን ለማሻሻል እንዲሁም የጤና ተቋማትን አቅምና ዝግጁነት ለማጠናከር ከ3.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የሕክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ ተቀብሏል።

ድጋፉን ያደረገው በአሜሪካ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ፣ በIMA World Health የሚመራና የሚተገበረው MOMENTUM Integrated Health Resilience (MIHR) ፕሮጀክት ነው።

የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ምክትልና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ በርክክቡ ወቅት እንደገለጹት፣ የተበረከቱት ቁሳቁሶች በአገር ደረጃም ሆነ በክልሉ ልዩ ትኩረት የሚሰጠውን የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናት ሞት ለመቀነስ ትልቅ ፍይዳ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡

አቶ በላይነህ አክለውም “የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናት ሕይወትን ለማዳን የሕክምና አገልግሎት ጥራትን ማስቀደም ወሳኝ ነው ፤ ይህ ድጋፍ ውጤታማና ዘላቂ የጤና አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ አቅም ይፈጥራል” ብለዋል:

ድጋፉ በክልሉ በሚገኙ አምስት ወረዳዎች ሥር የሚገኙ ጤና ተቋማት የሚያቀርቧቸውን የጤና አገልግሎቶች አፈጻጸም እና ጥራት ለማሻሻል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር አብራርተዋል፡፡

በሌላ በኩል የMIHR ሀዋሳ ማኔጀር አቶ አገኘሁ ገብሩ እንደገለጹት ፣ ፕሮጀክቱ በሀገርቱ ደረጃ ዝቅተኛ አፈጻጸም ያላቸውን ጤና ተቋማት በቁሳቁስ እና ሙያዊ ድጋፎችን ለማድረግ የተቀረጹ ስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎችን በተከተለ መልኩ እንደሆነ ጠቁመው ፤ በተለይም የጨቅላ ሕፃናትና የሕፃናት ጤና አገልግሎትን ጤና ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

አቶ አገኘው አክለውም በዚህ ዙር 41 ዓይነት የሕክምና ቁሳቁሶች መበርከታቸውንና በአጠቃላይ በግምት ከ3.5 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ የሚያወጡ መሆኑን ጠቁመዋል።

ድጋፉ የጤና ተቋማትን ዝግጁነት በማጠናከር፣ ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለማድረስ እንዲሁም የክልሉን የጤና ዘርፍ ስትራቴጂያዊ ግቦች ለማሳካት ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም በቁሳቁስ ርክክቡ ሥነ-ሥርዓት ላይ የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትልና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ፣ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደስታ ዶጊሶ እና የMIHR ሀዋሳ ማኔጀር እና ከፍተኛ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
28/09/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

04/06/2026

"የቤተሰብ ተኮር ጤና አገልግሎት“ በሲዳማ ክልል!

የቤተሰብ ተኮር ጤና አገልግሎት በማህበረሰቡ ደረጃ የፈጠረውን ግንዛቤ ተጠቅሞ በርካቶች የራሳቸውን ጤና በራሳቸው እንዲያመርቱ ከማድረግ ረገድ ፍይዳው ከፍ ያለ ነው::

ይህንን አጭር ዶክመንተሪ ቪዲዮውን ይመልከቱ፣ ሀሳብዎን በኮሜንት ያካፍሉን፣ ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!



የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share