13/06/2026
በሲዳማ ክልል የጤናው ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ዝግጅት ሥራዎች ተጠናክረው እየተከናወኑ መሆናቸው ተገለጸ
የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሰኔ 6/2018 ዓ.ም
በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ በጤናው ሴክተር የአገልግሎትና የአስተዳደር ሪፎርም ዝግጅት ሥራዎችን በተመለከተ የግምገማና የውይይት መድረክ ተካሂዷል።
በመድረኩ የጤና ቢሮ የማኔጅመንት አባላት፣ የቢሮው የተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎች እና በሪፎርሙ ሂደት የተሳተፉ አካላት ተገኝተው የጤናው ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ዝግጅት ሥራዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።
በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ፦ በጤና ሴክተሩ እየተዘጋጀ ያለው የሪፎርም ሥራ ፈጣንና ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት፣ ዘላቂ ስኬት ለማስመዝገብ እና ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
ኃላፊዋ አክለውም ሪፎርሙ ለተቋሙ ራዕይና ግቦች ስኬት ትልቅ ዕድል የሚፈጥር በማውሳት ፥ ሪፎርሙ በጤና ሴክተሩ ውጤታማነት፣ ተደራሽነትና የአገልግሎት ጥራት ላይ የሚያመጣው ለውጥ የክልሉን የጤና ልማት ወደ ከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሸጋግር ገልጸዋል።
እንዲሁም የሪፎርም እቅዱ ከሀገራዊ የጤና ፖሊሲዎችና የለውጥ አቅጣጫዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህም ለስኬታማ ትግበራው ጠንካራ መሠረት እንደሚሆን አስረድተዋል።
ኃላፊዋ ለሪፎርሙ ሰነድ ዝግጅት አስተዋፅኦ ያደረጉ ኮሚቴዎችን በማመስገን፣ የቀሩ ሥራዎች በከፍተኛ ትኩረትና ትብብር ተጠናቀው ሪፎርሙ ወደ ትግበራ ምዕራፍ እንዲሸጋገር ጥሪ አቅርበዋል።
በመድረኩ የቀረበው ሰነድ በጤናው ሴክተር የሪፎርም መነሻዎች፣ ግቦች፣ ተግዳሮቶች፣ አስቻይ ሁኔታዎች እና በክልል ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ የለውጥ ሥራዎችን የዳሰሰ ሲሆን፣ በተለያዩ ኮሚቴዎች የተከናወኑ ተግባራትና በቀጣይ የትግበራ ምዕራፍ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይም ውይይት ተደርጓል።
በሪፎርሙ የሚዘረጉ ዘመናዊ የአሠራር ሥርዓቶችና ሲስተሞች ብቁና ተወዳዳሪ የጤና ባለሙያዎችን ለመፍጠር፣ ዘርፉን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለማሸጋገር እና ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ጥራቱን የጠበቀ የጤና አገልግሎት ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።
በመድረኩ በቀረበው ሰነድ ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ አስተያየት ያቀረቡ ሲሆን፣ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል። በመድረኩ የአመራሩና የሰራተኞች ተነሳሽነት፣ ቁርጠኝነትና ተግባቦት ለሪፎርሙ ስኬት ወሳኝ መሆኑም ተገልጿል።
የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
6/10/2018 ዓ.ም
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ
Website: https://www.shb.gov.et
Facebook:
👇👇👇👇
https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/
Telegram : https://t.me/SidamaRHB
Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau
WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71
YouTube:
https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX
Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/