Sidama National Regional State Health Bureau

Sidama National Regional State Health Bureau Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Sidama National Regional State Health Bureau, Government Organization, Awassa.

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠና ኮሜቴ ሊቀመንበር በመሆን ተመረጡ ____________ዶ/ር መቅደስ ሊቀመንበርነቱን ከማሊ የጤና እና ማህበራዊ ልማት ሚኒ...
25/08/2026

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠና ኮሜቴ ሊቀመንበር በመሆን ተመረጡ
____________

ዶ/ር መቅደስ ሊቀመንበርነቱን ከማሊ የጤና እና ማህበራዊ ልማት ሚኒስትር ኮሎኔል አሳ ባዲያሎ ቱሬ ተረክበዋል።

በ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና ጉባኤ የዛሬ ውሎ ሁለት የኮሚቴው ምክትል ሊቀ መንበሮችንም ሾሟል። የኒጀር የፐብሊክ የህዝብ ጤና እና ንፅህና ሚኒስትር ዶ/ር ጋርባ ሃኪሚ እና የዚምባብዌ የጤና እና የህፃናት እንክብካቤ ሚኒስትር ዶ/ር ዳግላስ ሞምቦሾራን ምክትል ሊቀመንበርነት አፅድቀዋል።

በጉባኤው ዘላቂነት ያለው የጤና ፋይናንስን በአፍሪካ በ2035 ማረጋገጥ የሚያስችል ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። የአፍሪካ የጤና የሰው ኃይል አጀንዳ የሰው ሃብት እጥረትን በ2035 ለመቅረፍ የባለሙያዎች ስልጠና ላይ ትኩረት ማድረግን እንደሚጠይቅ በመድረኩ ተገልጿል።

በተጨማሪም በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ሪጅናል ዳይሬክተር ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።



የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
ነሀሴ 19/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa

"በአፍሪካ ባለፈው 10 ዓመት በጤናው ዘርፍ በርካታ ውጤቶች ተመዝግቧል" የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ───የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠና...
25/08/2026

"በአፍሪካ ባለፈው 10 ዓመት በጤናው ዘርፍ በርካታ ውጤቶች ተመዝግቧል" የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ

───

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠና ጉባኤ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ስብሰባ ለኢትዮጵያ ትልቅ አጋጣሚ ነው ብለዋል።

አፍሪካ ባለፉት 10 ዓመታት በጤናው ዘርፍ በርካታ ውጤቶችን ማስመዝገቧንም አስታውሰዋል።

ጉባኤው ለአፍሪካ የተሻለ የጤና ሥርዓት ለመገንባት ያስችላል ያሉት ዶ/ር መቅደስ፤ በተለይም በኢትዮጵያ በጤና ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን አብራርተዋል።

የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ሽፋን መሻሻሉን እና በሰው ኃይል ልማት የተሠሩ ሥራዎችንም ገልፀዋል። ይህ ውጤት በቁጥር ከመገለፁም በላይ መሬት ላይ ማህበረሰቡን በተግባር ተጠቃሚ ማድረጋቸውን አስረድተዋል።

የዓለም ጤና ድርጀት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠና ጉባዔ መልዕክት አስተላለፉ ዶ/ር ቴድሮስ ባስተላለፉት የቪዲዮ መልዕክት
የኢትዮጵያን ሕዝብና መንግሥት መድረኩን በማዘጋጀታቸው አመስግነዋል።

በአፍሪካ በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡትን እድገቶች ያብራሩት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በአፍሪካ የጤና ሥርዓት ውስጥ ያሉትን ፈተናዎችም ዘርዝረዋል።

በስብሰባው ላይ ከሚዳሰሱት አጀንዳዎች አንዱ በጤናው ዘርፍ ዘላቂ የፋይናንስ አቅርቦት ላይ እንደሚያተኩር አክለዋል።

የዓለም ጤና ድርጀት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠና ጉባዔ መልዕክት አስተላለፉ የዓለም ጤና ድርጀት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በበየነመረብ በስተላለፉት መልዕከት የኢትዮጵያን ሕዝብና መንግሥት መድረኩን በማዘጋጀታቸው አመስግነዋል። በአፍሪካ በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡትን እድገቶች ያብራሩት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በአፍሪካ የጤና ሥርዓት ውስጥ ያሉትን ፈተናዎችም ዘርዝረዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ሪጅናል ዳይሬክተር ፕ/ር መሐመድ ጃናቢ በበኩለቸዉ 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጠና ጉባዔ ላይ የሚደረጉ ውይይቶች በአፍሪካ የሚገኙ 1.5 ቢሊዮን ሕዝቦች ጤናን የሚመለከቱ ናቸዉ ብለዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
ነሀሴ 19/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

በሲዳማ ክልል የጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶችና ግብዓቶች ጥራትን ለማረጋገጥ የ“ጤንነቴ” (Teninete) የሞባይል መተግበሪያ ትግበራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።              የሲዳማ ክ...
22/08/2026

በሲዳማ ክልል የጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶችና ግብዓቶች ጥራትን ለማረጋገጥ የ“ጤንነቴ” (Teninete) የሞባይል መተግበሪያ ትግበራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም.

