04/06/2026
ጾታ ተኮር ጥቃትን የመከላከል ሥራ አጠናክሮ መስራት እንደሚገባ ተገለፀ
ግንቦት 27/2018ዓ.ም
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የጾታ ተኮር ጥቃት ህክምና በሁሉም አከባቢዎች ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን አስታውቋል።
በሴቶች ላይ የሚደርሱ ፆታዊ ጥቃቶችን ለመከላከል የህግ አገልግሎቶችን ማጠናከር እንደሚገባም አቶ ዳዊት መንግስቱ ገልፀዋል።
በጤና ቢሮ የኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ዳዊት መንግስቱ እንደገለፁት የጾታ ተኮር ጥቃት ህክምና ባልተጀመረባቸው ሆስፒታሎች ስራውን ለማስጀምር እና የጾታ ተኮር ጥቃት የመከላከል ስራዎችን አጠናክሮ ለመስራት ዝግጅት ማጠናቀቃቸው ጠቁመዋል።
የጊዶሌ፣ ሶያማ እና አማሮ ኬሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች የጾታ ተኮር ጥቃት ህክምና ለማስጀመር ዝግጅት ማጠናቀቃቸውንም አውስተዋል።
በውይይት መድረኩ የጾታ ተኮር ጥቃት ጫና በክልሉ ያለውን ነባራዊ ሁኔታን በመዳሰስ የዘጠኝ ወር የጾታ ተኮር ጥቃት ህክምና እና መከላከል ስራ ሪፖርትን ተመልክተዋል።
በጤና ቢሮ የኤች አይ ቪ/ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ጆሹዋ አየለ በበኩላቸው የአንድ ማዕከል ህክምና አገልግሎትን በመስጠት ፆታ ተኮር ጥቃት ለመከላከል ከዚህ በበለጠ ልሰራ ይገባል ብለዋል።
በመድረኩ የጂንካ አጠቃላይ ሆስፒታል የተቀናጀ የአንድ መዕከል አገልግሎት አሰጣጥና ተሞክሮ ልምድ ለተሳታፊዎች አቅርበዋል።
የክልሉ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ እና ፍትህ ቢሮ የሴቶችና ህጻናት ልዩ ምርመራና ክስ ዳሬክቶሬት ዳሬክተር አቶ ለማላ አበረሃም የተቀናጀ የአንድ መዕከል አገልግሎት፣ ማቆያና ማገገሚያ ተቋማት ላይ ዝርዝር ተግባራትና መረጃ አቅርበው ተወያይተውበታል።
በቱርሚ፣ ጊዶሌ፣ ሶያማ እና አማሮ ኬሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች የጾታ ተኮር ጥቃት የተቀናጀ የአንድ መዕከል አገልግሎት መጀመር እንዳለባቸውም ተመክሯል።