በሲዳማ ክልል የጤናና ጤና ነክ አገልግሎቶችና ግብዓቶችን ጥራት ለማረጋገጥ፣ የመድኃኒት አቅርቦትና ስርጭትን በዘመናዊ የዲጂታል ሥርዓት ለመቆጣጠር የ“ጤንነቴ” (Teninete) የሞባይል መተግበሪያ ትግበራ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለጸ።

“ጤንነቴ” በክልሉ የሚገኙ ፋርማሲዎችና የመድኃኒት ችርቻሮ ተቋማት የመድኃኒት ክምችት፣ አቅርቦትና ስርጭት ሁኔታን በዲጂታል መንገድ ለመከታተልና ለመቆጣጠር የሚያስችል ሲሆን፣ የጤና ግብዓቶችን ጥራት በማረጋገጥና ሕገ-ወጥ ወይም ሐሰተኛ መድኃኒቶች ዝውውርን በመከላከል ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑ ተጠቁሟል።

የሲዳማ ክልል ጤናና ጤና ነክ አገልግሎትና ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ቡሪሶ ቡላሾ በመልዕክታቸው፦ “ጤንነቴ” የሞባይል መተግበሪያ የሀገሪቱንና የክልሉን የጤና ሥርዓት በቴክኖሎጂ ለማዘመን እንዲሁም የሕብረተሰቡን የመድኃኒት ፍላጎት በተገቢው ለመመለስ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ አቶ ቡሪሶ ገለጻ፣ መተግበሪያው የጤና ተቋማትና የግሉ የጤና ዘርፍ የሚያቀርቡትን አገልግሎት ቀልጣፋ፣ ግልጽና ከወረቀት ንክኪ ነፃ ለማድረግ ከሚከናወኑ የዲጂታላይዜሽን ሥራዎች አንዱ ነው።

ሥርዓቱ ዜጎች ጊዜና ጉልበታቸውን ሳያባክኑ በሕክምና ባለሙያ የታዘዘላቸውን ሕጋዊ መድኃኒት በአቅራቢያቸው ከሚገኙ ፋርማሲዎች በቀላሉ እንዲፈልጉና እንዲያገኙ ከማስቻሉም በላይ፣ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለቱን በግልጽነት ለመከታተል ያስችላል ብለዋል፡፡

በዚህ መሠረት በሀዋሳ ከተማ ከ251 የመድኃኒት ችርቻሮ ተቋማት የመድኃኒት ምዝገባና መረጃ ወደ ዲጂታል ሥርዓቱ የማስገባት ሥራ ተከናውኗል። በዚህም 32,416 የመድኃኒት አይነቶች መመዝገባቸውን በመግለጽ፣ የመድኃኒት ግዢ ሂደትም በኦንላይን መከናወኑ ተጠቁሟል።

የትግበራው ተስፋ ሰጪ ውጤት ይበልጥ ወደ ላቀ ውጤት እንዲሸጋገር፣ አመራሩን ጨምሮ የቁጥጥር ባለሙያዎች፣ የጤና ተቋማትና የግሉ የጤና ዘርፍ በቅንጅት መሥራትና የጋራ ቁርጠኝነትን ማሳየት እንደሚጠይቅም ተገልጿል።

“በጋራ ችግሮችን በመፍታት፣ አቅሞችን አሟጦ በመጠቀምና ሥራዎችን በየጊዜው በመገምገም የበለጠ ውጤት እያመጣን እንሄዳለን” ያሉት አቶ ቡሪሶ፣ ቀሪ ሥራዎችንም በተቀናጀ ክትትልና ቁጥጥር በስኬት ለማጠናቀቅ ቁርጠኝነቱ መኖሩን አስገንዝበዋል።

የሲዳማ ክልል ጤናና ጤና ነክ አገልግሎትና ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን በተለያዩ ክፍለ ከተሞች 10 የዘርፉ ባለሙያዎችን ያካተተ ቡድን በማቋቋም የትግበራ ሥራውን ሲያስፈጽም መቆየቱም ተገልጿል።

በቀጣይም የድጋፍና ክትትል ሥራዎችን በማጠናከር፣ በትግበራ ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን በየደረጃው በመለየትና ተገቢውን የመፍትሔ አቅጣጫ በማስቀመጥ ሥርዓቱን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ በውይይቱ ተጠቁሟል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
ነሀሴ 16/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

በሲዳማ ክልል የእናቶችና ሕፃናት ጤና እና የወባ መከላከልን የሚያጠናክር የሦስት ዓመት ፕሮጀክት ማስተዋወቂያና ማስጀመሪያ  መርሃ ግብር  ተካሄደ ሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ  ነሐሴ 14/2018 ዓ...
20/08/2026

በሲዳማ ክልል የእናቶችና ሕፃናት ጤና እና የወባ መከላከልን የሚያጠናክር የሦስት ዓመት ፕሮጀክት ማስተዋወቂያና ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ

ሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ነሐሴ 14/2018 ዓ.ም.

በሲዳማ ክልል የእናቶች፣ የሕፃናት፣ የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ጤናን እንዲሁም የሥርዓተ ምግብ አገልግሎትን ለማሻሻል፣ የወባ በሽታን በዘላቂነት ለመከላከል፣ የጤና ኤክስቴንሽን ፍኖተ ካርታን ለማስፈጸምና የማኅበረሰብ ተሳትፎን ለማጠናከር ያለመ በጤና አጋር ድጋፍ የሚተገበር የሦስት ዓመት ፕሮጀክት በይፋ ተጀምሯል።

ፕሮጀክቱ በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ እና በJSI Research & Training Institute ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን፣ ከፍተኛና መካከለኛ የወባ ስጋት ባለባቸው፣ በእናቶችና ሕፃናት ጤና ላይ በተለይም በወሊድ አገልግሎት አፈጻጸም ዝቅተኛ በሆነባቸው እና ተጨማሪ ድጋፍ በሚያስፈልጋቸው ሦስት የተመረጡ ወረዳዎች(በወንዶ ገነት፣ ደራራ እና ቦርቻ) ይተገበራል።

የፕሮጀክቱ ማስጀመሪያና የሥራ ውይይት መድረክ በሲዳማ ክልል ጤና ቢሮና JSI Research & Training Institute ትብብር ተካሂዷል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ፣ በክልሉ በእናቶችና ሕፃናት ጤና ላይ ትኩረት ተሰጥቶ በመሠራቱ በመከላከል የሚቻሉ ምክንያቶች የሚከሰቱ የእናቶችና የጨቅላ ሕፃናት ሞት በመቀነስ የተሻለ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።

አዲሱ ፕሮጀክትም የተመዘገቡትን ውጤቶች ማስቀጠልና ማስፋት ላይ በማተኮር፣ የእናቶች፣ የሕፃናት፣ የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ጤና፣ የሥርዓተ ምግብ እና የወባ መከላከል ሥራዎችን በማቀናጀት የተሻለ የጤና ውጤት ለማስመዝገብ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር አቶ በላይነህ ገልጸዋል።

በቀጣይም የጎጥ ጤና መሪዎችን፣ የሴቶች ልማት ህብረቶችንና ሌሎች የማኅበረሰብ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የጤና መረጃና አገልግሎትን በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ ለማድረስ የተቀናጀ ሥራ መሥራት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የJSI IPHCSD፣ SSD , & regional program coordinator & RMNCH ተጠሪ ወ/ሮ ምንትዋብ ዘነበ በበኩላቸው፣ ፕሮጀክቱ በተመረጡት ወረዳዎች የባህሪ ለውጥ ተግባቦት (SBCC) በመጠቀም የማኅበረሰቡን የጤና ግንዛቤ ለማሳደግ፣ በቤት ውስጥ የሚወልዱ እናቶችን ቁጥር ለመቀነስና የተቋም ውስጥ ወሊድን ለማሳደግ እንደሚሠራ ገልጸዋል።

በፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ መድረክ አጠቃላይ ዓላማው፣ የሚጠበቁ ውጤቶችና የትግበራ አቅጣጫዎች ቀርበዋል። በተጨማሪም የእናቶችና ሕፃናት ጤናንና የወባ በሽታ መከላከልን ለማጠናከር የተዘጋጁ ሰነዶችና አዲሱ የጤና ኤክስቴንሽን ፍኖተ ካርታ ቀርበው ተወያይተዋል።

ፕሮጀክቱ የጤና አገልግሎቶችን ከማኅበረሰቡ ፍላጎት ጋር በማጣጣምና በጤና ተቋማትና በማኅበረሰቡ መካከል ያለውን ትስስር በማጠናከር የእናቶችና ሕፃናት ጤናን፣ የወባ መከላከልን እና ዘላቂ የጤና ውጤትን ለማስመዝገብ አቅም እንደሚፈጥር ተብራርቷል ።

በመድረኩ የጤና ቢሮ ማኔጅመንት አባላትና ዳይሬክቶሬቶች፣ የሲዳማ ልማት ማኅበር ኃላፊና ባለሙያዎች፣ የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የዞንና የወረዳ ጤና ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች፣ የቀበሌ አስተዳደር ተወካዮችና የአጋር ድርጅቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
ነሀሴ 14/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

14/08/2026

እናት ደህና፣ ልጅም ጤና!

የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ በእናቶችና ሕፃናት ጤና ያስመዘገበውን ለውጥና ውጤት የሚያሳይ ይህንን አጭር ዶክመንተሪ ቪዲዮውን ይመልከቱ፣ ሀሳብዎን በኮሜንት ያካፍሉን፣ ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
ነሀሴ 8/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

100 barri fayyimmate loossa handaari mixo lifixxinota ikkite dagooma horaameette assitannota xawinsi.Woxawaajje 6/2018 M...
12/08/2026

100 barri fayyimmate loossa handaari mixo lifixxinota ikkite dagooma horaameette assitannota xawinsi.

Woxawaajje 6/2018 M.D Fayyimmate Biiro

Qoqqowoho Ayr/ Paartete Sooreessinni Kalaa Abraami Marshaalonni massagantinoti 100 barri millimmote kakkayishshi barera shiqqinoti Fayyimmate Biiro mixo loosu aana hosse dagoomu horaamimma buuxissannota kulloonni.

Konnirano Qoqqowu Fayyimmate Biiro gede aananno 100 barrira konni woroonni noo bixxilluwa loosu aana hosiisate mixi’noonni .

👉 Taraabbannonna taraabbannokki dhiwanna ittisatenna gargarate loossa
Fayyimmanna fayyimma labbanno owaantena udiinnu qorqorsha assatenni hattono fayyimmate gawajjo abbitara dandiitanno dhiwanna xiinxallotenni irkisatenninna badatenni horrote ikkito ittisatenni lifixxino owaante aate akata injiino garinni jeefisate illacha tunge loonsoonni.

👉 Co'itte ikkitino fayyimmate uurrinshuwa yaano fayyimmate xaawubbanna hospitaaluwa kalaqa

👉 Owaante woyyitinota assa

👉 Gibiaatete qorqorshanna shiqo woyyeessa

👉 Dijitaale teknolooje horoonsi'ratenni woyyinore loosa

👉 Kuri loossa deerra deerraho afantanno tantanubba loosonsa loossanno gede assa
Gobbate deerrinni worroonni wodho bikkaasinchinni keenneenna qaddo ikkitinno woraada kiirotenni 5 kalaqa

👉 Luphiima guma maareekkisiisse qaddo ikkitinno fayyimmate uurrinshubba kiirotenni 31 ikkitannota kalaqa

👉 Qaddo ikkitinno oluubba fayyimmate ekistenshiine pakeejjubba ikkadimmatenni gumulinore 60 kalaqa.

👉 Fayyimmate uurrinshara qajeeltino fayyimmate ogeeyyenni uuynanni ilate owaante 93% ikkanno amuwi mixotenni illanno gede assa.

👉 Maatete jireenyi qaacha kaalaqa
Fayyimmate uurrinshubbara xagichunna looso harisate ikkado woxi gaamme egensiisa umi bocira hasiisannoha 100% dirrisa.

👉 Dagate Xagichi Mine fantinokki woradda ikkado baajeette amadde fantanno assa
Fayyimmate xaawubbaranna hospitaalubbate qara qara hasiissanno xagicho uurrinshubbate afirate bikka 90% iillisha.

👉 Fayyimmate Xaawanna Fayyimmate Keellubba (110) gatamarsha hasirannoha dagate millimillo assatenni 100% mucci asse guda hattono xaphooma Fayyimmate keella mittu mittunku woradi mitticho mixire dagate millimillonni hanafanno assa

👉 Amubulaansubba uurritinota baalante woraddara 100% gatamarante loosu aana hossanno assa .

👉 Dagooma hanqaffino fayyimmate woowe buxichu buxichira amandanni woxe woraddatenna qoqqowu qeecha amada hattono Dagooma hanqaffino fayyimmate woowe miilla kalaqate assinannita balaxote qixxaawo gudatenni loosu giddora ea

👉 Fayyimmate uurrinshubbara looso harisate ikkanno woxe mitte hospitaalera 1 miloone hattono mittu fayyimmate xaawira 600 kume birra mixote amada

👉 Fayyimmate uurinshubbara heedhanota laabratoorete owaante deerrase agadhitinota assate hasiissanno irko assa
Fayyimmate haandari hawadi dancha fajjo owaante loossa gumulate amandoonni mixo garinni baalantanni haja jeefisa hattono Hawadi yanna mundee gamba assa

👉 Hawaasi Quchumira hedhanota fayyimmate xaawubbanna hospitaalla womunni woma dijitaale assa hattono Hawaasi Quchumira heerano xagicho dagoomu fayyimanke/teninete ጤንነት/ yinannita dijitaale appe horoonsire afiranno assa/ baalantinni uurrinsha loosu giddora eanno gede kaajjisha

👉 Dillaloote gadi soorro ha'runsite kalaqama dandiitannota fayyimmate mitiimmuba balaxe huwatatenni dagate huwanyoote baalante woraddara kalaqa.

👉 Shoolu woradira shekkeere luphi yite leeltannowa hasiissanno irko assatenni kemikaalete kiifatto harinsanni
Hooro akaata affidhinno fayya 1 bari gido reporte assatenni 7 bari gido urisate loonsanni hajo balauku huwanyte afire gumulanno assa

👉 Halallaho shumate ofolatenni wolaphino (74) olla kalanqe waajo baandeera qasa

👉 HIV/ADIS 0.5% baalanti woradda wodhote garinni murtanno assanna harunsite baanke muramino woxe 100% eessitanno assanna horaameeyye mommoddo nookkiha horoonsidhanno assa hattono HIV/ADIS 0.5% konni albaanni murroonniha hafanfarre kalaqantinowa harunsine qorqorsha assa


የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ
ነሀሴ 6/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

የ2018 በጀት ዓመት የጤና ስኬትን ወደ ሞዴል ደረጃ ማሸጋገር የ2019 በጀት ዓመት ዋነኛ ትኩረት ነው — አቶ በላይነህ በቀለሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ — ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም.በሲዳማ ክልል ...
11/08/2026

የ2018 በጀት ዓመት የጤና ስኬትን ወደ ሞዴል ደረጃ ማሸጋገር የ2019 በጀት ዓመት ዋነኛ ትኩረት ነው — አቶ በላይነህ በቀለ

ሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ — ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም.

በሲዳማ ክልል በእናቶችና ሕፃናት፣ በአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ጤና እንዲሁም በሥርዓተ ምግብ ዘርፍ በ2018 በጀት ዓመት የተመዘገበውን ስኬት ማስቀጠልና ወደ ሞዴል ደረጃ ማሸጋገር የ2019 በጀት ዓመት ዋነኛ የሥራ አቅጣጫ መሆኑን የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራሞች ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ ገለጹ።

አቶ በላይነህ ይህን ያሉት የቢሮው የእናቶችና ሕፃናት፣ የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ጤና እንዲሁም የሥርዓተ ምግብ ዳይሬክቶሬቶች የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት መድረክ ላይ ነው።

እንደ አቶ በላይነህ ገለጻ፣ በ2018 በጀት ዓመት በእናቶች፣ በሕፃናት፣ በአፍላ ወጣቶችና በሥርዓተ ምግብ ጤና ዘርፎች ከቀደመው ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ተመዝግቧል። ይሁን እንጂ የተገኘው ውጤት መድረሻ ሳይሆን ለቀጣይ ስኬት መነሻ መሆኑን ጠቁመዋል።

የተመዘገበውን ለውጥ ለማስቀጠልና ወደ ሞዴል ደረጃ ለማሸጋገር በተቀናጀ አሠራር፣ በተጠናከረ ክትትልና በሁሉም አካላት የጋራ ርብርብ መሥራት እንደሚገባ ገልጸዋል። በ2018 በጀት ዓመት የተጀመረው ቅንጅታዊ አሠራርም በ2019 ይበልጥ እንደሚጠናከር አስታውቀዋል።

በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት የአፈጻጸም ሰነዶችና የድጋፍ ክትትል ሪፖርቶች ቀርበው ተገምግመዋል። የቀጣይ ዓመት አቅጣጫዎችም በሰነድና በባነር ኤግዚቢሽን ቀርበዋል።

በተጨማሪም በ2018 በጀት ዓመት በእናቶችና ሕፃናት፣ በአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ጤና እንዲሁም በሥርዓተ ምግብ የተመዘገቡ ውጤቶችና ተሞክሮዎች በዶክመንታሪ ቀርበዋል።

በ2018 በጀት ዓመት ለተመዘገበው የጤና ስኬት አስተዋጽኦ ላደረጉ ወረዳዎች፣ የጤና ልማት አጋሮች፣ የጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞች፣ የግል የጤና ተቋማትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በሜዳሊያና በሰርተፍኬት እውቅና ተሰጥቷል።

በተለይም ለእናቶችና ሕፃናት ጤና በግል ተነሳሽነትና በልዩ ትጋት ላበረከቱ ግለሰቦች ልዩ እውቅና ተሰጥቷል። ከእነዚህም የእናቶች፣ ሕፃናት፣ ወጣቶችና ሥርዓተ ምግብ ጤና አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ኢመላ ላሜቻ፣ ዳይሬክቶሬቱን በተሳትፎና ቅንጅት በመምራታቸው በዳይሬክቶሬታቸው እውቅና አግኝተዋል።

አቶ በላይነህ በቀለ በማጠቃለያ ንግግራቸው በበጀት ዓመቱ የተሰጠው እውቅና በእናቶችና ሕፃናት፣ በአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ጤና እንዲሁም በሥርዓተ ምግብ የተመዘገቡ ውጤቶችን መሠረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይም እንደ ሴክተር አጠቃላይ ግብ በቀደሙት ዓመታት የተሞከሩ ኢኒሼቲቮችና የተመዘገቡ ስኬቶች በመነሻነት፣ በአራተኛው ምዕራፍ ጥራት ያለውና ሞዴል የሆነ ተደራሽና ዘመናዊ የጤና አገልግሎትን የሚያረጋግጥ ሞዴል የጤና ሥርዓት መገንባት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በመጨረሻም የ2018 በጀት ዓመት ስኬቶችን በማጠናከር፣ የታዩ ክፍተቶችን በተግባራዊ መፍትሔ በመሙላትና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዶችን በውጤታማነት በመፈጸም የተሻለ የጤና ውጤት ለማስመዝገብ በቅንጅት ለመሥራት ተስማምተው መድረኩን አጠናቀዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
ነሀሴ 5/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

በክልላችን የተጀመሩ የአረንጓዴ አሻራ ቱርፋቶች ከሥነ-ምህዳር ጥገና እና ከላቀ ኢኮኖሚያዊ እድገት ባሻገር ለጤናማ ትውልድ ግንባታ መሰረት ነው።የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ነሀሴ 05/2018 ዓም ...
11/08/2026

በክልላችን የተጀመሩ የአረንጓዴ አሻራ ቱርፋቶች ከሥነ-ምህዳር ጥገና እና ከላቀ ኢኮኖሚያዊ እድገት ባሻገር ለጤናማ ትውልድ ግንባታ መሰረት ነው።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ነሀሴ 05/2018 ዓም

በሀገራችን ብሎም በሲዳማ ክልል የተጀመሩ የአረንጓዴ አሻራ ቱርፋቶች ከሥነ-ምህዳር ጥገናና ከላቀ ኢኮኖሚያዊ እድገት ባሻገር በጤና የበለፀገ ትውልድ ለማፍራት መሰረት መሆኑን "ተስፋን እንትከል" በሚል መርህ ሀገራዊ ግብን ለማሳካት የተደረገው ርብርብ ማሳያ ነው።

በሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ አመታት ወዲህ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና አካባቢያዊ ሽግግር ለማፋጠን እየተሰሩ ባሉ ስራዎች እንደ ክልልም ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መመዝገባቸው ፣ በተለይም ምድሪቷን አረንጓዴ በማልበስ ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖን የመቋቋም፣ ምርትና ምርታማነትን በመጨመር የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ እና የሁለንተናዊ ዕድገት መሠረት የመጣል ግዙፍ ሀገራዊ ራዕይ ይዞ የተነሳው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ-ግብር ጤናማ ና ደስተኛ ትውልድ ለማፍራትም መሰረት በመሆን ላይ ይገኛል ።

የተመጣጠነ ምግብ ለጤና ከሚኖረው ፋይዳ አኳያ ታይቶ በክልሉ የተቀረጹ የቤተሰብ ብልፅግና ኢንሼቲቮች እና ፓኬጆች በመታገዝ እየተተገበሩ ያሉ የሌማት ትሩፋት ስራዎች ፣ የተፈጥሮ ሀብት ልማትና አረንጓዴ አሻራን ከማጠናከር ባሻገር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ማህበረሰቡ በፕሮቲን የበለፀጉ ምግቦችንና ፍራፍሬዎችን በጓሮው እንዲያገኝ የሚያስችል ስራ በርብርብ እየተመራ ይገኛል ።

ስለ ስርዓተ-ምግብ ጠቀሜታ ለማህበረሰቡ በማስተማር ከዚህ በፊት ቤተሰብን ከመመገብ አስቀድሞ ለገበያ ይቀርብ የነበረውን ምርት ቅድሚያ ለቤተሰብ የመመገብ ተገቢነት ላይ በተፈጠረው ግንዛቤ ለውጥ ማምጣት መቻሉ የዚሁ ፕሮግራም ውጤት ነው ።

የአረንጓዴ አሻራ በአለም ደረጃ ስጋት ሆኖ የሚገኘውን የካርቦን ልቀት የሚቋቋም እና ለሰው ልጅ ጤና ወሳኝ የሆነውን ነፋሻማና ለሰው እና ለእንስሳት ጠቃሚ የሆነ የአየር ንብረት እንዲኖር የሚያስችል በመሆኑ ጠቀሜታው የላቀነው።
በሌላ በኩል የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ትኩረቱን ያደረገው የደን እንጨቶችን ላይ ብቻ ሳይሆን፣ ለምግብነት እና ለኢኮኖሚ ጥቅም የሚውሉ የፍራፍሬ፣ ቡና እና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብት ተክሎች ላይ በማድረጉ ቀጥተኛ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ ይገኛል።

በተለይም የአቮካዶ፣ ማንጎ እና የፓፓያ ችግኞች በስፋት መተከላቸው የቤተሰብን አመጋገብ ማሻሻል ብቻ ሳይሆን ለሀገር ውስጥ ገበያ እና ለውጭ ኤክስፖርትም ትልቅ አቅም መፍጠር ተችሏል።

‎አረንጓዴ አሻራ ሀገራዊ የማምረት አቅምን በማጎልበት ፤ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ለሁለንተናዊ ሀገራዊ ልዕልና የሚደረገውን የመደመር ጉዞ የሚያረጋግጥ የሁለተኛው ትውልድ የአርበኝነት መገለጫ ነው።

በአጠቃላይ በአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ምድሪቱን በማከም ህዝቦቿ የአረንጓዴ አሻራ ፍሬውን እንዲያጣጥሙ፣ ለሀገራችን ኢኮኖሚ፣ለአካባቢ ጥበቃና ለትውልድ ጤና የሚያበረክተው የላቀ አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ በመሆኑ ለስኬታማነቱ ሁሉም ሊረባረብ ይገባል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ
ነሀሴ 5/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ  በእናቶች፣ ሕፃናት፣ አፍላ ወጣቶችና ወጣቶች እንዲሁም በሥርዓተ ምግብ  አገልግሎት የ2018 አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የውይይት...
11/08/2026

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ በእናቶች፣ ሕፃናት፣ አፍላ ወጣቶችና ወጣቶች እንዲሁም በሥርዓተ ምግብ አገልግሎት የ2018 አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ተጀመረ።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ | ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም.

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ የ2018 ዓ.ም. የእናቶች፣ ሕፃናት፣ አፍላ ወጣቶችና ወጣቶች እንዲሁም የሥርዓተ ምግብ ጤና አገልግሎት አፈጻጸምን ገምግሟል።

በግምገማው የዓመቱ ዋና ዋና ስኬቶችና የአፈጻጸም ክፍተቶች በመለየት፣ ከተሳካ ተሞክሮዎች በመማር ለ2019 ዓ.ም. የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ እንደገለጹት፣ በቢሮ ደረጃ እየተተገበሩ ያሉት “ለውጤት እንስራ” እና “ለላቀ ውጤትና ለጥራት እንስራ” ኢኒሼቲቮች በጤና ዘርፉ የሚታዩ ለውጦችን ለማፋጠን ወሳኝ አቅም ናቸው።

በተለይም የእናቶችንና የሕፃናትን ሕመምና ሞት መቀነስ፣ የሥርዓተ ምግብ ሥራዎችን ማጠናከርና የጤና አገልግሎቱን ውጤታማነት ማሳደግ በቅንጅት በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤት መመዝገቡን ዶ/ር ሰላማዊት ገልጸዋል።

እንደ ዶ/ር ሰላማዊት ገለጻ፣ የእናቶችና የሕፃናት ጤና ላይ የሚታየውን ለውጥ የበለጠ ለማፋጠን የተቀናጀና የጋራ ሥራ ያስፈልጋል።

ለዚህም በቀጣዮቹ ዓመታት የጤና ዘርፉን ለመምራት ከተዘጋጀው ሁለተኛው የጤና ዘርፍ መካከለኛ ዘመን ልማትና ኢንቨስትመንት ዕቅድ (HSDIP-II) ጋር በማጣመር መሥራት ይገባል ብለዋል።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ በበኩላቸው፣ በክልሉ ለአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ተደራሽ፣ ጥራት ያለውና ምቹ የጤና አገልግሎት ለማቅረብ በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል።

የእናቶች፣ ሕፃናት፣ ወጣቶችና ሥርዓተ ምግብ ጤና አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ኢመላ ላሜቻ ያቀረቡት የ2018 ዓ.ም. ዓመታዊ ሪፖርት የዓመቱን ዋና ዋና ስኬቶች፣ የአፈጻጸም ክፍተቶችንና በቀጣይ የጤና አገልግሎቱን ውጤታማነት ለማሳደግ የተቀመጡ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በዝርዝር አካቷል።

በ2018 ዓ.ም. በእናቶችና ሕፃናት ጤና ላይ የተመዘገቡ ውጤቶችን ወደ ቀጣይ የለውጥ ምዕራፍ ለማሸጋገር የተቀመጡት የ2019 ዓ.ም. የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎችም የአገልግሎቱን ጥራት፣ ተደራሽነትና ውጤታማነት ይበልጥ ለማሻሻል ያለሙ ናቸው።

የግምገማና የዕቅድ መድረኩ በ2018 ዓ.ም. የተመዘገቡ ስኬቶችን ለማጠናከር፣ የታዩ ክፍተቶችን ለመቅረፍና በ2019 ዓ.ም. የተሻለ የጤና ውጤት ለማስመዝገብ የጋራ የሥራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ታላሚ ያደረገ መሆኑ ተብራርቷል።

በመድረኩ የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ፣ የሆስፒታል ሥራ አስኪያጆች፣ የጤና ቢሮ የማኔጅመንት አባላት፣ የግል ጤና ተቋማት ተወካዮች፣ የአፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ማኅበራት፣ የዞንና ወረዳ ጤና ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም የጤና ልማት አጋር ድርጅቶች ተወካዮች ተሳትፈዋል።


የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ
ነሀሴ 5/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

የሲዳማ ጤና ቢሮ በ2018 ዓ.ም. በእናቶች፣ ሕፃናት፣ ወጣቶችና ሥርዓተ ምግብ አገልግሎት የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡን ገለጸየሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም.የሲዳማ ክልል ጤና...
10/08/2026

የሲዳማ ጤና ቢሮ በ2018 ዓ.ም. በእናቶች፣ ሕፃናት፣ ወጣቶችና ሥርዓተ ምግብ አገልግሎት የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡን ገለጸ

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም.

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ በ2018 ዓ.ም. በእናቶች፣ ሕፃናት፣ ወጣቶችና ሥርዓተ ምግብ አገልግሎት አበረታች አፈጻጸም ማስመዝገቡን ገለጸ።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊና የጤና ፕሮግራም ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ፣ 2018 ዓ.ም. ለጤናው ዘርፍ፣ በተለይም ለእናቶች፣ ሕፃናት፣ ወጣቶችና ሥርዓተ ምግብ ጤና አገልግሎት፣ የተሻለ አፈጻጸም የተመዘገበበት ስኬታማ ዓመት መሆኑን ገልጸዋል።

በዓመቱ ከተመዘገቡ ዋና ዋና ውጤቶች መካከል፣ የቅድመ ወሊድ ክትትልና የአልትራሳውንድ አገልግሎት መስፋፋት፣ የእናቶች ማቆያ ቤቶችን ማጠናከር፣ የሕፃናት ክትባት አፈጻጸምን ማሻሻልና የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን ማስፋፋት ይገኙበታል።

አቶ በላይነህ እንደገለጹት፣ በክልሉ የሚታየውን የጤና አገልግሎት ስኬት ለማረጋገጥና በ2030 የተቀመጡ የጤና ግቦችን ለማሳካት የተጀመረው ጥረት መጠናከርና መቀጠል እንደሚገባ አፅንዖት ሰጥተዋል።

ይህንንም ለማሳካት የተዘጋጀው የመማሪያ ጉብኝት፣ አንዱ የጤና ተቋም ከሌላው የተሻለ አሠራርና ተሞክሮ እንዲቀስም፣ በመሬት ላይ የተሳኩ ተሞክሮዎች ወደ ሌሎች ተቋማት እንዲስፋፉና የአገልግሎት ጥራት እንዲሻሻል እንደሚያግዝ ገልጸዋል።

የመድረኩ ዋና ዓላማ የ2018 ዓ.ም. አፈጻጸምን በመገምገም የተገኙ ውጤቶችንና ክፍተቶችን መለየት፣ ከተሳካ ተሞክሮ መማርና ለ2019 ዓ.ም. የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ ነው።

በመማሪያ ጉብኝቱ ተሳታፊዎች በ11 ቡድኖች ተከፍለው በተለያዩ የጤና ተቋማት የመስክ ምልከታ አድርገዋል። በጉብኝቱም የተመለከቷቸውን ጠንካራ አሠራሮች፣ ምርጥ ተሞክሮዎችና የአገልግሎት ክፍተቶች በመለየት ግብረ መልስ አቅርበዋል።

በቀጣዩ ቀን በይፋ በሚጀመረው መድረክ፣ የቢሮው የእናቶች፣ ሕፃናት፣ ወጣቶችና ሥርዓተ ምግብ ጤና አገልግሎት የ2018 ዓ.ም. አፈጻጸም፣ የተመዘገቡ ስኬቶችና ያሉ ክፍተቶች በጥልቀት ይገመገማሉ። በተጨማሪም ከተሳካ ተሞክሮዎች በመማር ለ2019 ዓ.ም. የጋራ የትኩረት አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በመድረኩ የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ፣ ከፌዴራል ጤና ሚኒስቴር የተወከሉ አካላት፣ የክልሉ ጤና ቢሮ የማኔጅመንት አባላት፣ የዞንና የወረዳ ጤና ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች፣ የጤና ተቋማት ባለሙያዎችና የጤና ልማት አጋር ድርጅቶች ተወካዮች ተገኝተዋል።


የሲዳማ ክልል መንግስት ጤና ቢሮ
ነሀሴ 4/2018 ዓ.ም

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ

Website: https://www.shb.gov.et

Facebook:
👇👇👇👇

https://www.facebook.com/share/1EUdJhqmFM/
https://www.facebook.com/1000649355740¡57/posts/1065870482254128/

Telegram : https://t.me/SidamaRHB

Twitter: https://x.com/sidama_health_bureau

WhatsApp:
https://chat.whatsapp.com/K7W4vwM1mqG8SyGz4PYC71

YouTube:

https://youtube.com/?si=bjGP9rGIpwIlZWQX

Tik Tok:
https://vm.tiktok.com/ZMBCWXXxa/

Address

Awassa

Telephone

+251462211767

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama National Regional State Health Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share